አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል

 መስከረም 20 ቀን 2007 ዓ.ም. 

በእግዚአብሔርና በሰው ልጆች መካከል የነበረውን የጥል ግድግዳ ያፈርስ ዘንድ ከአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በኋላ ከሦስቱ አካል አንዱ አካል አምላካችን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ፤ እንደ ሕፃናት ቀስ በቀስ አድጎ፤ ወንጌልን ለዓለም ሰብኮ፤ ለሰው ልጆች ቤዛ ይሆን ዘንድ፤ በሞቱ ሞትን ይሽር ዘንድ፤ በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በትንሣኤውም ለሰው ልጆች ትንሣኤን አወጀ፡፡ በእግዚአብሔርና በሰው ልጆች መካከል የነበረውንም የጥል ግድግዳ አፈረሰ፡፡ የሰው ልጆች ያጣነውን የእግዚአብሔር ልጅነትንም አገኘን፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ “ወወሀብኮሙ ትዕምርተ ለእለ ይፈርኁከ ከመ ያመስጡ እምገጸ ቅስት ወይድኅኑ ፍቁራኒከ” ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው መዝ.49፡4 እንዲል፡፡ “ጠላቶቻችንን በአንተ ድል አናደርጋቸዋለን” በማለት የመስቀልን ክብርና አሸናፊነት አብስሯል፡፡መዝ. 43፡5፡፡

“እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኀኒተ በማዕከለ ምድር” እግዚአብሔር ዓለም ከመፈጠሩም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፤ በምድርም መካከል መድኀኒትን አደረገ፡፡ መዝ. 73፡16 በማለት ቅዱስ ዳዊት እንደተቀኘው እግዚአብሔር የሰውን ልጆች ለማዳን የቃልኪዳን ቦታዎችን በዚህች ምድር ላይ አዘጋጅቷል፡፡ በዓለም ላይ ቃል ኪዳን ከተሰጣቸው ቅዱሳት መካናት መካከል አብዛኛዎቹ በኢትዮጵያ ሀገራችን ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል በግምባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም አንዷ ናት፡፡ አባቶቻችን “ግሸን ደብረ ከርቤ መካነ መስቀሉ ለክርስቶስ እንተ ይእቲ ኢየሩሳሌም” የክርስቶስ መስቀል መንበር የሆነችው ግሸን ደብረ ከርቤ ናት ይህችውም ኢየሩሳሌም ናት በማለት ግሸን ደብረ ከርቤ ከኢየሩሳሌም ጋር እኩል መሆኗን መስክረውላታል፡፡

የጌታን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ መስቀል በቅድስት እሌኒ በ325 ዓ.ም. ከተቀበረበት ከወጣና በክብር ለረጅም ዓመታት በኢየሩሳሌም ከተቀመጠ በኋላ ዐረቦች ኢየሩሳሌምን በመውረራቸው ምክንያት በአረማውያን እጅ እየተማረከ ከአንዱ ሀገር ወደ አንዱ ሀገር ሲንከራተት ቆይቷል፡፡ በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖችም በመስቀሉ መማረክ ያዝኑና ይበሳጩ ስለነበር ጦራቸውን አሰልፈው መስቀሉ ወደሔደበት ሀገር በመዝመት ጦርነት ያካሔዱ ነበር፡፡

በ778 ዓ.ም. አራቱ አኅጉራት ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ በአራቱ የመስቀሉ ክንፍ የተያያዙት ምልክቶችን በማንሳት የተከፋፈሉ ሲሆን በወቅቱ በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩ ዐረቦች በእስክንድርያ ለሚኖሩ አባቶች የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግሮቹ እና እጆቹ ተቸንክረው የተሰቀለበትን ሙሉ መስቀል ላኩላቸው፡፡ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስም በክብርና በጥንቃቄ እንዲቀመጥ አድርጓል፡፡

የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር መስቀሉ ለብዙ ዘመናት በግብፅ እስክንድርያ ከቆየ በኋላ የግብፅ እስላሞች ቁጥራቸው በመበራከቱ በክርስቲያኖች ላይ የመከራ ቀንበር ስላጸኑባቸው ከዚህ ስቃይ ይታደጓቸው ዘንድ ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዐፄ ዳዊት “ንጉሥ ሆይ በዚህ በግብፅ ያሉ እስላሞች መከራ አጽንተውብናልና ኃይልህን አንስተህ አስታግስልን” ብለው ይልካሉ፡፡ አንዳንድ መጻሕፍት ደግሞ የግብፅ ንጉሥ አቡነ ሚካኤልንና አቡነ ገብርኤልን በማሰሩ ምክንያት ከዚህ አስከፊ ችግር እንዲታደጓቸው ክርስቲያኖች መልእክት እንደላኩባቸው ይገለጻል፡፡ መልእክቱ የደረሳቸው ፄ ዳዊትም ስለ ሃይማኖታቸው በመቅናት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሠራዊት አሰልፈው ወደ ግብፅ ይዘምታሉ፡፡ በክርስቲያኖችና በሙስሊሞች መካከልም እርቅ እንዲወርድ ተደረገ፡፡

የግብፅ ክርስቲያኖችም ዐፄ ዳዊት ስላደረጉላቸው መልካም ነገር እጅ መንሻ ይሆናቸው ዘንድ ብዛት ያለው ወርቅና ብር ያቀርባሉ፡፡ ዐፄ ዳዊት ግን ፍላጎታቸው ወርቅና ብሩን መውሰድ ሳይሆን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል እንዲሰጧቸው ይጠይቃሉ፡፡ በጥያቄያቸውም መሠረት ተሰጣቸው፡፡ “መስቀልየ ይነብር በዲበ መስቀል” የሚል ራዕይ አይተው ስለነበር ጉዟቸውን በሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ ያደርጋሉ፡፡ በመንገድም እያሉ ያርፋሉ፡፡ ዐፄ ዳዊት መስከረም 10 ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል ከግብፃውያን የተቀበሉበት ቀን በመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን ተቀጸል ጽጌ በመባል የሚታወቅ ሲሆን በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡

ከዐፄ ዳዊት በኋላ በቦታቸው የተተኩት ዐፄ ዘርዐያዕቆብ “አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል” የሚል ራዕይ በማየታቸው መስቀሉን በ1443 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት በተለያዩ ቦታዎች ለማሳረፍ ጥረት አድርገዋል፡፡ በደብረ ብርሃን፤ በሸዋ ደርሄ ማርያም፤ በጨጨሆ፤ በአንኮበር፤ በመናገሻ አምባ፤ በእንጦጦ፤ ወዘተ አሳርፈውት አልተሳካላቸውም፡፡ በመጨረሻም መስከረም 21 ቀን 1446 ዓ.ም. በራዕይ በተነገራቸው ቅዱስ ስፍራ በግሸን ደብረ ከርቤ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አኑረውታል፡፡

የተራራው ተፈጥሯዊ አቀማጥ ሲመለከቱት አንድ ጥሩ አናፂ ከጥሩ እንጨት ባማረ ጌጥ ጠርቦ የሰራው ግሩም የእጅ መስቀል ይመስላል፡፡ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም መሠረቱ የተጣለውና ቤተ ክርስቲያን ሊታነጽ የበቃው በ514 ዓ.ም. በዐፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት አባ ፈቃደ ክርስቶስ በሚባሉ አባት ነው፡፡ አባ ፈቀደ ክርስቶስ የዐፄ ካሌብ የንስሐ አባት ሲሆኑ በየመን ሀገረ ናግራን ላይ የነበሩ የእግዚአብሔር አብና የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሁለት ጽላቶችን ወደ ኢትዮጵያ ይዘው በመምጣት በግሸን ደብረ ከርቤ ተራራ ላይ በማኖር ሲቀደስባቸውና ስብሐተ እግዚአብሔር ሲደረስባቸው ቆይተዋል፡፡ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም የአሁኑን ስም ከማግኘቷ በፊት በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ስሞች ስትጠራ የቆየች ሲሆን ደብረ ነጎድጓድ፤ ደብረ እግዚአብሔር፤ ደብረ ነገሥት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አባቶችና መጻሕፍት ለአፍሪካ የደረሰው የመስቀሉ ቀኝ ክንፍ ብቻ ነው ሲሉ፤ የግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም አበው ሊቃውንት ግን አጥብቀው እንደሚቃወሙት መጻሕፍት ያረጋግጣሉ፡፡ መስቀሉ ለአራቱ ክፍለ ዓለማት ሲከፋፈል መስቀሉ ላይ ተለጥፈው የነበሩት ምልክቶች በማንሳት ለሦስቱ ክፍለ ዓለማት እንደተሰጠና ለአፍሪካ ግን ሙሉ መስቀል እንደደረሰ ይመሰክራሉ፡፡ ዛሬም በኢትዮጵያ ውስጥ በግሸን ደብረ ከርቤ በእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው መስቀል የቀኝ እጁ በኩል ብቻ ሳይሆን ሙሉው የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያያናችንም ይህንን መሠረት በማድረግ መስከረም 21 ቀን በየዓመቱ በግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም በድምቀት ታከብራለች፡፡

  • ምንጭ፡- አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል 1990 ዓ.ም.

ግሸን ደብረ ከርቤ የቃል ኪዳን አምባ ቀሲስ በላይ ተገኝ 1996 ዓ.ም.

ቅዱሳት መካናት በኢትዮጵያ ዘመድኩን በቀለ 1992 ዓ.ም.

 

meskel damera

ወሰአረ መርገመ በዲበ ዕፀ መስቀል

መስከረም 16 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ምስጢረ ሥላሴ ማናየ

 

  • መርገምን በመስቀል ላይ ሻረ” ቅዱስ አትናቴዎስ ሃይማኖተ አበው

በቅmeskel dameraድሚያ ከዘመን ወደ ዘመን ያሸጋገረን ለብርሃነ መስቀሉ ያደረሰን በሀብቱ የሳበን በረድኤቱም ያቀረበን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፡፡

ከላይ በርዕሱ ያነሣነው ኃይለ ቃል ቅዱስ አትናቴዎስ የመስቀሉን ነገር በተናገረበት ድርሳኑ የተናገረው ነው፡፡ አስተሀፈረ ኃጢአተ በዲበ ምድር ወሰአረ መርገመ በዲበ ዕፀ መስቀል ወአብጠለ ሞተ በውስተ ሲዖል ወነሰተ ሙስና እምውስተ መቃብር”

“በምድር ላይ ኃጢአትን አሳፈረ መርገምን በመስቀል ላይ ሻረ ሞተ ነፍስን በሲዖል አጠፋ ፈርሶ በስብሶ መቅረትን በመቃብር አፈራረሰ” በማለት ጌታችን ለሰው ልጆች ነጻነት እና ድኅነት የከፈለውን የቤዛነት ሥራ በተናገረበት ክፍል የተናገረው ነው የሰው ልጆች ነጻነታቸው የተዋጀው በመስቀል ተሰቅሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በሥልጣኑ ለይቶ ዲያብሎስን በመስቀሉ ገሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲዖል ወርዶ ነፍሳትን ከዲያብሎስ ባርነት ከአጋንንት ቁራኝነት ከሲዖል ግዛት ነጻ አውጥቷቸዋልና፡፡

