ማይኪራህ
ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤
ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤
ኃጢአቴን ደምስሶ ወገኑ ሊያደርገኝ
ኢየሱስ ክርስቶስ በፍቅር ተቀበለኝ
ይህን የዓለም መድኅን የበጐች እረኛ
የድንግል ማርያም ልጅ የእውነት መገኛ
ከአብ የተላከ ለአዳም ዘር ሁሉ እንዲሆን መዳኛ
በሚያስፈራ ግርማህ በምጽዓት ቀን ስትገለጥ
በፊትህ የሚቆም ጠፍቶ ዓለም ሁሉ ሲንቀጠቀጥ
መልካሙን ዘር ከክፉው አበጥረህ ስትለያቸው
በፍርሃት ያርዳል የጽድቅ ፍሬ ለሌላቸው
ለእኔም ጨንቆኛል ዳግም የምትመጣበት
በደሌ ተቆጥሮ በሥራዬ የምመዘንበት
በእስራኤል ምድር በሰማርያ ላይ አክዓብ ነገሠ
ጣዖትን አቆመ …መለከትን ነፋ …ለበኣል ደገሠ
የቤተ መቅደሱ መሠዊያው ፈረሰ
የእግዚአብሔር ካህናት ደማቸው ፈሰሰ
በሰማርያ ረኃብ በጸናበት ዘመን የሚቀመስም ጠፋ፤ ከረኃቡ ጽናት የተነሣ እናት ልጇን እስከ መብላት ደረሰች። በእዚያም ሀገር ኤልሳዕ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ነበረ። እንዲህም አለ፤ ነገ በዚህች ከተማ በአንድ ሰቅል አንድ መሥፈርያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል ሁለት መስፈርያ ገብስ ይሸመታል። ያኔ ንጉሡ በእግዚአብሔር ላይ ተገዳደረ፤ እንዴት ይቻላልም አለ። የእግዚአብሔር ሰው ኤልሳ እንዲህ አለው፤ “ታየዋለህ እንጅ አትቀምሰውም” ልብን የሚከፍል ንግግር! በረኃብ የቆየች ሀገር ደስ በምትሰኝበት ሰዓት የማይጨበጥ ሕልም ሲሆን ምንኛ ያሳዝናል? የሶርያ ንጉሥ ሲመኘው የኖረውን ነገር በዓይኑ አየው ግን አልቀመሰውም። (፪ኛነገ.፯፥፪)