አንተ ጽኑ አለት ነህ

በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ

እያለ ሲነግረው ጌታችን  ለጴጥሮስ

በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር

በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር

ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር

መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!

ግእዝ ዘኢትዮጵያ

እፎ ኃደርክሙ…

ተናገረው ይውጣ እንጂ አንደበትህ አይዘጋ
የአባቶችህ መገለጫ ዜማቸውን አትዘንጋ

አብረን እንዘምር!

ጌታ ተወለደ በትንሿ ግርግም፤

በከብቶቹ በረት ከድንግል ማርያም፡፡

እርሷም ታቀፈችው የተወደደ ልጇን፤

ሰማይና ምድር የማይወስነውን፡፡

ዕግትዋ ለጽዮን

ያች ያማረ ወርቅን የተጫማች

እንደአጥቢያ ጨረቃ ብርሃን የተመላች

ለክረምቱ ስደት መጠለያ ሆነች

ጽዮንን ክበቧት ሰማይ ታደርሳለች!

ቸሩ እረኛዬ

ሰላምን ስሻ በአንተ አምኜ
በጭንቅ በነበርኩበት እጅጉን አዝኜ
በዚህች በከንቱ ዓለም በጨለማ ሆኜ
ፈጥነህ ደረስክልኝ ሆነኸኝ አጽናኜ

ጽኑ ተስፋ

ተድላ እና ደስታ ከሞላባት ገነት
ሥርዓተ ጾም ነው የተተከለባት
ደግሞም በሌላ መልክ የሞት ሕግ አለባት
የሕጉን ጽንዐት አዳም ጠነቀቀ
ከእባብም ሽንገላ ራሱን ጠበቀ…

ስለጥቂቶች

የምጽአት ቀን መቃረብን ሥራችን ሲመሰክር

ክፉ ግብር ሚዛን  ደፍቶ በዓለም ግፍ ሲመነዘር

ኃጢአት የወለደችው የጥፋት ቀን እንዲያጥር

ጻድቃንን ባያስቀርልን ሁላችን በጠፋን ነበር

ሥጋን ለነፍስ አስገዝተው በበረኃ ጉያ የከተሙ

ቤተ ክርስቲያን ልጆች አሏት የሚማልዱ ለዓለሙ

በፊትህ ናት

በኀምሳኛው ዕለት መንፈስ ቅዱስ ሲያድርባቸው

በ፸፪ የተለያየ ዓይነት ቋንቋቸው

ሲናገሩ ተገረሙ አሕዝቡ ሰምተው

በእግዚአብሔር ሥራ እጅግ ተደንቀው

የወንጌሉን ቃል ሲረዱ ተነክቶ ልባቸው

ሦስት ሺህ ነፍሳትም ተጠመቁ አምነው…

የቀለሙ ልጅ

ከጸሐፊው ማስታወሻ…

አባቴ ሲጠራ ሲነሣ ሰማሁኝ
የአብራኩ ክፋይ የቀለሙ ልጅ ነኝ
አባቴን አታንሳው እኔ እበቃለሁኝ
አባትህ ተረት ነው ብለህ ለጠየከኝ…

በእንተ ዕለተ ስቅለት

ጨረቃ ደም ሆነች፤ ፀሐይም ጨለመ
ከዋክብት ረገፉ፤ ሐኪሙ ታመመ
ልዑል ተዋረደ፤ ጌታ ሎሌ ሆነ
ፈጣሪ ሠራው ፍጡሩ በየነ…