“ሞተ በሥጋ ወሐይወ በመንፈስ ወወረደ ኀበ እለ ሙቅሕታ ትነብር ነፍሶሙ ወሰበከ ሎሙ ግዕዛነ” በሥጋ ሞተ በመንፈስ /በመለኮት/ ግን ሕያው ነው እርሱም ደግሞ ሄደ በወህኒ /በሲዖል/ ለነበሩ ነፍሳት ነጻነትን ሰበከላቸው” 1ጴጥ.3፡18

መስቀል በዓለመ መላእክት
መስቀል በዓለመ መላእክት በጥንተ ፍጥበረት ሰባቱ ሰማያት በተፈጠሩበት ዕለተ እሑድ ሥላሴ ጽርሐ ዓርያምን ከእሳት ዋዕዩን ትቶ ብርሃኑን ነሥቶ በፈጠረበት ጊዜ በውስጧ ታቦት ዘዶርንና የብርሃን መስቀልን ቀረፀባት ይላል ሊቁ ኤጲፋንዮስ ሥነ ፍጥረትን አምልቶ አጉልቶ በጻፈበት አክሲማሮስ በተባለ መጽሐፉ ይህ በእንዲህ እንዳለ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጥሮ በተሰወራቸው ጊዜ ዲያብሎስ እኔ ፈጠርኳቸው ባለበት ሰዓት በአለመ መላእክት በመላእክትና በዲያብሎስ በተደረገው ጦርነት መላእክት ዲያብሎስን ድል ያደረጉት በመስቀል መሣሪያነት ነው፡፡

“በሰማይ ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን /ዲያብሎስን/ ተዋጉት ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም ከዚያም ወዲያ በሰማይ ቦታ አልተገኘለትም ዓለሙን የሚያስተው ሁሉ ምድር ተጣለ መላእክቱም /ሠራዊተ ዲያብሎስ/ ከእርሱ ጋር ተጣሉ” ራዕ.12፡7፡፡

በዚህ ውጊያ መካከል የነበረውን ሁኔታ ሲገልፅ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ዲያብሎስ ሁለት ጊዜ ዲያብሎስ ድል ነሳቸው በሦስተኛው ፈጣሪያቸውን ጠየቁ ፈቃድህ አይደለምን ዲያብሎስን እንድንዋጋው አሉት፤ መላእክት ፈቃዴስ ነው ግን ድል የምታደርጉበትን ኃይል እንድታውቁ ብዬ ነው ብሎ በክንፋቸው ላይ የብርሃን መስቀል ቀረጸላቸው በእጃቸው የብርሃን መስቀል አስያዛቸው ሄደው ገጠሙት “ጐየ እግዚእ ምስለ ዓርያሙ” ጌታ ሰማይን ጠቅልሎ ሸሸ ብሎ እየደነፋ ወደ ምድር ወረደ ይላል፡፡ ስለዚህ መስቀል ፀረ ዲያብሎስነቱ የታወቀው ጌታችን ከመሰቀሉ በፊት ነው፡፡ ኃይሉም የተገለጠው ያን ጊዜ ነው፡፡

በሌላ መልኩ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ የመላእክትን ምስጋና በገለጠበት እንዲህ ሲል ጽፏል “ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን ከፍ ባለ ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ አየሁት ኪሩቤልና ሱራፌል ዙሪያውን ነበሩ ለእያንዳንዱም ስድስት ስድስት ክንፍ ነበራቸው በሁለት ክንፋቸው ፊታቸውን ይጋርዳሉ በሁለት ክንፋቸው እግራቸውን ይጋርዳሉ በሁለት ክንፋቸው ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይበራሉ፡፡ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ እያሉ ያመሰግናሉ” ኢሳ.6፡1-6፡፡

ሲበሩ ክንፋቸውን መዘርጋታቸው የመስቀል ምልክት ከመሆኑም በተጨማሪ አምላክ ሰው ሆኖ በመስቀል ተሰቅሎ ዓለምን እንደሚያድነው ምልክት ነበር፡፡
ይህን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ “በአርአያ ትዕምርተ መስቀል” በመስቀል ተሰቅለህ ዓለምን ታድናለህ ሲሉ ነው ብሎ ተርጉሞታል፡፡

መስቀል በዘመነ አበው
በዘመነ አበው መስቀል የመባረኪያ ምልክት እንደነበረ የሚያሳዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉ ለምሳሌ፡-
“በተአምኖ አመይመውት ያዕቆብ ባረኮሙ ለደቂቀ ዮሴፍ ለእለ አሐዱ” ያዕቆብ በሚሞትበት ጊዜ የዮሴፍን ልጆች በእምነት ባረካቸው” ዘፍ.47፡31፣ ዕብ.11፡22 “ወአስተሐለፈ እዴሁ ላዕለ ርዕሰ ኤፍሬም ወምናሴ” እጆቹን በኤፍሬምና በምሴ ላይ በመስቀል አምሳል አመሳቀለ እጆቹንም በራሳቸው ላይ ጭኖ ባረካቸው ይላል፡፡ 

ዛሬም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህኑ ቀድሶ በሚወጣበት ጊዜ በእጆቹ ይባርካል ይህም የሚያሳየው ቤተ ክርስቲያኗ መሠረቷ ከላይ በዓለመ መላእክት ከታች በዘመነ አበው ያየነው መስቀል መሆኑን ነው፡፡ “በአምስት ቀን ተኩል ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በመስቀል ተሰቅዬ ሞቼ አድንሃለሁ” የሚል የተስፋ ቃል ተሰጥቷል፡፡

መስቀል በዘመነ ነቢያት እና በዘመነ ነገሥት
መስቀል በዘመነ ነቢያት በዘመነ ነገሥት እንደየሀገሩ ግእዝን /ሁኔታ/ ልዩ ልዩ ተግባራት ሲፈጽሙበት ቆይቷል፡፡ ለምሳሌ፡- ለወንጀለኞች መቅጫነት አገልግሏል በዕርግጥ አሁንም የወንጀለኞች የአጋንንት መቅጫ ነው ለሚያምኑበት ግን የጭንቅ መውጫ የነጻነት መገለጫ ነው፡፡

በተለይ ፋርስ ሰዎችን ሰቅሎ መግደል መገለጫዋ ነበር የተጀመረውም በፋርስ ነው ሰውን በመስቀል ሰቅሎ መግደል የባቢሎን እቶነ እሳት እና አናብስት፣ የሮማውሪያንና የፋርስ ስቅለት የአይሁድ ውግረት  መቅጫቸው ነው፡፡

መርዶክዮስን ሊሰቅል ባዘጋጀው መስቀል የተሰቀለው ሐማ በፋርስ ሕግ ነበር “እነሆ ሐማ ለንጉሡ በጎ ለተናገረው ለመርዶክዮስ ያዘጋጀው አምሳ ክንድ የሆነ ግንድ በሐማ ቤት ተተክሎአል “ንጉሡም በእርሱ ላይ ስቀሉት አለ ሐማንም ለመርደክዮስ ባዘጋጀው ግንድ ላይ ሰቀሉት” አስቴ.7፡9፡፡

በእርግጥም ይህን አልን እንጂ ይህ ሥርዓት ከፋርስ ወደሮማውያን ተላልፎ በመቅጫነት አገልግሎአል፡፡ አይሁድም ብዙ ጊዜ ወንጀለኞችን የሚቀጡት በውግረት በእሳት በማቃጠል ቢሆንም በመስቀልም ይቀጡ ነበር፤ ምክንያቱም መነሻው ኦሪት ነውና የኦሪት መደበኞች ደግሞ ፋርሶች ወይ ሮማውያን ሳይሆኑ እነርሱ ናቸው፡፡

“ርጉም ውእቱ ኩሉ ዘስቁል ዲበ ዕፅ” ዘዳ.21፡23 ሰርቆ ቀምቶ በእንጨት የተሰቀለ የተረገመ ይሁን” ተብሎ የተጻፈው በኦሪት ነው፡፡ ስለዚህ መስቀል የወንበዴ የሌባ መቅጫ የጥፋተኛ መቀጥቀጫ ነበር፡፡ በአይሁድ ሕግ ከፍተኛ ወንጀል የፈጸሙ ሰዎች አይገረፉም በመስቀል ይቀጡ ነበር፡፡ ከተገረፉ ደግሞ አይሰቀሉም፤ የፈጸሙት በደል ለዚያ ርግማን የሚያበቃ አይደለም፡፡ ማለት ነው፡፡

መስቀል በዘመነ ነቢያት በብዙ ኅብረ ትንቢት አሸብርቆ በብዙ ኅብረ አምሳል ደምቆ የመጣ እንጂ፤ እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተገኘ አይደለም፡፡ ለእስራኤል በ40 ዘመን ጉዟአቸው ውስጥ ተአምራት በማረግ የታዩት የሙሴ በትር እና በምድረ በዳ ሙሴ የሰቀለው አርዌ ብርት የታየበት አላማ የመስቀል ምልክቶች ወይም ምሳሌዎች ነበሩ፡፡

የሙሴ በትር ባሕር ከፍሏል ጠላት ገሏል መና አውርዷል ደመና ጋርዷል ውኃ ከአለት አፍልቋል፤ በግብጻውያን ላይ ድንቅ ድንቅ ተአምራት አድርጓል፡፡ ሙሴም ምሳሌው የሆነለት ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀልም ባሕረ እሳትን ከፍሏል ማየ ገቦን ደመ ገቦን ለመጠጣችን ለጥምቀታችን አስገኝቷል፡፡ ኃይሉን በዲያብሎስና በአጋንንት ላይ አሳይቷል፡፡ ነፍሳትን ከሲዖል ባርነት ከዲያብሎስ ቁራኝነት ነጻ አውጥቷል፡፡ “ወሀደፎሙ በመስቀሉ” በመስቀሉ አሻገራቸው” እንዲል መጽፈሐፈ ኪዳን፡፡ ሙሴ በምድረ በዳ የሰቀለው የነሐስ እባብ ክርስቶስ በመሰቀል የሚፈጽመውን የማዳን ሥራ የሚያሳይ ነበር፡፡

“ሙሴም ስለ ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ እግዚአብሔርም ሙሴን “የናስ እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል እባቡም ሰውን ቢነድፍ የተነደፈው ሁሉ ይመልከተው ይድናልም” ሙሴም የናሱን እባብ ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ እባቡም የነደፊችው ሁሉ የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ” ዘኁ.21፡7፡፡

የነሐሱ እባብ የክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ የነሐሱ አባብ ጽሩይ ነው ክርስቶስም ጽሩየ ባሕርይ ነውና የነሐሱ እባብ መርዝ የለበትም ክርስቶስም መርገመ ሥነጋ መርገመ ነፍበስን የሚያርቅ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን የሚያድል ክፋት ተንኮል የሌለበት ነውና እባቡ የተሰቀለበት ዓላማው ደግሞ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀልምሳሌ ነበር፡፡

