መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹ልጆች ሆይ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ›› (ኤፌሶን ፮፥፩)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የሁለተኛው መንፈቅ የትምህርት ዘመን እንዴት ነው? ከቀደመው ይልቅ የበለጠ ጠንክራችሁ በመማር ዕውቀትን በመሸመት ጥሩ ውጤትን ለማምጣት እየጣራችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው!
ልጆች! ዐቢይ ጾምን አንድ ብለን እየጀመርን ነው፤ እንደ ዐቅማችሁ ለመጾም እንደምትጥሩም እምነታችን ነው፤ በርቱ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መንፈሳዊ ትምህርትንም መማርም እንዳትዘነጉ፤ መልካም! ልጆች ለዛሬ ስለ መታዘዝ እንማራለን፡፡
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!
ዘወረደ
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም” እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)
በዓለ ኪዳነ ምሕረት
ሰአሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት፣ ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ማኅደረ መለኮት፣ ብፅዕት፣ ከፍጥረት ይልቅ የተመሰገነች፣ እመ ብዙሃን፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለፍጥረት ሁለ ድኅነት ይሆን ዘንድ ከተወደደ ልጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን የተከበረች ናት፡፡
“የጠገበች ነፍስ የማር ወላላ ትረግጣለች፤ ለተራበች ነፍስ ግን የመረረ ነገር ሁሉ ይጣፍጣታል።” (ምሳሌ ፳፯፥፯)
ንጉሥ ሰሎሞን የሰው ልጅ በጥጋብ ሲኖር ፈጣሪው እግዚአብሔርንም እንኳን እንደሚረሳ “የጠገበች ነፍስ የማር ወለላ ትረግጣለች” እያለ የጥበብ ቃልን ተናገረ። ለፈቃድ መገዛት እና ሆዳምነት ጠቢቡ እንደተናገረ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግሞ ሲነገር በሊቃውንት አበው በተስፋ ተገልጧል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስ ወንጌልን በተረጎመበት ፵፭ኛ ድርሳኑ ሆዳምነት የሰው ልጆችን ወደ ዲያብሎስ መንገድ የሚወስድ የጥፋት ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ይነግረናል። “ከሆዳምነት በላይ የከፋ እና አዋራጅ ምንም ነገር የለም። አእምሮን ያፈዛል፣ ነፍስን በጠፊ ሐሳብ ያስራል፣ የያዛቸውንም ሰዎች አውሮ እንዳያዩ ያግዳቸዋል።” [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ትርጓሜ ወንጌለ ዮሐንስ፣ ድርሳን ፵፭]
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም መንፈሳዊ ተቋማትን ለመገንባት ከሚቻልባቸው መሠረታዊ ተግባራቶች የምሕንድስና ሙያ ቀደምት ተጠቃሽ እንደመሆኑ በሀገራችን እንዲሁም በውጭ ሀገር ለሚገኙት የቤተ ክርስቲያናትና አድባራት ግንባትና መልሶ ማቋቋም ሥራ መሐንዲሶች እጅጉን ተፈላጊዎች ናቸው፡፡ በተለይም በሀገራችን ውስጥ ያሉ ቤተ ክርስቲያናት በጠላቶች ሥውር ደባና ጥቃት፣ ምዝበራ፣ ቃጠሎ እንዲሁም መራቆት የደረሳበቸው በመሆኑ እነዚህን ቤተ ክርስቲያናት መልሶ ለመንባትና አዳዲሶችን ለማነጽ በታቀደው ሥራ መሠረት የማኅበረ ቅዱሳን የምሕንድስና ባለሙያዎች ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል፡፡
የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂን በማበልጸግም ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉ በርካታ ድረ ገጾችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ለስብከተ ወንጌል ተደራሽነትና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ጥንካሬ ለመጨመር ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው፡፡ በመደበኛና በኢ-መደበኛ ዳታቤዝና ሲስተም ዴቨሎፕመንት ባለሙያ በሆኑ አገልጋዮች በመታገዝ ከተካተቱት ዋና ተግባራት በጥቅል ሲገለጽ የኮምፒዩተር ሲስተም እና የመረጃ ቋት ፍሎጎቶች ላይ ተስማሚ ቴክኖሎጂ በመጠቆም፣ በማበልጸግ እና ለብልሽቶች እንዲሁም ለጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ይሰጣል፡፡
