• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)

ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡…ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡

የማያልቀው ሀብት

ነጭ አይሉት ጥቁር፣ አመዳማም አይደል ቀለሙ ይለያል፡፡ብዙዎች ስለ መልኩ መናገር ያዳግታቸውና ዝምታን ይመርጣሉ፤አያሌዎች ደግሞ በተፈጥሮው ተማርከው ውበቱን ያደንቃሉ፤ መግለጽ ግን ያቅታቸዋል፡፡

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የክረምትን ወቅት እንዴት እያሳላፋችሁ ነው? በአቅራቢያችሁ ወዳለው ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መንፈሳዊ ትምህርት እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን፤ ምክንያቱም ትምህርት ተዘጋ ብለን ጊዜውን በጨዋታ ብቻ ልናሳልፈው አይገባም፡፡ ለመጪው የትምህርት ዘመን አዲስ ለምትገቡበት ክፍል ቅድመ ዝግጅት በማድረግ (መጻሕፍትን በማንበብ) ጊዜውን ልትጠቀሙበት ያስፈልጋል፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! የክረምት ወቅት ከበድ ያለ ዝናም የሚዘንብበት ወቅት በመሆኑ በእያንዳንዱ ነገር ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ! መልካም! ከዚህ ቀደም በተከታታይ መሠረታዊ የሆነ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሥነ ፍጥረት፣ አምስቱ አዕማደ ምሥጢራትን ስንማማር ቆይተናል፤ አሁን ደግሞ ስለ ሰባቱ ምሥጢራት እንማራለን!

የስሜት ሕዋሳቶቻችንና ክርስትና

ሰው በልዩ ልዩ ሁኔታዎች ውስጥ ሲገኝ የሚሰማውን ስሜት በስሜት ሕዋሳቱ አማካኝነት ይገልጣቸዋል፡፡ ደስታ፣ ቁጣ፣ ፍርሃት፣ ሕመም፣ ፍቅር እና የመሳሰሉት ስሜቶቻችን ናቸው፡፡ ሰው እነዚህን ስሜቶቹን በስሜት ሕዋሳቱ በዐይኑ፣ በእጁ፣ በእግሩ፣ በአንደበቱ፣ በፊት ገጽታውና በሰውነት እንቅስቃሴው ይገልጣል፡፡ እነዚህ ስሜቶች ከሚቀሰቀሱበት ሁነቶች፣ ድርጊቶችና ክስተቶች አንጻር በፍጥነት ምላሽ ሳይሰጥ ነገሮችን በዕርጋታ የሚመረምር ሰው በሳል ወይም ባለ አእምሮ ይባላል፡፡ በተቃራኒው ለጉዳዮች ፈጣን ምላሽ የሚሰጠውን ደግሞ ስሜታዊ እንለዋለን፡፡ ባለ አእምሮ ሰው በመረጋጋቱ ብዙ ሲያተርፍ ስሜታዊ ሰው ግን የሚያጸጽቱና ግላዊ፣ ማኅበራዊ እንዲሁም ሀገራዊ ጥፋቶችን የሚያስከትሉ ዋጋዎችን ይከፍላል፡፡ በመሆኑም መጽሐፍ “እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ” በማለት ያስተምረናል፡፡ (፩ኛጴጥ.፬፥፯-፰)

የቀና ልብ

ድሮ ድሮ ልቡ ሲቀና ሕሊናውን መግዛት ተስኖት፣ አእምሮውን ወጥሮ ሲይዘው፣ ሐሳቡን መሰብሰብና አቅንቶ ማየት ያቅትውና ይጨነቅ ነበር፤ ቀጥተኛውን መንገድ  ጠማማ፣ ከፍተኛውን ኮረብታ ዝቅተኛ፣ አባጣ ጎርባጣውን ምቹ አድርጎ ሲመለከት ለመልካም ነገር መወሰን ይሳነዋል፤ ፍቅር ግን ይህን ሁሉ ቀየረለት፤ በትዕቢት የታወረውን ዓይኑን አብርቶ፣ ትምክህቱንና ጭንቀቱን አጥፍቶ የውስጥ ዕረፍት ሰጥቶታልና፡፡