እባብ የነደፈው ሁሉ በተመለከተው ጊዜ ይድን እንደነበር የሰው ልጅ በሙሉ በእባብ ዲያብሎስ መርዝ ተነድፎ ቆስሎ በኃጢአት ተመርዞ ሲኖር በመስቀል በተፈጸመው የቤዛነት ሥራ ድኗልና፡፡
“ወበከመ ሙሴ ሰቀሎ ለአርዌ ምድር በገዳም ከማሁ ሀለዎ ለወልደ እጓለመሕያው ይሰቀል ከመ ኩሉ ዘየአምን ቦቱ ኢይትሐጐል አላ የሐዩ ለዓለም”

ሙሴ እባብን በምድረ በዳ እንደሰቀለው እንዲሁ የሰው ልጅ ይሰቀል ዘንድ ይገባዋል የአመነበት ሁሉ ለዘለዓለም ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ዘንድ ይገባዋል” ዮሐ.3፡15፡፡

ከነቢያት ዳዊት እንዲሁም ልጁ ሰሎሞን የመስቀሉን ነገር አምልተው አጉልተው ተናግረዋል፡፡ “ወወሀብኮሙ ትዕምርተ ለእለይፈርሁከ ከመ ያምስጡ እምገፀ ቅሥት”  “ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው ወዳጆችህ እንዲድኑ” መዝ.59፡4 ለመዳን የተሰጠ ምልክት ደግሞ መስቀል ነው ለዚህ ነው እኛ ኦርቶዶክሳውያን በአንገታችን የምናስረው በእጃችን የምንይዘው የምንሳለመው የምንባረክበት ምክንያቱም የመዳን ምልክት ነውና፡፡

ጥበበኛው ሰሎሞንም የመስቀሉን ነገር በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ይላል “ሐረገ ወይን ኮነ መድኃኒትየ ዘእምሐሲሦን ይትገዘም ወበጎልጎታ ይተከል” “የወይን ሐረግ /መስቀል/ መድኃኒቴ ሆነ ሐሲሦን ከተባለ ቦታ ይቆረጣል በጎልጎታ ይተከላል” መኃ.3፡44 ግዕዙን ተመልከት፡፡

ዳዊት ለመዳን የተሰጠ መሆኑን ሲገልጽ ልጁ እንጨቱ ከየት ተነቅሎ በየት ቦታ እንደሚተከል እና መድኃኒትነቱን አጉልቶታል ስለዚህ መስቀል በብሉይ ኪዳን ትልቅ ቦታ ይዟል ማለት ነው፡፡
መስቀል በሐዲስ ኪዳን

መስቀል ከብሉይ ኪዳን ይልቅ የመዳን ምልክት መሆኑ የተረጋገጠበት በክርስቶስ ደም የተቀደሰ የጠብ ግድግዳን ያፈረሰ ቅድስና ያለው ክብር ያለው የአበው ተስፋ የተፈጸመበትም ሰው ከውድቀቱ የተነሳበት መሆኑ ተረጋጋጧል፡፡

ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስተምሩን ጌታችን የተሰቀለበት መስቀል የተዘጋጀው ከሰባት ዓይነት ዕፅዋት ነው፡፡
1.    ሳኦል ከገነት ያስመጣው ዕፅ
2.    ሰሎሞን ቤተ መቅደስን በሠራበት ወቅት ሠረገላ አድርጎ የተጠቀመበት ዕፅ
3.    ከመቃብረ አዳም የበቀለ ፅፀ ሕይወት
4.    ሎጥ በእንባው ያለመለመው ፅፀ ከርካዕ
5.    ታቦተ ጽዮንን ይሸከሙበት የነበረው ሠረገላ
6.    ጌታችን በቢታንያ የረገማት ዕፀ በለስ
7.    ዘኬዎስ ጌታችንን ለማየት የወጣበት ዕፀ ሠግለ /ሾላ/ ከእነዚህ ሰባት ዕፅዋት በተዘጋጀ መስቀል ነው ጌታችን የተሰቀለው /መጽሐፈ ኪዳን ትርጓሜ ተመልከት/ 

ጌታችን ከእነዚህ ዕፅዋት የተዘጋጀ መስቀሉን ተሸክሞ በቀራንዮ አደባባይ በመስቀሉ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ ቀድሶታል በዚህ የተነሣ መስቀል ነዋይ ቅዱስ ነው መስቀል በሐዲስ ኪዳን ሁለት መሠረታዊ ትርጉሞች አሉት፡፡
1.    ጌታችን የተሰቀለበት ከሰባት ዕፅዋት የተዘጋጀውን መስቀለኛ እንጨት /ቅዱስ መስቀል/
2.    ጌታችን ዓለምን ለማዳን የተቀበለው መከራ መስቀል ይባላል መስቀል ስንል እነዚህን ከላይ ያነሳናቸውን ሁለት አበይት ትርጉሞች ማስታወስ የግድ ይላል፡፡

ስለ መስቀል የክርስቶስ ትምህርት
ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ደጋግሞ ነገረ መስቀልን አስተምሯል፡፡ “ዘኢጻረ መስቀለ ሞትየ ኢይክል ይጸመደኒ” መስቀሉን የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ የእኔ ሊሆን አይገባውም” ማቴ.10፡38፣ 16፡24፣ ማር.8፡34፣ ሉቃ.9፡23፣ 14፡27፡፡

ጌታችን ይህንን ያስተማረው ከመሰቀሉ በፊት መሆኑ ግልፅ ነው በቃል ካስተማረው በኋላ በተግባር ፈጸመው መስቀሉን እንድንሸከም መከራውን እንድንቀበል አስቀድሞ አስጠነቀቀን መስቀሉ የሌለው የክርስቶስ ሊሆን እንደማይችል አስረግጦ ነገረን፡፡

ከዚህ የተነሣ ክርስቶስ ራሷ የሆነላት ሐዋርየዊት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መስቀሉን በየዓመቱ በየወሩ ታከብረዋለች ትሸከመዋለች፡፡ በመስቀሉ የሚገኘውን መከራ ትቀበላለች በመስቀሉ የሚገኘውን በረከት ታድላለች ክርስቶስን በግብር ትመሰለዋለች በእግር ትከተለዋለች የእርሱ መሆኗ መልክት መስቀሉ ነው፡፡

“በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ “እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ” ማቴ.16፡24፡፡ “የሰው ልጅ /ክርስቶስ/ ለካህናት አለቆችና ለጻፎች አልፎ ይሰጣል የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል ሊዘባበቱበትም ሊገርፉትም ሊሰቅሉትም ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታል” ማቴ.20፡18፡፡ መስቀል ስንል ይህን ሁሉ መከራ ያጠቃልላል ይህ ሁሉ መከራ የተፈጸመበት ነዋይ ቅዱስም መስቀል ይባላል፡፡

“ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁ የሰው ልጅ ሊሰቀል አልፎ ይሰጣል” ማቴ.26፡1፡፡ ይህ እስከ አሁን ጌታችን በቃል ያስተማረውን ተመልክተናል ተግባሩ እነሆ፡-“የአይሁድ ንጉሥ ሰላም ላንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት ተፉበትም መቃውን ይዘው ራሱን መቱት ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉት ወሰዱት ሲወስዲትም ስምዖን የተባለ የቀሬና /ሊቢያ/ ሰው አገኙ እርሱንም መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ሥፍራ በደረሱ ጊዜ ሰቀሉት” ማቴ.27፡29፡፡ መስቀል ማለት ይህን ሁሉ ያጠቃልላል፡፡

ሰሎሞን የወይን ሐረግ መድኀኒቴ ሆነ ከሀሲሦን ይቆረጣል በጎልጎታ ይተከላል” ያለው ተፈጸመ መድኃኒት መስቀል መድኃኒት ክርስቶስን ተሸክሞ ታየ መድኃኒት ክርስቶስ የሚሰቀልበትን መስቀል ተሸክሞ ደፋ ቀና ብሎ መከራን ሲቀበል ተመለከትን መስቀሉን እርሱ ብቻ አይደለም ተከትዮቹ እነስምዖን ቀሬናዊም ተሸከሙት የድካሙ ተካፋይ ሆኑ፡፡ ልዩነቱ እነ ስምዖን ተገደው እኛ ግን ወደን ነው፡፡ እነ ስምዖን በአጋጣሚ እኛ ክርስቲያኖች ግን በዓላማ ክርስቶስን እንመስለው ዘንድ መስቀሉን የማይሸከም ለእኔ ሊሆን አይገባውም ብሎ አስተምሮናልና በተግባርም ፈጽሞ አሳይቶናልና፡፡
ከሰቀሉትም በኋላ እንዲህ ዘበቱበት “የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን” ማቴ.27፡40-42

“ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት መስቀሉንም ተሸክሞ በእብራይስጥ ጎልጎታ ወደተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ በዚያም ሰቀሉት” ዮሐ.19፡17፡፡ ራስ ቅል ስፍራ ማለት የአዳም የራስ ቅል የተቀበረበት ቦታ ነው መስቀሉ የተተከለበት ቦታም ይህ ነበር ለአዳምና ለልጅ ልጆቹ የተፈጸመ ካሳ ነውና፡፡

“እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር” እግዚአብሔር ከዓለም በፊት ንጉሥ ነው በምድር መካከል መድኀኒትን አደረገ” መዝ.73፡13፡፡ ይህ መድኃኒት ዓለም የዳነበት ቅዱስ መስቀሉ አይደለምን?

“ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል” የአበው ተስፋ በድንግል ማርያም ተፈጸመ በቀራንዮም መድኃኒት መስቀል ተተከለ” እንዲል ስለሆነም መስቀልን ስናስብ ለእኛ የተከፈለውን የአምላካችንን የቤዛነት ሥራ የተቀበለውን መከራ የተገረፈውን ግርፋት የታሰረበት ሀብል የተሰቀለበትን መስቀል የጠጣውን መራራ ሐሞት እደቹ እና እግሮቹ የተቸነከሩበትን ቅንዋት /ችንካሮች/ ጎኑ የተወጋበትን ጦር የፈሰሰውን ደሙን የተቆረሰ ሥጋውን በጠቅላላው ለእኛ ሲል አምላካችን የተቀበለውን ጸዋትወ መከራ እናስባለን፡፡

ስለ መስቀል የሐዋርያት ትምህርት
ስለ ቅዱስ መስቀል ከክርስቶስ ቀጥሎ ያስተማሩት ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው፡፡ ርዕሰ ሐዋርየት ቅዱስ ጴጥሮስ እንዲህ በማለት ያስተምራል፡፡ “ወበእንተ ኃጣውኢነ ውእቱ ተሰቅለ ዲበ ዕፀ በሥጋሁ ከመያውጽአነ እምኃጣውኢነ” ስለ ኃጢአታችን እርሱ በእንጨት /በመስቀል/ ላይ ተሰቀለ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ” 1ጴጥ.1፡24 በማለት በመስቀሉ ክርስቶስ የከፈለልንን ዋጋ ነገረን፡፡
“ወንገረ መስቀሉሰ እበድ ውእቱ በኃበ ህጉላን ወለነሰ ለእለ ድኅነ ኃይለ እግዚአብሔር ወጥበበ እግዚአብሔር ውእቱ” 1ቆሮ.1፡18፡፡ 

