አንተ ጽኑ አለት ነህ
በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ
እያለ ሲነግረው ጌታችን ለጴጥሮስ
በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር
በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር
ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር
መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!
በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ
እያለ ሲነግረው ጌታችን ለጴጥሮስ
በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር
በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር
ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር
መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!
ሰላምን ስሻ በአንተ አምኜ
በጭንቅ በነበርኩበት እጅጉን አዝኜ
በዚህች በከንቱ ዓለም በጨለማ ሆኜ
ፈጥነህ ደረስክልኝ ሆነኸኝ አጽናኜ
ተድላ እና ደስታ ከሞላባት ገነት
ሥርዓተ ጾም ነው የተተከለባት
ደግሞም በሌላ መልክ የሞት ሕግ አለባት
የሕጉን ጽንዐት አዳም ጠነቀቀ
ከእባብም ሽንገላ ራሱን ጠበቀ…
የምጽአት ቀን መቃረብን ሥራችን ሲመሰክር
ክፉ ግብር ሚዛን ደፍቶ በዓለም ግፍ ሲመነዘር
ኃጢአት የወለደችው የጥፋት ቀን እንዲያጥር
ጻድቃንን ባያስቀርልን ሁላችን በጠፋን ነበር
ሥጋን ለነፍስ አስገዝተው በበረኃ ጉያ የከተሙ
ቤተ ክርስቲያን ልጆች አሏት የሚማልዱ ለዓለሙ
በኀምሳኛው ዕለት መንፈስ ቅዱስ ሲያድርባቸው
በ፸፪ የተለያየ ዓይነት ቋንቋቸው
ሲናገሩ ተገረሙ አሕዝቡ ሰምተው
በእግዚአብሔር ሥራ እጅግ ተደንቀው
የወንጌሉን ቃል ሲረዱ ተነክቶ ልባቸው
ሦስት ሺህ ነፍሳትም ተጠመቁ አምነው…
ከጸሐፊው ማስታወሻ…
አባቴ ሲጠራ ሲነሣ ሰማሁኝ
የአብራኩ ክፋይ የቀለሙ ልጅ ነኝ
አባቴን አታንሳው እኔ እበቃለሁኝ
አባትህ ተረት ነው ብለህ ለጠየከኝ…
ጨረቃ ደም ሆነች፤ ፀሐይም ጨለመ
ከዋክብት ረገፉ፤ ሐኪሙ ታመመ
ልዑል ተዋረደ፤ ጌታ ሎሌ ሆነ
ፈጣሪ ሠራው ፍጡሩ በየነ…
ፖስታ ሳጥን ቁጥር ፡ 80078
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
ድረገጽ: www.eotcmk.org
ጌታ ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰጥቶታል ያንን መስራት የእሱ ፈንታ ነዉ። ቢቻለዉ እሱን ማገድ የዲያብሎስ ሥራ ነዉ። በእርግጥ ሥራዉን እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሰይጣን ሊያግድህ ይሞክራል። ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል። በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል የሐሜት ጎርፍ ያስወርድብሃል። ደራሲያን ኦንዲጠይቁህ እጅግ ስመ ጥሩ ሰዎችም በክፋ እንዲናገሩብህ ይጠቀምባቸዋል። ጲላጦስ፥ሄሮድስ፥ሀናንያ፥ቀያፋ ሁሉም በአንተ ላይ ያድማሉ . . . አንተ ግን በፀና ውሳኔ በማያወላውል ቅናት በመጨረሻ ላደርገው የሰጠኽኝን ስራ ፈፀምኩ ሃይማኖቴንም ጠበቅሁ ለማለት እስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማ እና የተፈጠርክበትንም ግብ ተከተል።
አባ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፩፱፫፪፡፩፱፰፪ ዓ.ም.