ማኅበራዊ አገልግሎትን በተመለከተ ለምእመናን በልዩ ልዩ መንገዶች ግንዛቤ በመስጠት የማኅበራዊ አገልግሎት ተሳትፏቸውን ያሳድጋል:: ኦርቶዶክሳዊያን በማኅበራዊ አገልግሎት ያላቸው ተሳትፎ እንዲያድግ ስልት ቀይሶ ይተገብራል፤ የከፍተኛ ትምህረት ተቋማት ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በማኅበራዊ፣ በሥራ ፈጠራና በኢኮኖሚ ተጽእኖ ፈጣሪ የሚሆኑበትን ትምህርት ክፍል እንዲመርጡ የተለያዩ ግንዛቤ እና ሥልጠና ይሰጣል::
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ሁሉ መሰብሰቢያችን በመሆኗ ቅድስት ቤታችንን ልናንጽና ልንጠብቅ እንደሚገባ ቅዱስ ቃሉ እንዲህ ሲል አስተምሮናል፡ ‹‹ቤቴንም ሥሩ፡፡›› የእግዚአብሔር ቤት ቅድስናው ተጠብቆና ሥርዓቱ ሳይፋለስ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ቅድስት ቤቱን በአምሳለ ግብሩ ተምሳሌት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን እናንጻለን፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንን የመገንባት ወይም የማስገንባት ሥራን የማካነወን ተልእኮ ማኅበረ ቅዱሳን ሥራዬ ብሎ የያዘው ተግዳሮት ነው፡፡ ማኅበሩ ለምእመናንና ለአብያተ ክርስቲያናት የሙያ አገልግሎት እንዲሰጥ ዕቅድና ስትራቴጂ በማውጣት በተለይም በገጠር ያሉ አብያተ ቤተ ክርስቲያናትንና ሕንጻ ግንባት ያንጻል፤ ያሳንጻል፡፡ (ሐጌ.፩፥፰)
“ስለ ምን ጾምን?” (ኢሳ.፶፰፥፫)
የነነዌ ከተማ ሰዎች ኃጢአት በትንቢተ ዮናስ ውስጥ አንድ ሁለት ተብሎ አልተገለጸም፤ በጥቅሉ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ” ተብሎ በእግዚአብሔር ከመገለጹ በቀር አልተዘረዘረም። (ዮናስ ፩፥፪) ሆኖም ክፉታቸው ወደ ፊቴ ወጥቶአልና የሚለው የልዑል አምላክ ቃል የኃጢአታቸውን ታላቅነት ያመለክታል። ኃጢአታቸው በዮናስ መጽሐፍ ውስጥ አልተዘረዘረም አልን እንጂ በሌሎቹ መጻሕፍት ውስጥ ግን ተዘርዝሯል። ለምሳሌ ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኃጢአት ምን ምን እንደነበረ ገልጿል። እነዚህም፡-
ወርኃ የካቲት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ስድስተኛው ወር “የካቲት” ተብሎ ይታወቃል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል “ከተተ” ከሚለው ግስ ከወጣው “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን በቁሙ “የወር ስም፣ ስድስተኛ ወር፣ የመከር ጫፍ (መካተቻ)፣ የበልግ መባቻ ማለት ነው” ብለው ተርጉመውታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲፭)
ሌሎችም ጸሐፍያን “የካቲት” የሚለው ቃል “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን “መውቃት፣ ማምረት፣ መሰብሰብ፣ መክተት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል ካሉ በኋላ ይህንም ስም ያገኘው የካቲት ወር አዝመራ (ምርት) ወደ ጎተራ የሚከተትበት ወራት በመሆኑ ነው ብለዋል። (ኅብረ ኢትዮጵያ፣ ከቴዎድሮስ በየነ፣ አዲስ አበባ ፲፱፻፺፱ ዓ.ም፡፡ አንድሮ ሜዳ፣ ገጽ ፫፻፺፭፣ አቡሻክር የጊዜ ቀመር፣ በኢንጅነር አብርሃም አብደላ ገጽ ፵፱) በቁጥር ትምህርት አንዱ ወር በባተበት የትኛው ወር እንደሚብት በቃል የሚጠና ሲሆን የካቲት በባተችበትም ጳጕሜን እንዲሁም የካቲት በባተበት ሳኒታ ሰኔ ይብታል፡፡
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ፳፻፲፯ ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት ዐዋጅ መግለጫ
‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ ጉባኤውንም ዐውጁ፤ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።›› (ኢዩ.፩÷፲፬)