“የመስቀሉ ቃል /ትምህርቱ/ ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚብሔር ኃይል ነው በማለት እግዚአብሔር ኃይሉን የገለጠበት ማዳኑን ያሳየበት ትድግናው የተከናወነበት መሆኑን ያስረዳናል፡፡ ይህን ዓለም አልተቀበለውም አላወቀምና፡፡

“እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” 1ቆሮ.1፡2 ሲል የክርስቶስ መገለጫው መስቀሉ ነው፡፡ ዙፋኑ ነውና ዲያብሎስን የቀጣበት ኃይሉን የሻረበት ነውና ሰው ይህን መቀበል ካልቻለ ሰው መሆኑ ያጠራጥራል፡፡

“እስመ ይቤ መጽሐፍ ርጉም ውእቱ ኩሉ ዘስቁል ዲበ ዕፅ ወለነሰ ተሣሃለነ እመርገማ ለኦሪት” መጽሐፍ በእንጨተ የተሰቀለ ሁሉ ርጉም ይሁን ይላልና እኛን ግን ከኦሪት ርግማን በእንጨት ተሰቅሎ ዋጀን” ገላ.3፡12፡፡

የኦሪትን ርግማን ተቀብሎ በእንጨት መስቀል ተሰቅሎ መርገሙን ወደበረከት ለወጠልን መስቀል የእርግማን ምልክት ሳይሆን የድል፣ የነጻነት፣ የበረከት ምልክት መሆኑን አወጀልን፡፡ እኛም ይህን ተቀብለን መስቀል ኃይላችን ነው መስቀል መድኃኒታችን ነው እንላለን፡፡ በመስቀሉ እንመካለን ጥግ አድርገን ጠላታችንን እንዋጋበታለን፡፡

“በሥጋ መልካም ሆነው ሊታዩ የሚወዱ ሁሉ እንድትገረዙ ግድ አሏችሁ ነገር ግን ስለ ክርስቶስ መስቀል እንዳይሰደዱ ብቻ ነው ገላ.5፡12፡፡ ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት /ከኃጢአት/ የተለየበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት /ከኃጢአት የተለየሁበት/ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ”

እዚህ ላይ ቅዱስ ጳውሎስ ከኃጢአት የተለየበት ከእግዚአብሔር ጋር የታረቀበት መመኪያው መስቀል እንደሆነ ከመሰከረ እኛስ ከእርሱ አንበልጥም እኔን ምሰሉ ብሎናልና” 1ቆሮ.11፡1፡፡ ስለዚህ ነው በመስቀሉ የምንመካው የምናከብረው ኃይላችን ብለን የምንጠራው መስቀሉን መስቀል የሰላም መሠረት ነው ጥልን /ዲያብሎስን/ የገደለ /ድል የነሣ/ ለሰው ሰላም የተደረገበት ነው፡፡

“ሰላምንም ያደርግ ዘንድ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን /ሕዝብና አሕዛብን/ በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው” ኤፌ.2፡16፡፡ “ወገብረ ሰላመ በደመ መስቀሉ ለእለ ውስተ ሰማይ ወእለ ውስተ ምድር ወዘታህቴሃ ለምድር በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ለራሱ /ከራሱ ጋር/ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና ቆላ.1፡20፡፡ ለዚህ ነው መስቀል ሰላም ነው የሰላም ምልክት ነው የምንለው ሰውና መላእክት ሰውና እግዚአብሔር ሕዝብና አሕዛብ ነፍስና ሥጋ የታረቁበት ነውና፡፡

“በትዕዛዛት የተጻፈውን የእዳ ጽሕፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀል ጠርቆ አስወግዶታል ቆላ.2፡14፡፡ እንግዲህ የዕዳ ደብዳቤያችን የተሻረበት እኛ ጸጋና ክብርን የተጎናጸፍንበት የዕርቅ የሰላም የመዳን ምልክት ነው መስቀል፡፡

ስለዚህ ብዙዎች መስቀልን ይወዱታል በአንጻሩም ብዙወች ባለማወቅና በክፋት ይጠሉታል ሊቀብሩት ፈለጉ ለምን? ተአምራት በማድረጉ ድውይ በመፈወሱ ሙት በማስነሣቱ፣ እውር በማብራቱ ባለቤቱን ክርስቶስን እንደጠሉት ሁሉ መስቀሉን የጠሉ አይሁድ መስቀሉን ለ300 ዓመታት ቀበሩት መስቀል ገቢረ ተአምራት የሚያደረግ ተቀብሮ ይቀር ዘንድ የማይቻል ነውና በእሌኒ ንግሥት አማካኝነት ከተቀበረበት ወጣ መስቀል በጎልጎታ ብቻ አይደለም የተቀበረው በክርስቶሳውያን ልቡና ጭምር እንጂ ስለሆነም ቀብሮ ማስቀረት አይቻልም ይልቁንም ቤዛነቱን ኃይሉን ተአምራቱን አምኖ መቀበል ነው፡፡

በጥንታውያን ክርስቲያኖች መስቀል ተቀብሮ ከወጣበት ጊዘ ጀምሮ እሌኒ ንግሥት ቤተ መቅደስ ከሠራችለት ጊዜ ጀምሮ በመስከረም አሥራ ሰባት ቀን አሁን በኢትዮጵያ እንደሚከበረው ይከበር ነበር፡፡ ዛሬ ግን በኢትዮጵያ ብቻ በደማቅ ሁኔታ ሲከበር በሌሎች ታስቦ ይውላል፡፡ ይህም የሚያሳየው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቱያን ታሪክን በመጠበቅ ከሌሎች ይልቅ ምን ያህል ብርቱ እንደሆነች ያሳያል፡፡

ለመስቀሉ ጠላቶች የተሰጠ ተግሳጽ
ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና ብዙ ጊዜ ስለ እርሱ አልኳችሁ አሁንም እንኳ እያለቀስኩ እላለሁ መጨረሻቸው ጥፋት ነው ሆዳቸው አምላካቸው ነው ክብራቸው በነውራቸው ነው አሳባቸው ምድራዊ ነው” ፊል.3፡18፡፡

የመስቀሉ በረከት ይደርብን

anoros gedam 5.jpg

አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ

መስከረም 13 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

anoros gedam 5.jpgአቡነ አኖሬዎስ በ13ኛው መ.ክ.ዘ የነበሩ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ናቸው፡፡ ትልቁ አኖሬዎስ ይሏቸዋል፡፡ የአቡነ ዜና ማርቆስ የእኅት ልጅ ናቸው፡፡ አባታቸው ቄስ ሰላማ እናታቸው ክርስቶስ ዘመዳ ሲባሉ የትውልድ ቦታቸው ምዕራብ ሸዋ ሙገር አካባቢ ልዩ ስሙ ማትጌ በሚባል ቦታ ነው፡፡ ገድለ ዜና ማርቆስ አባቱ ዘርዐ አብርሃም የተባለ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት ዘመድ ነበረ ይላል፡፡

ለአቡነ አኖሬዎስ ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም ናርዶስ ሲሆን በሕፃንነታቸው የዳዊትን ንባብና የመጻሕፍትን ትርጓሜ ከተማሩ በኋላ በወቅቱ ከነበሩበት ግብፃዊ ጳጳስ ዲቁና ተቀበሉ፡፡ በወቅቱ ሐራንኪስ የተባለ የትርጓሜ መጻሕፍትና የዜማ ዐዋቂ በቤታቸው በእንግድነት ለብዙ ጊዜ በቆየበት ወቅት ለአቡነ አኖሬዎስ ዜማና ትርጓሜ መጻሕፍት በሚገባ አስተምሯቸዋል፡፡ በዚህም ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ዜማና ትርጓሜ መጻሕፍት የበለጠ ለመረዳት ከነበራቸው ፍላጎት አንጻር ወደ ደብረ አስቦ (ደብረሊባኖስ) በመሔድ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተገናኙ፡፡ በደብረ አስቦ (ደብረሊባኖስ) በገዳም ለረዥም ዓመታት ካገለገሉና ከተማሩ በኋላ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ መንኩሰው አባ አኖሬዎስ ተባሉ፡፡

የገዳሙ መነኮሳት በሊቀ ዲያቆንነት መርጠዋቸው ትርጓሜ መጻሕፍትና ዜማ ያስተምሯቸው ነበር፡፡  ትጋታቸውን ያዩት የገዳሙ መነኮሳትም ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት በታች የገዳሙ መጋቢ አድረገው መረጧቸው፡፡ በዚያ ዘመን በገዳሙ ወንዶች እና ሴቶች መነኮሳዪያት በአንድነት ይኖሩ ነበር፡፡ ነገር ግን አቡነ አኖሬዎስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን አማክረው የሴትና የወንድ ገዳም እንዲለይ አደረጉ፡፡ ከዚህ በኋላ በወቅቱ በነበሩት አቡነ ቄርሎስ ዘንድ ተልከው ቅስናን ተቀበሉ፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ ወደ ትግራይ ጸዐዳ አምባ ተጉዘው ከአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ጋር ቆዩ፡፡ ነገር ግን አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ወዲያው ስላረፉ ወደ ደብረ አስቦ ተመልሰው አበ ምኔቱን እጨጌ ፊልጶስን እየተራዱ ገዳሙን ማገለግሉ ጀመሩ፡፡

anoros gedam 7.jpgበ1317ዓ.ም ንጉሥ ዓምደ ጽዮን በዘመነ መንግሥቱ የስብከተ ወንጌልን መስፋፋት ሥራ አጠናከረ፡፡ ይኸውም ግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ዮሐንስ ሲያርፉ ወደ ግብፅ ልዑካንን ልኮ አቡነ ያዕቆብን አስመጣ፡፡ በዚህ ወቅት አቡነ ያዕቆብ ከአቡነ ፊልጶስ ጋር በመነጋገር “ኢትዮጵያ በአንድ ጳጳስ መወሰን የለባትም፡፡” በማለት እጨጌ አቡነ ፊልጶስን ኤጲስ ቆጶስነት ሰይመው ሐዋርያዊ አገልግሎት እንዲፈጽሙ ዐሥራ ሁለቱን ንቡራነ ዕድ ለስብከተ ወንጌል በመላዋ አገሪቱ ክርስትና እንዲስፋፋ አቡነ ያዕቆብ ባቀረበው ሀሳብ መሠረት ተሰማሩ፡፡ እነሱም አቡነ ፊልጶስ ዘደብረ ሊባኖስ /ኤጲስ ቆጶስ/፣ አቡነ አኖሬዎስ ዘሞረት፣ አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋር፣ አቡነ ሳሙኤል ዘወገግ፣አቡነ አኖሬዎስ ዘወረብ፣አቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ፣አቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘግድም፣ አቡነ መርቆሬዎስ ዘመርሐ ቤቴ፣ አቡነ አድኃኒ ዘዳሞት፣ አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል፣ አቡነ ኢዮስያስ ዘወጅ፣ አቡነ ዮሴፍ ዘእናርያ ነበሩ፡፡