በዓለ ቅድስት ሥላሴ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? አሜን! የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን! በዓለ ቅድስት ሥላሴን በተመለከተ አጭር ጽሑፍ አቅርበንላችኋል፤

ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አባቶቻችን ሐዋርያትን ሰማዕትነት በተቀበሉበት ቀናት በዓላት ሰይማ ታከብራቸዋለች፡፡ እንዲሁም በስማቸው የተሰየመውን ጾም በመጾም አሠረ ፍኖታቸውን ይከተሉ ዘንድ ምእመናንን ታሳስባለች፡፡ በሐምሌ ፭ ቀን ደግሞ የደጋጎቹን ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስን በዓል ታደርጋለች፡፡ የእነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን በዓል መደረጉ በአንድ ቀን ሰማዕትነት በመቀበላቸው ነው፡፡

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ነገን ዛሬ እንሥራ በሚል ርእስ ጀምረን በርካታ ጉዳዮችን የዳሰስንበትን ጽሑፍ በክፍል ከፋፍለን ስናስነብባችሁ ቆይተናል፡፡ ነገን ዛሬ ለመሥራት፣ የነገዋን ቤተ ክርስቲያን የተሻለች ለማድረግ፣ ወደ ቀደመ ክብሯ፣ መታፈሯና መከበሯ ለመመለስ ይቻል ዘንድ ክብረ ምንኩስናን ማጠናከር፣ ገዳማዊ ሥርዓትን መጠበቅ፣ አሁን የሚታዩ ተግዳሮቶችን ማስወገድ የዚህ ትውልድ ግዴታ መሆኑን አንሥተን ክብረ ምንኩስና ነገ የተሻለ እንዲሆን ከቤተ ክርስቲያን የሚጠበቁ እና ከመነኮሳት የሚጠበቁ ጉዳዮችን በክፍል ዘጠኝ አስነብበናችኋል፡፡ ክፍል ዐሥርን (የመጨረሻውን ክፍል) ይዘን ቀርበናል፡፡ መልካም ንባብ!

ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በተለምዶ የሰኔ ጾም እየተባለ የሚታወቀው ጾመ ሐዋርያት ሰኔ ፲፯ (ዐሥራ ሰባት) ቀን ተጀምሮ እስከዚህ ዕለት ደርሷል፡፡ ይህ ጾም ከሰባቱ የዐዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ አገልግሎታቸውን በጸሎትና በጾም ጀምረዋል፤ እኛም እነርሱን አብነት አድርገን በዓለ ጰራቅሊጦስ ከተከበረበት ማግሥት አንሥቶ እስከ ሐምሌ አራት ቀን ድረስ እንጾመዋን፡፡ከዚያም በኋላ ሐምሌ አምስት ቀን የጾሙ ፍቺ ይሆናል፡፡ በዚህም ቀን የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስ የዕረፍት በዓል ነው፡፡

መልካም ልጆች! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! ባለፈው ምሥጢረ ቁርባንን ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ የምሥጢረ ትንሣኤ ሙታንን ትምህርት እንማራለን፡፡ ተከታተሉን!

በእሾህ መካከል የበቀለች ጽጌሬዳ

የውበት ልኬት በእርሷ እንደሆነ እስኪሰማኝ ድረስ ማረከችኝ፡፡ የምድር ጌጥ በመሆኗም ብዙዎች ተደነቁባት፤ ውበቷን በቃላት መግለጽ እስኪያቅታቸው ድረስ ተገረሙባት፡፡ ተፈጥሮዋና ውስጠቷ ዕፁብ የሆነው ጽጌሬዳ በማይነገረው ድንቅ ፍጥረቷ የተማረኩ ብዙኃኑ ሊቀርቧት፣ሊነኳት ወይም ሊያበላሿት አልያም ሊቀጥፏት ይከጅላሉ፡፡…

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