ጥምቀት
/in በዓላት, ትምህርተ ሃይማኖት /by Mahibere Kidusanበዘመነ ሥጋዌ በናዝሬት ከተማ፤ ዮርዳኖስ ወንዝ የእስራኤል ሕዝብ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ተራ ይዘው በሚጠብቁበት ጊዜ እርሱ እንዲህ እያለ ይሰብክ ነበር፤ ‹‹እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው መቅሠፍት ታመልጡ ዘንድ ማን ነገራችሁ? እንግዲህ ለንስሓ የሚያበቃችሁን ሥራ ሥሩ፤ አብርሃም አባታችን አለን …
ልደተ ክርስቶስ
/in በዓላት, ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusan‹‹እነሆ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፡፡…››
የተስፋው ቃል
/in ኪነ ጥበብ /by Mahibere Kidusanበአንዲት ፍሬ ቅጠል ሕይወትን አጥቼ
ርስቴን ተነጠኩ የሞት ሞትን ሙቼ
በግዞት ተነዳሁ በድቅድቅ ጨለማ
ወደ ፍዳ መንደር ወደ ሞት ከተማ…
ልደቱ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት
/in በዓላት, ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusanከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሆኖ የሥላሴን መንበር ያጠነው ጻድቁ አባት አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱበት ዕለት የተቀደሰች ናት፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ለአባታቸው ካህኑ ጸጋ ዘአብና ለእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ ባበሠራቸው መሠረትም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ ኢቲሳ በሚባል ቦታ በታኅሣሥ ፳፬፤ ፲፪፻፲፪ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ በሦስተኛው ቀን እሑድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ አንዱ አብ ቅዱስ ነው፤ አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው፤ አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡
‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ!›› (ማቴ.፯፥፲፭)
/in ስብከት /by Mahibere Kidusanነቢይ ማለት ተነበየ፣ ተናገረ ከሚለው የግእዝ ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም ወደፊት ስለሚሆነውና ስለሚመጣው አስቀድሞ መናገር፣ መተንበይ ማለት ነው፡፡ ከዚህም በተመሳሳይ ‹ናቪ› ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተገኘ ስያሜ ነው፤ መምራት፣ ማብሠር፣ መምከር፣ መንገር የሚል ትርጓሜም አለው፡፡ ይህ ቃል ወደ ግሪክ ሲተረጎም ‹ፕሮፌቴስ› ወይንም ‹ፕሮ› እና ‹ፌሚ› ከሚሉት ጥምር-ቃላት የተገኘ በመሆኑ ‹ፕሮ› ቅድሚያ፣ ከአንድ ነገር በፊት ማለትን ሲያመለክት ‹ፌሚ› ደግሞ መናገር፣ ማብሠርና ማሳወቅ ማለት እንደሆነ መምህር ብዙነሽ ስለሺ ‹ትምህርተ ሃይማኖት› በተሰኘው መጽሐፋቸው ውስጥ ገልጸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ‹ፕሮፌቴስ› የወደፊቱን ነገር አስቀድሞ መናገር፣ ማብሠር ወይም ማሳወቅ የሚል ትርጓሜ እንዳለው እንረዳለን፡፡ ምዕራባውያን በመጽሐፍ ቅዱሳቸው ውስጥ ቃሉን ‹ፕሮፌት› በሚለው ሲጠቀሙ የሴሜቲክ ቋንቋ ዘር የሆነው ግእዝ ከዕብራይስጡ ቃል ‹ናቪ› የሚቀራረብ ትርጓሜ በመውሰድ ነቢይ የሚለውን ቃል ይጠቀማል፡፡ (ትምህርተ ነቢያት ገጽ ፲፩)
የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል
/in በዓላት, ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusanበንጉሥ ናቡከደነፆር ዘመነ መንግሥት እስራኤላውያንን በባቢሎናውያን ቅኝ ግዛት ሥር በወደቁበት ጊዜ ከአይሁድ ወገን የሆኑ አዛርያ፣ አናንያ እና ሚሳኤል የተባሉ ሦስት ሕፃናትም ተማርከው በባርነት ተወሰዱ፡፡ ንጉሡም መልካቸው ያመረ፣ የንጉሣዊና የመሳፍንት ልጆች የሆኑትን መርጦ ሥነ ጥበብ፣ የመንግሥት አስተዳደርና የባቢሎናውያን ቋንቋዎችን እንዲሠለጥኑ ለማድረግ በቤተ መንግሥቱ አስቀመጦ ይቀልባቸው ጀመር፡፡…
‹‹አባታችሁ አብርሃም የእኔን ቀን ያይ ዘንድ ተመኘ፤ አይቶም ደስ አለው›› (ዮሐ. ፰፥፶፮)
/in ስብከት /by Mahibere Kidusanጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሰበከበት በዘመነ ሥጋዌ እርሱ የሚያስተምረውን ትምህርት እና የሚያደርገውን ገቢረ ተአምራት ወመንክራት ሰምተውና አይተው አይሁድ ቅናት አደረባቸው፡፡ ጌታችንንም በክፋት በሚከታተሉበት ጊዜ የእርሱን ጌትነትና የባሕርይ አምላክነት በትምህርት እየገለጠ ብዙ ተአማራት ቢያሳያቸውም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ እንዲሁም በሥጋ ተገልጦ ሲመላለስ ስላዩት አምላክነቱን ተጠራጥረው እንዲህ አሉት፤ ‹‹በውኑ ከሞተው ከአባታችን አብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማን ታደርጋለህ?›› (ዮሐ. ፰፥፶፫-፶፱)…
‹‹መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ፤ ለሞት ግን አሳልፎ አልሰጠኝም›› (መዝ. ፻፲፯፥፲፰)
/in ስብከት /by Mahibere Kidusanተግሣጽ የሚለው ቃል እንደየገባበት ዐውድ እና እንደየተነገረበት ዓላማ የተለያየ ፍቺ ቢኖረውም በመዝገበ ቃላት ደረጃ ቤተ ክርስቲያናችን ካፈራቻቸው ሊቃውንት አንዱ የሆኑት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ በተሰኘ መጽሐፋቸው (ገጽ ፫፻፳፯) ‹‹ተግሣጽ›› ማለት ትምህርት፣ ብርቱ ምክር፣ ምዕዳን፣ ኀይለ ቃል፤ እና ቁጣ ብለው ተርጉመውት ይገኛል፡፡
ዘመነ ስብከት
/in ስብከት, አጽዋማት /by Mahibere Kidusanበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዘመን አከፋፈል መሰረት ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፊት ከታኅሣሥ ፯ ጀምሮ እስከ ፳፱ ያለው ወቅት ዘመነ ስብከት ይባላል፡፡ እያንዳንዱ ሳምንታትም ስብከት፣ ብርሃን እና ኖላዊ በሚል ስያሜ ይታወቃሉ፡፡ በዚህም ወቅት ስለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር መምጣት መወለድ ነቢያት የተናገሩት ትንቢት በስፋት ይነገርበታል፡፡