ሀገረ ስብከት ተሰጥቷቸው ለሐዋርያዊ ተልእኮ ተሰማሩ፡፡ ይህ የተቀናጀ የስብከተ ወንጌል ሥምሪት ሲደረግ ከተሰዓቱ ቅዱሳን በኋላ መጀመሪያና ትልቅ ለውጥ ያመጣ ነው፡፡ እነዚህ ዐሥራ ሁለቱ አበው “ንቡረ እድ” የሚል መጠርያ ኖሯቸው ክህነት ከመስጠት ውጭ ያለውን የኤጲስ ቆጶሱን ሥራ ይሠሩ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ለአቡነ አኖሬዎስ እንደ ግብጦን የተባለ ቦታ ደረሳቸው፡፡ ይህ ቦታ ከግንደ በረት እስከ ባሌ ያለውን አገር ያካትታል፡፡ እርሳቸውም ባሌ በመሄድ ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ተክለው ክርስትናን አስፋፉ፡፡ የሐዋርያነት አገልግሎታቸው እስከ ኬንያ ድንበር ደርሶ ነበር፡፡

በአካባቢው ስብከተ ወንጌልን ካስፋፉ በኋላ ባርጋባን የተባለ የአካባቢው ሰው ደግነታቸውንና ትምህርታቸውን ተመልክቶ በጽጋጋ ገዳም (ደሴ አካባቢ) እንዲመሠርቱ ጋበዛቸው፡፡ ጽጋጋ እንደ ደረሱ መምለክያነ ጣዖታት በእጅጉ ተቃውመዋቸው ነበር፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በትምህርታቸውና በበርጋባን ረዳትነት ተቃውሞው በረደ፡፡ በርጋባንም በትምህርታቸው ይማረክ እንጂ ክርስቲያን አልነበረምና ተጠምቆ ዘካርያስ ተባለ፡፡ አቡነ አኖሬዎስም የአካባቢውን ሕዝብ ለማስተማር ካላቸው ፍላጎትና የምነና ሕይወትንም ለማጠናከር በጽጋጋ ገዳም መሠረቱ፡፡ በገዳሙ የሚሰበሰቡት መነኮሳትም ቁጥር በየቀኑ ይጨምር ነበር፡፡ ከትውልድ አካባቢያቸውም በየጊዜው ብዙዎች ይመጡ ነበር፡፡

አቡነ አኖሪዎስ ዘወረብ ተብለውም ይጠራሉ፡፡ ይህም ወረብ በሚባለው ሥፍራ በተጋድሎ የቆዩበት ቦታ በመሆኑና ዐፅማቸው በዚያ እንደተቀበረ ይነገራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አንድ የእስልምና ተከታይ ወረብ ከተባለው አካባቢ የአቡነ አኖሪዎስ ነው ብሎ ያመጣው መስቀል አሁን በጽጋግ ገዳማቸው ይገኛል፡፡

 አቡነ አኖሬዎስ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን 1297-1317 ዓ.ም የአባቱን ዕቁባት ማግባቱን ሰሙ በጉዳዩም እጅግ አዝነው እጨጌ አቡነ ፊልጶስ ዘደብረ ሊባኖስ፣ አቡነ ናትናኤል፣ አባ እንድርያስ፣ አባ ድምያኖስ፣ አባ ዮሐንስ፣ አባ ገብረ ናዝራዊ፣ አባ ዘርዐ ክርስቶስ፣ አባ ገብረ አምላክ፣ አባ ብንያም፣ አባ አቡነ አሮን ዘደብረ ዳሬት ይዘው ወደ ንጉሡ ከተማ መጡ፡፡

ንጉሥ ዓምደ ጽዮንም የአባቶችን ድንገት መምጣት አይቶ “ምን አመጣችሁ?” ብሎ ሲጠይቃቸው አቡነ አኖሬዎስ “የአባትህ ዕቁባት እናትህ ማለት ስለሆነች ማግባትህ አግባብ አይደለም፡፡ መኝታህን ማርከስህን ተው፡፡ ያለበለዝያ እንለይሃለን፤ ሥጋ ወደሙንም አናቀብልህም አሉት” ንጉሡም መነኮሳቱን አስደበደባቸው፡፡ ደማቸውም በአደባባይ ፈሰሰ፡፡ በዚያ ዕለት በከተማው እሳት ተነሥቶ እስከ ቤተ መንግሥቱ በመድረሱ ማስደብደቡን ትቶ በአማካሪዎቹ የቀረበለትን ሐሳብ በመቀበል ወደ ሩቅ አገር ለማጋዝ ወሰነ፡፡ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን ይህንን ተግሳጽ ከቁም ነገር አልቆጠረውም ነበር፡፡ ነገር ግን ሥጋወ ደሙ በድፍረት  ሊቀበል በቀረበ ጊዜ አባቶች “የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ” ተብሏል ብለው  ከለከሉት፤ እየተናደደ ወደ ቤተ መንግሥት ገባ፡፡ በቤተ መንግሥቱም ጳጳሱን፣ ንቡራነ እዱንና በአንድ ሐሳብ የጸኑ ሌሎች ሰባ ሁለት ካህናት አስጠርቶ አቡነ ያዕቆብ ከእኔ አያስጥላችሁም፡፡ በአስቸኳይ ወደ ሀገሩ(ግብፅ) እልከዋለሁ፡፡ ሲል በቁጣ ተናገራቸው፡፡ እነርሱ ግን “በቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት ኑር፣ የአባትህን ሚስት መፍታት ይገባሃል” ብለው ጸኑበት፡፡

በዚህ ምክንያት አባቶች እየተጋዙ በሰሜን በደቡብና በምዕራብ ኢትዮጵያ ተሰደዱ፡፡ ከእነርሱ ስደት በኋላ ብዙ ካህናትና መነኮሳት ወደ ንጉሡ መጡ፡፡ በድፍረትም ይገሥጹት ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት መነኩሴ ወደ ከተማ እንዳይገባ እስከ መከልከል ደርሷል፡፡ በመጨረሻ አባ እንድርያስ የተባሉ አባት ወደ ንጉሡ መጥተው መክረው ንስሐ አስገብተው ወደ ቤተ ክርስቲያን መለሱት፡፡
አቡነ አኖሬዎስ ወደ ወለቃ /ደቡብ ወሎ ጋሥጫ አካባቢ/ ተጉዘው ለጥቂት ዓመታት ከቆዩ በኋላ ዓምደ ጽዮን ዐረፈ፡፡ መንግሥቱንም ሰይፈ አርዕድ ወረሰ፡፡ ንጉሥ ሰይፈ አርዕድም የተጋዙት አባቶች በሙሉ እንዲመለሱ ዐወጀ፡፡ አቡነ አኖሬዎስም ወደ በኣታቸው ጽጋጋ ተመለሱ፡፡

ንጉሥ ሰይፈ አርዕድ እንደ አባቱ የአባቱን ዕቁባት ማግባቱን ሰሙ፡፡ ቀድሞ ንጉሥ ዓምደ ጽዮንን የገሰጹት እነዚያ ቅዱሳን አባቶች ተሰባስበው ወደ ንጉሡ መጡ፡፡ አቡነ አኖሬዎስ አፈ ጉባኤ ሆነው ንጉሡን ገሰጹት፡፡ ንጉሡም በወታደሮቹ አስደበደባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ከአፍ እና ከአፍንጫቸው ብዙ ደም ፈሰሰ፡፡ በኋላም ምድረ ጸወን ወደምትባል አገር /ደቡብ ወሎ፣ ቦረና/ ተጋዙ፡፡ በዚያም እጅግ ብዙ ተአምራት ማድረጋቸውና የንጉሡን ተግባር መቃወማቸው ስለተሰማ እንደገና ወደ ዝዋይ ደሴት ገማስቄ በምትባል ሥፍራ እንዲቀመጡ ተደረገ፡፡

በዝዋይ እያሉም ነገረ ሠሪዎች ወደ ንጉሡ ቀርበው “አኖሬዎስ ሠራዊትህን ሁሉ ማርኮ ሊያመነኩሳቸው ነውና አንድ ነገር አድርግ፡፡” ብለው ስለ መከሩት አቡነ አኖሬዎስ የፊጥኝ በወታደሮች ታስረው እንዲመጡ አደረገና፡፡ ባሌ ግድሞ ወደ ተባለው አገር እንዲጋዙ አደረገ፡፡

እዚያም ለብዙ ዓመታት ገዳም መሥርተው በሐዋርያነት እያገለገሉ ከቆዩ በኋላ ወደ ጥንት በኣታቸው ጽጋጋ እንዲመለሱ ተፈቀደላቸው፡፡ በዚያም በማስተማርና በምነና ሕይወት ሲተጉ ኖሩ፡፡ ኋላም የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ዐፅም በደብረ ሊባኖስ ከሌሎች አበው መነኮሳት ጋር አፍልሰው ከቀበሩ በኋላ በተወለዱ በ104 ዓመታቸው መስከረም 18 ቀን 1471 ዓ.ም በጽጋጋ ገዳማቸው ዐረፉ፡፡ በረከታቸው በሁላችንም ይደር፤ አሜን፡፡

 

  • ምንጭ፡- ገድለ አቡነ አኖሬዎስ፣ ገድለ ተክለ ሃይማኖት፣ የቤተ ክርስቲያን መረጃዎች

የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠርና አጠቃቀሙ ክፍል 2

 መስከረም 22 ቀን 2005 ዓ.ም.

ዲ/ን ኃ/ኢየሱስ ቢያ

 

መጥቅዕ እና አበቅቴ ከየት መጣ ቢሉ

  1.  የፀሐይና የጨረቃ ቀን አቆጣጠር ልዩነት ነው፡፡ አንድ ዓመት በፀሐይ 365 ቀን ከ15 ኬክሮስ ሲሆን በጨረቃ 354 ቀን ከ22 ኬክሮስ ነው፡፡ ስለዚህ የሁለቱ ልዩነት 365 – 354 = ይህ ልዩነት አበቅጽ ተባለ፡፡

  2.  ሁለተኛው የቅዱስ ዲሜጥሮስ ሱባኤ ውጤት ነው፡፡ በዓላትና አጽዋማት የሚውሉበት ቀን በጥንተ ዕለቱ እንዲውል ለማድረግ ይመኝ ነበርና ከሌሊቱ 23 ሱባኤ ከቀኑ 7 ሱባኤ ገብቷል፡፡ ይህንን 23×7=161 ይሆናል፡፡ 161 ሲካፈል ለ30= 5 ይደርስና 11 ይተርፋል ይህን ቀሪ አበቅቴ አለው፡፡ 7 x7 = 49 ይሆናል፡፡ 49 ለ 30 ሲካፈል 1 ጊዜ ደርሶ 19 ይቀራል ይህን ቀሪ መጥቅህ አለው፡፡

– ዓመተ ዓለሙን

– ወንጌላዊውን

– ዕለቱን

– ወንበሩን

– አበቅቴውን

– መጥቁን

– መባጃ ሐመሩን

– አጽዋማትን

በዓላትን ለይቶ ለማወቅ ሒሳባዊ ሰሌቱ እንዲሚከተለው ነው፡፡ 

1. ዓመተ ዓለሙን ለማግኘት ስሌቱ ዓመተ ኩነኔ ሲደመር ዓመተ ምሕረት እኩል ይሆናል ዓመተ ዓለም፡፡ ምሳሌ 5500 + 2006= 7500 ዓመተ ዓለም ይባላል

