የቀለሙ ልጅ

ከጸሐፊው ማስታወሻ…

አባቴ ሲጠራ ሲነሣ ሰማሁኝ
የአብራኩ ክፋይ የቀለሙ ልጅ ነኝ
አባቴን አታንሳው እኔ እበቃለሁኝ
አባትህ ተረት ነው ብለህ ለጠየከኝ…

በእንተ ዕለተ ስቅለት

ጨረቃ ደም ሆነች፤ ፀሐይም ጨለመ
ከዋክብት ረገፉ፤ ሐኪሙ ታመመ
ልዑል ተዋረደ፤ ጌታ ሎሌ ሆነ
ፈጣሪ ሠራው ፍጡሩ በየነ…

ቀራንዮ

ቀራንዮ … ቀራንዮ …ቀራንዮ ጎልጎታ

የተለየሽው ከሁሉ ቦታ

የመከራ ቤት የደም ማማ

የመስቀል ዙፋን የግፍ አውድማ…

ሆሣዕና በአርያም

ሆሣዕና በአርያም . . . ሆሣዕና በአርያም

ለዳዊት ልጅ መድኃኔ ዓለም

በጌታ ስም የሚመጣ

ከምርኮ ሀገር ከባርነት የሚያወጣ

ቃና

የተስፋው ቃል

በአንዲት ፍሬ ቅጠል ሕይወትን አጥቼ
ርስቴን ተነጠኩ የሞት ሞትን ሙቼ
በግዞት ተነዳሁ በድቅድቅ ጨለማ
ወደ ፍዳ መንደር ወደ ሞት ከተማ…

በአታ ለማርያም

ጥንትም ስትታሰብ በአምላክ ኅሊና

ትታወቅ ነበረ በሥሉስ ልቡና

በአቷን አደረገች የአርያም መቅደስ

የዓለሙን ፈጣሪ ዘወትር ለማወደስ…

እውነተኛ ፍቅር

መስቀሉን ይሸከም

ሊሄድ በ’ኔ መንገድ

ሊከተል የሚወድ

ራሱን ይካድ…

ሥራህን ሥራ

በሁዳዱ መሬት መልካም በሚያፈራው

ሠራተኛው ጥቂት መኸሩ ብዙ ነው…