መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ጾመ ነነዌ
ምሕረቱ የበዛው አምላካችን የነነዌ ሰዎችን ይቅር እንዳላቸው ሁሉ እኛንም ጸሎታችንን ሰምቶ፣ ልመናችንን ተቀብሎና ጾማችንን አስቦ ምሕረትን ያደርግልን ዘንድ ከክፋት ርቀን፣ ከቂም በቀል ከጥላቻ ነጽተን፣ በበጎነትና በመልካም ምግባር ጾሙን እንጹም!
“እግዚአብሔር ብርሃኔ ነው” ቅዱስ ዑራኤል
በቅዱስ ፈቃዱ ዓለምን የፈጠረው ሁሉን ቻይ አምላካችን እግዚአብሔር መላእክትን ከእሳትና ከነፋስ በቀዳሚት እሑድ ሲፈጥራቸው በነገድና ከተሞች ከፋፍሎ እንደነበርና ለእያንዳንዱም ሊቃነ መላእክት እንደሾመላቸው የመጽሐፍተ ፍጥረታት ይጠቅሳሉ፡፡
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
በዚያም ተጽናንታ በምድር ኖረችበት
የአምላክ እናት ለ፷፬ ዓመታት
አብዝታ በመመላለስ ሳታቋርጥ ጸሎት
በጌቴሴማኒ መቃብሩ ቤት
ጊዜው ደረሰና ከተወደደው ልጇ የምትሄድበት
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና
ሥዕለ አድኅኖ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ዘመነ አስተርእዮ ተብሎ በሚጠራው ወርኃ ጥር በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ብዙ በዓላትን አክብረናል፤ የጥምቀት፣ የቃና ዘገሊላ እንዲሁም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ ዓመታዊ ክብረ በዓልና የቅዱሳን መላእክት፣ የቅዱሳን አባቶቻችን፣ እናቶቻችንን በዓላት አክብረናል፡፡ እንዴት ነበር ልጆች! በጣም ልዩ ነበር አይደል? ታዲያ እነዚህ መንፈሳዊ በዓላት ወደፊትም እንዲከበሩ የእናንተ ጉልህ አስተዋጽኦ ያስፈልጋል፤ ምክንያቱም የነገዋን አገርና ቤተ ክርስቲያን የምትረከቡት እናንተ ስለሆናችሁ በዓሉን ከማክበራችሁ በተጓዳኝ ለምን እንደሚከበርና የአከባበበር ሥርዓቱን በመጠየቅ መረዳት አለባችሁ፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ታዲያ ይህን አደራ ለመረከብ በመንፈሳዊውም፣ በዘመናዊው ትምህርት ጎበዞች መሆን አለባችሁ! በነገራችን ላይ ዘመናዊ ትምህርታችሁ የመንፈቀ ዓመት ፈተናችሁን እየተፈተናችሁ ያላችሁ፣ ለመፈተንም በዝግጅት ላይ ያላችሁም በርትታችሁ ማጥናት እንዳለባችሁ መዘንጋት የለበትም፡፡ ልጆች! ባለፈው ትምህርታችን በሥዕለ አድኅኖ ከተደረጉ ተአምራት ለአብነት ያህል ተመልክተን ነበር፤ ለዛሬ ደግሞ ቅዱሳን ሥዕላትን እንዴት አክብረን መያዝ እንዳለብን እንመለከታለን፡፡
ሕፃኑ ሰማዕት
ግብዝና ደካማ የሆነው የሰውን ሥጋ አሸንፎ፣ መከራን ተቀብሎ፣ ችግርን ተቋቁሞ፣ ፈተናን አልፎ መንፈሳዊ ሕይወትን ለመኖርና ክርስቲያን ለመሆን የሚደረገው ትግል እራሱን የቻለ ተጋድሎ እንደሚያስፈልገው የታወቀ ነው፡፡ እውነተኛ ለሆነው የክርስትና እምነተና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖት የሚከፈለው መሥዋዕትም የተለየ ስፍራ አለው፡፡
የቃና ዘገሊላ ሰርግ
በቃና ሰርግ ቤት የተደረገው ተአምር የአዳዲስ አማኞችንና የሐዋርያትን እምነት ለማጽናትም የተደረገ በመሆኑ፣ ወንጌላዊው ዮሐንስ “ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ” ይለናል። እመቤታችን ድንግል ማርያምም ጌታችን ማንነቱ የሚገለጥበት ጊዜ መድረሱን አውቃ “የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው። ጌታችንም “ጊዜዬ ገና አልደረሰም” ማለቱ፣ በወቅቱ ያልነበረው ይሁዳ መጥቶ ተአምሩን እንዲያይና ለወደፊት “እኔ በሌለሁበት ተአምር አድርጎ ለየኝ” የሚል ምክንያት እንዳይኖረው ለማድረግ እንደሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጒሞታል፡፡
በዓለ ጥምቀት
በጥር ዐሥራ ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ።
ለፈጣሪ በበጎ ፈቃድ መገዛት ይገባል!
ሰው በራሱ ፈቃድ በጎ አልያም በክፉ ሐሳብና ምኞት መጥፎ ሊሆን ይችላል፡፡ የአዳም ዘር ጥንተ ተፈጥሮውን ዐውቆና ተረድቶ በድንቅ ሥራው ለፈጠረው አምላክ ተገዢ የመሆን ፈቃድም የራሱ ነው፡፡ በውዴታ ብቻ ሳይሆን በግዴታም ለፈጣሪ መገዛት እንዳለብን ቅዱሱ መጽሐፍ ያስተምረናል፡፡
በዓለ ግዝረት
በዘመነ ብሉይ ግዝረት የተጀመረው በአባታችን አብርሃም ነበር፤ በዚያን ጊዜ የነበሩ ሕዘበ እግዚአብሔር ከአሕዛብ የሚለዩበትና ክብር የሚያገኙበት ሕግ መጽሐፊያዊ ግዝረት ነበር፡፡ ያም እንደ ጥምቀት ይሆንላቸው ነበርና ነው፡፡ (ዘሌ.፲፪፥፫)
በበረት ውስጥ እነሆ ተወለደ!
ሰማያትን በደመና የሚጋርድ፣
ተወለደ በዐውድ
እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች፣
የጸብ ግርዶሽ ተቀዳዶ ሰላም ሆኗል በላይ በታች፡፡
፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈጸመ
አምላክ ወሰብእ በግርግም ውስጥ ከበጎች ጋር ከተመ!