2. ወንጌላዊውን ለማግኘት ስሌቱ፡- ዓመተ ዓለሙን ለአራት ማካፈል ማለትም ሰባት ሺህ አምስት መቶ ስድስት ለአራት ሲካፈል ለአንድ ወንጌላዊ አንድ ሺህ ስምንት መቶ ሰባ ስድስት ደርሶ ሁለት ይተርፋል፡፡ ዘመኑ ዘመነ ማርቆስ ይባላል፡፡
ዓመተ ዓለሙ ለ4 ተካፍሎ፡-

– ቢቀር ማቴዎስ

– ቢቀር ማርቆስ

– ቢቀር ሉቃስ

እኩል ሲካፈል ዮሐንስ ይሆናል፡፡

3. ዕለቱን/መስከረም 1 ቀንን ለማግኘት ስሌቱ ዓመተ ዓለም ሲደመር መጠነራብዒት /ለአንድ ወንጌላዊ የደረሰውን/ ሲካፈል ለሰባት ለምሳሌ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ስድስት ሲደመር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ሰባ ስድስት እኩል ይሆናል ዘጠኝ ሺህ ሦስት መቶ ሰማንያ ሁለት፡፡ ይህን ለሰባት ሲያካፍሉት ዘጠኝ ሺህ ሦስት መቶ ሰማንያ ሁለት ለሰባት ሲካፈል አንድ መቶ ሰላሳ አራት ደርሶ ሁለት ይቀራል፡፡

ዓመተ ዓለሙና መጠነ ራብዒት ተደምሮ ለሰባት ተካፍሎ

1. ቢቀር ማክሰኞ

2. ቢቀር ረቡዕ

3. ቢቀር ሐሙስ

4. ቢቀር ዓርብ

5. ቢቀር ቅዳሜ

6. ቢቀር እሑድ

እኩል ሲካፈል ሰኞ ይሆናል፡፡ ስለዚህ የዘንድሮው ቀሪ 2 ስለሆነ ዕለቱ ረቡዕ ነው፡፡

4. ተረፈ ዘመኑን /ወንበሩን/ ለማግኘት ስሌቱ ዓመተ ዓለሙ ለሰባት ተካፍሎ ቀሪው ተረፈ ዘመን/ ወንበር ይባላል፡፡ ከቀሪው ላይ ስለተጀመረ ተቆጠረ ስላልተፈጸመ ታተተ/ ተቀነሰ ብሎ አንድ መቀነስ ቀሪው ወንበር ይባላል፡፡
ለምሳሌ፡- 7506፥7=395 ደርሶ 1 ይቀራል 1-1=0 ዘንድሮ ወንበሩ ዜሮ ሆነ ማለት ነው፡፡

5. አበቅቴን ለማግኘት ስሌቱ ወንበር ሲባዛ በጥንት አበቅቴ /11/ ሲካፈል ለሰላሳ ቀሪው አበቅቴ ይባላል፡፡ የዘንድሮ ወንበሩ ዜሮ ስለሆነ በአሥራ አንድ ሲባዛ ውጤቱ ዜሮ በመሆኑ አበቅቴ ዜሮ/አልቦ/ ነው፡፡

6. መጥቅዕን ለማግኘት ስሌቱ ወንበር ሲባዛ በጥንተ መጥቅዕ /19/ ሲካፈል ለሰላሳ ቀሪው መጥቅዕ ይባላል፡፡ የዘንድሮ ወንበሩ ዜሮ/አልቦ ስለሆነ በአሥራ ዘጠኝ ሲባዛ ውጤቱ ዜሮ/አልቦ በመሆኑ መጥቅዕ ዜሮ/አልቦ ነው፡፡
እዚህ ላይ ስትደርስ አዋጁን ተመልከት

አዋጁ/መመሪያው – መጥቅዕ ከ14 በላይ ከሆነ በመስከረም ይውላል የመስከረም ማግስት/ሳኒታ የካቲት ነው፡፡

– 14 ራሱ መጥቅዕ መሆን አይችልም፡፡

– መጥቅዕ ከ14 በታች ከሆነ በጥቅምት ይውላል የጥቅምት ማግስት/ሳኒታ ጥር ነው፡፡

– መጥቅዕ ሲደመር አበቅቴ ሁል ጊዜ 30 ነው፡፡

– መጥቅዕ አልቦ ዜሮ ሲሆን መስከረም 30 የዋለበት የቀኑ ተውሳክ መባጃ ሐመር ይሆናል፡፡

7. መባጃ ሐመርን ለማግኘት ስሌቱ የዕለት ተውሳክ ሲደመር መጥቅዕ ሲካፈል ለሰላሳ ይሆናል፡፡ ለ30 መካፈል ካልቻለ እንዳለ ይወሰዳል፡፡
ስለዚህ ዘንድሮ መጥቅዕ አልቦ ስለሆነ መስከረም ሰላሳ የዋለበት ዕለት ሐሙሰ ነው፡፡ የሐሙስ ተውሳክ 3 ነው፡፡ ሦስት ከዜሮ ጋር ተደምሮ ለ30 መካፈል ስለማይችል እንዳለ ይወሰዳል፡፡ ስለዚህ መባጃ ሐመሩ 3 ነው፡፡ ከዚህ በኋላ የአጽዋማትና የበዓላትን ተውሳክ እየደመርክ አውጣ፡፡

8. ጾምን ለማግኘት ስሌቱ መባጃ ሐመር ሲደመር የጾም ተውሳክ ሲካፈል ለሰላሳ ይሆናል /ለ30 መካፈል ካልቻለ እንዳለ ይወሰዳል/

9. በዓልን ለማግኘት ስሌቱ መባጃ ሐመር ሲደመር የበዓል ተውሳክ ሲካፈል ለሰላሳ ይሆናል፡፡ /ለ30 መካፈል ካልቻለ እንዳለ ይወስዳል

በዚህ መሠረት የ2006 ዓ.ም. አጽዋማትና በዓላትን አውጣ

1. ጾመ ነነዌ = 3 + 0=3 የካቲት 3 ቀን ሰኞ ይውላል፡፡

2. ዐቢይ ጾም = 3 + 14 = 17 የካቲት 17 ቀን ሰኞ ይውላል፡፡

3. ደብረ ዘይት = 3 + 11= 14 መጋቢት 14 ቀን እሑድ ይውላል፡፡

4. ሆሣዕና = 3 + 2= 5 ሚያዚያ 5 ቀን እሑድ ይውላል፡፡

5. ስቅለት = 3 + 7= 10 ሚያዚያ 10 ቀን ዓርብ ይውላል፡፡

6. ትንሣኤ = 3 + 9= 12 ሚያዚያ 12 ቀን እሑድ ይውላል፡፡

7. ርክበ ካህናት = 3 + 3= 6 ግንቦት 3 ቀን ረቡዕ ይውላል፡፡

8. ዕርገት = 3 + 18= 21 ግንቦት 21 ቀን ሐሙስ ይውላል፡፡

9. ጰራቅሊጦስ = 3 + 28= 31 – 30 = 1 ሰኔ 1 ቀን እሑድ ይውላል፡፡

10. ጾመ ሐዋርያት = 3 + 29= 32 – 30= 2 ሰኔ 2 ቀን ሰኞ ይውላል፡፡

11. ጾመ ድኅነት = 3 + 1= 4 ሰኔ 4 ቀን ረቡዕ ይውላል፡፡

ሃሌ ሉያ ባዘ ንዜከር ሐሰበተ ሕጉ

ወትዕዛዛትሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኀኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ

ሐሳበ ነቢያት ወሐዋርያት

ሐሳበ ጻድቃን ወሰማዕታት

ሐሳበ ደናግል ወመነኮሳት

ሐሳበ ኄራን መላእክት እንዘ ሀሎነ በዘመነ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ቡሩክ ያበጽሐነ እስከ ዘመነ ቅዱስ ሉቃስ ፍስሐ ዘናዊ በሰላመ እግዚአብሔር አሜን፡፡

በሃምሳ ምዕት ወበ ሃምሳቱ ምዕት ኮነ ዓመተ ኩነኔ ዓመተ ፍዳ፡፡ /5500/

በሰብአ ምዕት ወበሃምስቱ ምዕት ወስድስቱ ኮነ ዓመተ ዓለም /7506/

በእስራ ምዕት ወስድስቱ /2006/ ኮነ ዓመተ ምሕረት ዮም ሠረቀ ለነ ሠርቀ ወርህ መስከረም ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ወርኃ ጥቅምት በሰላመ እግዚአብሔር አሜን፡፡

ረቡዑ ሠረቀ ዕለት /ዕለቱ ረቡዕ/

አሚሩ ሠረቀ መዓልት /ቀኑ አንድ/

ሰኑዩ ሠርቀ ሌሊት /ሌሊቱ ሁለት/

ስድሱ ሠርቀ ወርኅ /በጨረቃ ስድስት ሆነ ማለት ነው/

ስብሐት በል ቀጥሎም አቡነ ዘበሰማያት በል

 

የሌሊት አቆጣጠር ስሌቱ

– አበቅቴ ሲደመር ህፀፅ ሲደመር መዓልት እኩል ይሆናል ሌሊት፡፡

የጨረቃ አቆጣጠር ስሌቱ

– አበቅቴ ሲደመር ህፀፅ ሲደመር መዓልት ሲደመር ጨረቃ እኩል ይሆናል የጨረቃ ሌሊት፡፡

አበቅቴ የተረፈ ዘመን ቁጥር ነው፤ ህፀፅ ጨረቃ ጠፍ ሆና የምታድርበት ሌሊት ነው፡፡ አንድ ጊዜ 29/30 ስለምትሆን የሁለት ወር ህፀፅ አንድ ነው፡፡ መዓልት ከ1-30 ያለው የወሩ ቀን የደረሰበት ዕለት ነው፡፡ የጨረቃ ህፀፅ ሁል ጊዜ 4 ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 

በሶዲቾ ዋሻ የእመቤታችን ጽላት በአገር ሽማግሌዎች እየተጠበቀ ነው

 

 

 መስከረም 9ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ልዩ ስሙ ሶዲቾ ዋሻ ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ በ984 ዓ.ም. የነበረ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽላት በአገር ሽማግሌዎች እየተጠበቀ ነው፡፡

 

