መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች
የፍቅር ባለቤት፣ የምሕረት ጌታ፣ የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት፣ የሰው ልጆች ቤዛ ጌታችን በተወለደባት በኢየሩሳሌም ከተማ በቤተ መቅደሱ አቅራቢያ የምትገኝ በዕብራይስጥ ቋንቋ “ቤተ ሳይዳ” በአማርኛው ደግሞ “የምሕረት ቤት” የተባለች የመጠመቂያ ቦታ ነበረች፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? የግማሽ ዓመት ትምህርት ተጀምሯልና በደንብ ትኩረት ሰጠታችሁ መማር ይገባል! ልጆች! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! በባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን “ሃይማኖት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ “ሀልዎተ እግዚአብሔር” ማለትም ዓለምን ሁሉ የፈጠረ የአምላካችን የእግዚአብሔር መኖር በምን እንደሚታወቅ እንማራለን፤ ተከታተሉን!
ሰው ሲቀደስም ሲረክስም የሚኖረው በፈቃደ ሥጋ እና ፈቃደ ነፍስ መካከል ባለው የአሸናፊነትና ተሸናፊነት ትግል ነው፡፡የተቀደሰ ጾምን በተቀደሰ ሥርዓት ጹመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እናገኝ ዘንድ በሥርዓቱ፣ በትሕትና፣ በንስሓና በተሰበረ ልቡና ሆነን ልንጾም ይገባል።
ዓለም ሁሉ ተሰብስቦ ቢመዘን አንድ የራሷን ፀጉር የማያህል ደግ ፍጥረት፣ ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች፣ ንጽሕናዋንም ይሁን ቅድስናዋን ፍጥረት በአንደበቱ ተናግሮም ሆነ ጽፎ የማይጨርሰው፣ የአምላክ ማደሪያ፣ እመ አምላክ፣ እመ ብዙኃን፣ ሰዓሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት የከበረ በዓል ነው፡
ነቢዩ ኤልያስ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች ! እንዴት አላችሁ? ባለፈው ትምህርታችን ስለ ቅዱሳን ነቢያት፣ እነርሱ ስለ ጾሙትና የነቢያት ጾም ተብሎ ስለሚጠራው ጾም በጥቂቱ ተመልክተናል፤ለዛሬ የምንነግራችሁ ደግሞ ስለ ከቅዱሳን ነቢያት አንዱ ስለሆነው ስለ ነቢዩ ኤልያስ ነው፡፡
መልእክተኛውም ሚክያስን ‹‹እነሆ ነቢያት ሁሉ በአንድ አፍ ሆነው ለንጉሡ መልካሙን ይናገራሉ፤ ቃልህም እንደ ቃላቸው እንዲሆን መልካም እንድትናገር እለምንሃለሁ›› ይለዋል፡፡ (፩ኛ ነገ.፳፪፥፲፫) ነቢዩ ግን ‹‹ሕያው እግዚአብሔርን! እግዚአብሔር የሚነግረኝን እርሱን እናገራለሁ›› አለው፡፡
ምስጋና ለሥሉስ ቅዱስ ይድረስና ሁልጊዜ በየዓመቱ በኅዳር ፳፬ ቀን እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን የካህናተ ሰማይ (ሱራፌ) በዓልን እንድናከብር አባቶች ሥርዓትን ሠርተውልናል፡፡
፭፻ ዓመታት ገደማ በእስራኤል ብዙ ገቢረ ተአምራትን ስታደርግ የነበረችዋ በሙሴ የተቀረጸች ታቦት በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል ለኢትዮጵያ ተሰጠች።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ኅዳር ፳፩ ቀን በታላቅ ክብር ታከብረዋለች፡፡ካህናቱም ከዋዜማው ጀምረው በከበሮና በጸናጽል ስብሐተ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፡፡በጽዮን ፊት እንደ የመዓርጋቸው ቆመው ‹‹እግትዋ ለጽዮን ወህቀፍዋ፤ ጽዮንን ክበቧት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ›› እያሉ ይዘምራሉ፡፡
የእግዚአብሔር ሰዎች ትክክለኛና እውነተኛ ሰዎች በመሆናቸው የተናገሩት ሁሉ የሚፈጸም ነው፡፡ በአንደኛ ሳሙኤል መጽሐፍ ላይ እንዲህ የሚል ቃል አለ፤ ‹‹…እነሆ አንድ የእግዚአብሔር ሰው በዚህች ከተማ አለ፤ እርሱም የተከበረ ሰው ነው፤ የሚናገረውም ሁሉ በእውነት ይፈጸማል …፡፡›› (፩ኛሳሙ.፱፥፮)
ውድ የዚህ ጽሑፍ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ዘመነ ክረምቱን/ዘመነ ጽጌን እግዚአብሔር ረድቶን ብዙ ተምረንበት አልፏል፡፡ከፊታችን ኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ ፳፰/፳፱ ድረስ ደግሞ ዘመነ ነቢያትን የምንዘክርበት፣ ‹‹ጾመ ነቢያት›› ብለን ከጾም ጋር አገናኝተን ስለ ነቢያትና ነቢይነት፣ እንዲሁም ስለ ትንቢት ዓላማና ምክንያቱ ቤተ ክርስቲያን ብዙ የምታስተምርበት ወቅት ነው፡፡