በግንቦት ወር ላይ ቆሞስ አባ ኤልያስ የተባሉ አባት ወደ ሶዲቾ ዋሻ በመምጣት ከሚመለከታቸው የቤተክርስቲያንና የዞኑ የመንግስት አካላት ፈቃድ በማግኘት ከዋሻው ውስጥ የእመቤታችን ቅድስት ድንግልማርያም ጽላት፤ የአንድ አባት አጽምና የእጅ መስቀል በቁፋሮ ማውጣታቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በሥፍራው በሚከናውነው የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ብዙዎች በጸበል እየተፈወሱ ሲሆን ኢ- አማንያንም ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት እየተመለሱ ይገኛሉ፡፡ ይህ ያሳሰባቸው አንዳንድ ግለሰቦች በቡድን በመደራጀት በቦታው ላይ የሚገኙትን አባት ቆሞስ አባ ኤልያስን ከአካባቢው እንዲለቁ በማስገደድ፤ በማስፈራራትና ድንጋይ በመወርወር ደብድበው ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው የሚታወስ ነው፡፡ በርካታ ጸበል ሊጠመቁ የመጡ ምእመናንም በድንጋይ ድብደባ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት የወረዳውና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጆች ከምእመናን ጋር በመሆን ለሚመለከተው የወረዳ፤ ብሎም የዞኑ መንግስት ባለሥልጣናት ድረስ ጉዳዩን በመውሰድ እልባት እንዲያገኝ ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን ከወረዳው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ነገር ግን የወረዳው ካቢኔ በዋሻው ውስጥ የሚገኘውን ጽላት አቅራቢያው ወደሚገኘው የእመቤታችን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ወስዳችሁ እንድታስገቡ፤ ቦታውንም እንድትለቁ በማለት መስከረም 3 ቀን 2005 ዓ.ም. የመጨረሻ የቀን ገደብ አስቀምጦ እንደነበር የወረዳው ቤተ ክህነት ሓላፊዎች ይገልጻሉ፡፡ ነገር ግን ጉዳዩ በዞን ደረጃ እንዲታይ ቢደረግም መፍትሔ ማግኘት ባለመቻሉ ወደ ክልል በመሔድ አቤቱታ በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡

 

ጽላቱን ያገኙት አባት ቆሞስ አባ ኤልያስ ማንንም እንዳያጠምቁ፤ እንዳያስተምሩ፤ የማዕጠንትም ሆነ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት እንዳያከናውኑ ተከልክለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ቆሞስ አባ ኤልያስ ከዋሻው በመውጣት ወዳልታወቀ ሥፍራ በመሔድ ሱባኤ እንደገቡ የሚነገር ሲሆን ጽላቱ በአካባቢው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታይ በሆኑ የአገር ሽማግሌዎች ጥበቃ እየተደረገለት መሆኑን የወረዳው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ አባ ኃይለ ሚካኤል ገልጸዋል፡፡

 

 

tena 3

5ኛው ሀገር አቀፍ ዓመታዊ ዐውደ ጥናት ተካሔደ

 

መስከረም 3 ቀን 2006 ዓ.ም.

 
በእንዳለ ደምስስ

tena 3በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው 5ኛው ሀገረ አቀፍ ዓመታዊ ዐውደ ጥናት “ጥናትና ምርምር ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ መጠናከር” በሚል ጳጉሜ 2 እና 3 ቀን 2005 ዓ.ም. በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ተካሄደ፡፡

በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልእክት “እግዚአብሔር ሲፈቅድ ልጆቹን ለመልካም ነገር ያውላቸዋል፡፡ የዚህ ጉባኤ ዓላማም ለመልካም ሥራ ነው፡፡ መልካም ሰዎች ለመልካም ነገር ይውላሉና፡፡ ሰው ሰውን አፍቃሪ፤ ረጂ፤ ለሀገሩም ለእግዚአብሔር የተመቸ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ የዘመኑ የፈጠራ ትምህርት ከመንፈሳዊ ትምህርት ጋር በተያያዘ መመራመርን ይጠይቃል፡፡ ሰው ካወቀ ለሌላው ያሳውቃል፤ ለሌላው ያስረዳል፤ መልካም መሳሪያም ይሆናል፡፡ ይህ የተጀመረው ምርምርና ጥናት እኛንም የበለጠ ያፋቅረናል፤ በሃይማኖት እንድንቆም፤ የበለጠም እንድንሠራ ያደርገናል፡፡ የተሸሸገውን ታሪካችንን፤ያሳውቀናል፤ ልጆቻችንንም ተረካቢ ያደርጋቸዋል፡፡ ጥሩ ጅምር በመሆኑ በዚሁ እንድንቀጥል ያስፈልጋል” ብለዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በተካሄደው ዐውደ ጥናት ስምንት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል “ጥንታዊ ቅርሶችን ከመጠበቅና ከማሰባሰብ አንጻር የካህናት ሚና” በፕሮፌሰር አየለ በክሪ በመቀሌtena 3 2 ዩኒቨርስቲ የታሪክና ባህል ጥናት መምህር፤ “ልማትና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በአቶ ፀጋዬ አስገለ እና በመምህር ካኽሳዬ ገብረ እግዚአብሔር፤ “ሥርዓተ ፆታና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በወ/ሮ ሐረገወይን ቸርነት በፐብሊክ ሣይንስና ምግብ ዋስትና የሥርዓተ ፆታ አማካሪ፤ “የሕይወት ምህንድስና፤ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በአቶ ኃይለ ማርያም ላቀው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤሌክትሪካል ኢንጂነር ቅዳሜ ጳጉሜ 2 ቀን 2005 ዓ.ም. በዐውደ ጥናቱ ላይ የቀረቡ አራት ጥናታዊ ጽሑፎች ናቸው፡፡

እሑድ በተካሄደው ቀጣይ ዐውደ ጥናትም አራት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል፡፡ “የበዓላት አከባበር፤ ቱሪዝምና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በአቶ ባንታለም ታደሰ በጎንደር ዩኒቨርቲ የታሪክና የቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር፤ “የሃይማኖት ቱሪዝም ልማት ተግዳሮት እና ትንበያ” በአቶ ኤርሚያስ ክፍሌ በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ወንዶ ገነት ስኩል ኦፍ ዋይልድ ላይፍ እና ቱሪዝም መምህር፤ “ሳይንስና ሃይማኖት እንዴት ይለያያሉ” በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የንግድ ሥራ ኮሌጅ መምህር፤ “ሃይማኖታዊ እሳቤዎች በሳይንስ እይታ” በዶክተር አብርሃም አምኃ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል መምህር ጥናታዊ ጽሑፎቻቸውን አቅርበዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በተካሄደው ዐውደ ጥናት ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በጥናት አቅራቢዎች ምላሽ የተሰጠ ሲሆን ሰፊ ውይይትም ተካሂዶባቸዋል፡፡ ዐውደ ጥናቱ ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት የቀጥታ ስርጭት ሽፋን የነበረው ሲሆን በርካታ በተለያዩ አህጉራት የሚገኙ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ተከታትለውታል፡፡ ጥያቄዎቻቸውንም በማቅረብ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡

 

የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠርና አጠቃቀሙ

ዲ/ን ኃ/ኢየሱስ ቢያ

የዘመን አቆጣጠር ማለት፡- ዓመታትን፤ ወራትን፣ ሳምንታትን፣ ዕለታትን፤ ደቂቃንና ድቁቅ ሰዓታትን በየሥፍራቸው የሚገልጽ፤ የሚተነትን፤ የሚለካ የቤተ ክርስቲያን የቁጥር ትምህርት ነው፡፡
እነዚህ ሁሉ ተመርምረው ተመዝነው ተቆጥረው ሲያበቁ ምድብና ቀመር ተሰጥቶአቸው የሚገኙበትን ውሳኔና ድንጋጌ የሚያሰማ የዘመን አቆጣጠር ሐሳበ ዘመን ይባላል፡፡
ዓመታታ፣ ወራት፣ ሳምንታት፣ ዕለታትና ሰዓታት የሚለኩት /የሚቆጠሩት በሰባቱ መሰፈሪያና በሰባቱ አዕዋዳት ነው፤ እነሱም፡-
1.    ሰባቱ መስፈርታት
–    ሳድሲት
–    ኃምሲት
–    ራብዒት
–    ሣልሲት
–    ካልዒት
–    ኬክሮስ
–    ዕለት ይባላሉ
2.    ሰባቱ አዕዋዳት
–    ዐውደ ዕለት፡- ከእሑድ እስከ ቅዳሜ ያሉት ሰባቱ ዕለታት ናቸው፤ አውራህን ለማስገኘት በዚህ ሲመላለሱ ይኖራሉ፡፡
–    ዐውደ ወርኅ፡- በፀሐይ 30 ዕለታት በጨረቃ 29/30 ዕለታት ናቸው ዓመታትን ለማስገኘት በዚህ ሲመላለሱ ይኖራሉ፡፡
–    ዐውደ ዓመት፡- በፀሐይ ቀን አቆጣጠር 365 ቀን ከ15 ኬክሮስ፡፡ በጨረቃ ቀን አቆጣጠር 354 ቀን ከ22 ኬኬሮስ ነው፡፡ እነዚህ 3ቱ በዕለት ሲቆጠሩ አራቱ በዓመት ይቆጠራሉ፡፡ ዘመናትን ለማስገኘት በዚህ ሲመላለሱ ይኖራሉ፡፡
–    ዐውደ ፀሐይ፡- 28 ዓመት ነው በዚህ ዕለትና ወንጌላዊ ይገናኙበታል፡፡
–    ዐውደ አበቅቴ፡- 19 ዓመት ነው በዚህ ፀሐይና ጨረቃ ይገናኙበታል፡፡
–    ዐውደ ማኅተም፡- 76 ዓመት ነው በዚህ አበቅቴና ወንጌላዊ ይገናኙበታል፡፡
–    ዐውደ ቀመር፡- 532 ዓመት ነው በዚህ ዕለትና ወንጌላዊ አበቅቴም ይገናኙበታል፡፡
የዘመናት/የጊዜያት ክፍልና መጠን
1 ዓመት በፀሐይ 365 ቀን ከ15 ኬክሮስ፣ በጨረቃ 354 ቀን ከ22 ኬኬሮስ ነው፡፡ 1 ወር በፀሐይ 30 ዕለታት አሉት በጨረቃ 29/30 ዕለታት አሉት፡፡ ዕለት 24 ሰዓት ነው፤ ቀን 12 ሰዓት ነው ፤ ሰዓት 60 ደቂቃ ነው ፤ ደቂቃ 60 ካልዒት ነው ፤ካልዒት 1 ቅጽበት ነው፡፡ ኬክሮስ ማለት የክፍል ዕለት ሳምንት ነው /የዕለት 1/60ኛው ወይም 1/24ኛ ሰዓት ነው/ 1 ዕለት 24 ሰዓት ወይም 60 ኬክሮስ ማለት ነው፡፡
ክፍለ ዓመት /የዓመት ክፍሎች/
1.    መፀው፡- ከመስከረም 26 እስከ ታኅሳስ 25 ቀናት ድረስ ያለው ክፍለ ዓመት መጸው ይባላል፡፡ በዚህ ክፍለ ዓመት ሌሊቱ ረጅም ቀኑ አጭር ነው፡፡
2.    በጋ፡- ከታኅሳስ 26 እስከ መጋቢት 25 ቀናት ድረስ ያለው ክፍለ ዓመት በጋ ይባላል፡፡ በዚህ ክፍለ ዓመት የቀኑና የሌሊቱ ርዝመት እኩል ነው፡፡
3.    ፀደይ፡- ከመጋቢት 26 እስከ ሰኔ 25 ቀናት ድረስ ያለው ፀደይ ይባላል፡፡ በዚህ ክፍለ ዓመት ቀኑ ይረዝማል ሌሊቱ ያጥራል፡፡
4.    ክረምት፡- ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25 ቀናት ድረስ ያለው ክረምት ይባላል፡፡ በዚህ ከፍለ ዓመት የቀኑና የሌሊቱ ርዝመት እኩል ነው፡፡
በአራቱ ወንጌላውያን መካከል የዘመናት አከፋፈል /ርክክብ/
1.    ማቴዎስ ዘመኑን ከምሽቱ በ 1ሰዓት ጀምሮ በዓመቱ ከሌሊቱ በ6 ሰዓት ይፈጽማል፡፡
2.    ማርቆስ ዘመኑን ከሌሊቱ በሰባት ሰዓት ጀምሮ በዓመቱ ከጠዋቱ በ12 ሰዓት ይፈጽማል፡፡
3.    ሉቃስ ዘመኑን ከጠዋቱ በ1 ሰዓት ጀምሮ በዓመቱ በቀትር በ6 ሰዓት ይፈጽማል፡፡
4.    ዮሐንስ ዘመኑን ከቀኑ በሰባት ሰዓት ጀምሮ በዓመቱ ከቀትር በኋላ በ12 ሰዓት ይፈጽማል፡፡

የየወራቱ ሌሊትና ቀን ስፍረ ሰዓት
1.    የመስከረም ወር ሌሊቱ 12 ሰዓት መዐልቱ 12 ሰዓት ነው፡፡
2.    የጥቅምት ወር ሌሊቱ 13 ሰዓት መዐልቱ 11 ሰዓት ነው፡፡
3.    የኅዳር ወር ሌሊቱ 14 ሰዓት መዐልቱ 10 ሰዓት ነው፡፡
4.    የታኅሣሥ ወር ሌሊቱ 15 ሰዓት መዐልቱ 9 ሰዓት ነው፡፡
5.    የጥር ወር ሌሊቱ 14 ሰዓት መዐልቱ 10 ሰዓት ነው፡፡
6.    የየካቲት  ወር ሌሊቱ 13 ሰዓት መዐልቱ 11 ሰዓት ነው፡፡
7.    የመጋቢት ወር ሌሊቱ 12 ሰዓት መዐልቱ 12 ሰዓት ነው፡፡
8.    የሚያዝያ ወር ሌሊቱ 11 ሰዓት መዐልቱ 13 ሰዓት ነው፡፡
9.    የግንቦት ወር ሌሊቱ 10 ሰዓት መዐልቱ 14 ሰዓት ነው፡፡
10.    የሰኔ ወር ሌሊቱ 19 ሰዓት መዐልቱ 15 ሰዓት ነው፡፡
11.    የሐምሌ ወር ሌሊቱ 10 ሰዓት መዐልቱ 14 ሰዓት ነው፡፡
12.    የነሐሴ ወር ሌሊቱ 11 ሰዓት መዐልቱ 13 ሰዓት ነው፡፡
የበዓላትና የአጽዋማት ኢየዐርግና ኢይወረድ
1.    ጾመ ነነዌ ከጥር 17 ቀን በታች ከየካቲት 21 ቀን በላይ አይውልም
2.    ዐቢይ ጾም ከየካቲት 1 ቀን በታች ከመጋቢት 5 ቀን በላይ አይውልም
3.    ደብረ ዘይት ከየካቲት 28 ቀን በታች ከሚያዝያ 2 ቀን በላይ አይውልም፡፡
4.    በዓለ ሆሣዕና ከመጋቢት 19 ቀን በታች ከሚያዝያ 23 ቀን በላይ አይውልም፡፡
5.    በዓለ ስቅለት ከመጋቢት 24 ቀን በታች ከሚያዝያ 28 ቀን በላይ አይውልም፡፡
6.    በዓለ ትንሣኤ ከመጋቢት 26 ቀን በታች ከሚያዝያ 3ዐ ቀን በላይ አይውልም፡፡
7.    ርክበ ካህናት ከሚያዝያ 20 ቀን በታች ከግንቦት 24 ቀን በላይ አይውልም፡፡
8.    በዓለ ዕርገት ከግንቦት 5 ቀን በታች ከሰኔ 19 ቀን በላይ አይውልም፡፡
9.    ጾመ ሐዋርያት ከግንቦት 16 ቀን በታች ከሰኔ 20 ቀን በላይ አይውልም፡፡
10.    ጾመ ድኅነት ከግንቦት 18 ቀን በታች ከሰኔ 22 ቀን በላይ አይውልም፡፡
ሁለት ዓይነት የተውሳክ አቆጣጠር አለ
1.    የዕለት ተውሳክ በቅዳሜ ይጀምራል፡፡
የቅዳሜ ተውሳክ 8፤ የእሑድ ተውሳክ 7፤ የሰኞ ተውሳክ 6፤ የማክሰኞ ተውሳክ 5፤ የረቡዕ ተውሳክ 4፤ የሐሙስ ተውሳክ 3፤ የዓርብ ተውሳክ 2
2.    የአጽዋማትና የበዓላት ተውሳክ
የነነዌ ተውሳክ 0፤ የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14፤ የደብረ ዘይት ተውሳክ 1፤ የሆሣዕና ተውሳክ 2፤ የስቅለት ተውሳክ 7፤ የትንሣኤ ተውሳክ 9፤ የርክበ ካህናት ተውሳክ 3፤ የዕርገት ተውሳክ 18፤ የጰራቅሊጦስ 28፤ የጾመ ሐዋርየት ተውሳክ 29፤ የጾመ ድኅነት ተውሳክ 1
በዓላትና አጽዋማት የሚውሉበት ቀን
–    ጾመ ነነዌ
–    ዐብይ ጾም
–    ጾመ ሐዋርያት
                     ሰኞ                   
–    ደብረ ዘይት
–    ሆሣዕና
–    ትንሣኤ
–    ጰራቅሊጦስ
                      እሑድ
–    ስቅለት
                      ዓርብ
–    ርክበ ካህናት
–    ጾመ ድኅነት
                       ረቡዕ
–    ዕርገት
                      ሐሙስ ቀን ይሆናል፡፡
ይቀጥላል

 

ከሶዲቾ ዋሻ ጽላት ያገኙት አባት ከፍተኛ ድብደባ ደረሰባቸው

በከምባታ ጠምባሮ ዞን በሶዲቾ ዋሻ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽላትና ንዋያተ ቅድሳት በቁፋሮ እንዲወጣ ያደረጉት አባት ቆሞስ አባ ኤልያስ ጳጉሜ 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ከፍተኛ ድብደባ ደረሰባቸው፡፡
ዋሻው በ1998 ዓ.ም. የተገኘና የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በቅርስነት ከያዛቸው የመስህብ ቦታዎች አንዱ ነው፡፡ በአካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቁጥር አነስተኛ ሲሆን የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች እንደሚበዙ ይታወቃል፡፡ ከዋሻው መገኘት በኋላ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች በዋሻው ውስጥ በዓመት 2 እና 3 ጊዜያት ጉባኤ ያካሒዱበት እንደነበር ይነገራል፡፡ በቅርቡ በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. ቆሞስ አባ ኤልያስ የተባሉ አባት ወደ ሥፍራው በመምጣት በቦታው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳትና ቅርሶች እንዲሁም ጽላት እንደሚገኝ፤ ይህንንም ማውጣት እንዲችሉ ከዞኑ የመንግስት አካላት፤ ከሀገረ ስብከቱና ከወረዳው ቤተ ክህነት ፈቃድ ማግኘታቸውን አባ ኤልያስ ይገልጻሉ፡፡ ሀገረ ስብከቱም ሆነ ወረዳ ቤተ ክህነቱ ይህንኑ ያረጋግጣሉ፡፡
ቆሞስ አባ ኤልያስ በዋሻው ውስጥ ቁፋሮ በማካሔድም የአንድ አባት አጽም፤ የእጅ መስቀልና በ984 ዓ.ም. /ከአንድ ሺህ ዓመት በፊት/ የነበረ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽላት አግኝተዋል፡፡ በቦታው የነበረውንም ጸበል ባርከው በርካታ ምእመናንና ኢ-አማንያንን በማጥመቅ እየተፈወሱ እንደሚገኙ ቆሞስ አባ ኤልያስ ይገልጻሉ፡፡ ወደ ሥፍራው በሔድንበት ወቅት ለአራት ዓመታት ሙሉ ሰውነታቸው የማይንቀሳቀስና የአልጋ ቁራኛ የነበሩ አባት ሙሉ ለሙሉ መዳናቸውን በአካል ምስክርነታቸውን ሲሰጡ ተመልክተናል፡፡ በቁጥር 38 የሚሆኑ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች አምነው ለመጠመቅ መቻላቸውንም ቆሞስ አባ ኤልያስ ይናገራሉ፡፡
ጉዳዩ ያሳሰባቸው አንዳንድ ግለሰቦች በቡድን በመሆን ድንጋይ በመወርወርና በመዛት ከቦታው እንዲለቁ ለማድረግ በተለያዩ ጊዜያት ሙከራዎች ማድረጋቸውን ቆሞስ አባ ኤልያስ እና የዓይን እማኞች ያረጋግጣሉ፡፡
ጳጉሜ 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ግን የግለሰቦቹ የኃይል እርምጃ ተጠናክሮ ድንጋይ በመወርወር ቆሞስ አባ ኤልያስን በመደብደብ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሱባቸው ከወረዳው ቤተ ክህነት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ለወረዳው አቅራቢያ ወደሆነ የህክምና መስጫ ጣቢያ በመውሰድም ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ፡፡ ጉዳዩን ለመፍታትና ዘላቂ እልባት ለመስጠትም የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅና የወረዳው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ከሚመለከታቸው የዞኑ የመንግስት አካላት ጋር እየተነጋገሩ እንደሚገኙ ከወረዳው ቤተ ክህነት ያገኘነው የመረጃ ምንጭ ያመለክታል፡፡

new 4

ቅዱስ ፓትርያርኩ የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

ጳጉሜን 4 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

new 4

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ2006 ዓ.ም. አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡

ቅዱስነታቸው እግዚአብሔር ለፍጡራን ከሰጣቸው መልካም ስጦታዎች መካከል የዘመን ስጦታ የመጀመሪያውን ደረጃ እንደሚይዝ በመግለጽ ከ2005 ዓም. ዘመነ ማቴዎስ ወደ 2006 ዓ.ም. ዘመነ ማርቆስ በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል፡፡

አዲሱን ዘመን ሥራ በመሥራት ማሳለፍ እንደሚገባ ሲገልጹም “እያንዳንዱ ሰው ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ በኅሊናው ማቃጨል ያለበት ዓብይ ነገር በሥጋዊም ሆነ በመንፈሳዊ ሓላፊነቴ ምን ሠራሁ፤ ምንስ ቀረኝ? ለአዲስ ዓመትስ ምን ሠርቼ ከእግዚአብሔር ጋር ተባባሪ ልሁን የሚለውን ነው፡፡ ሥራ መሥራት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መተባበር ነውና፡፡ እያንዳንዱ ሰው ይህንን አስተሳሰብ አንግቦ አዲሱን ዘመን በአዲስ መንፈስ ከተቀበለው እውነትም ዘመኑን በሥራ ወደ አዲስነት ይለውጣል፡፡” በማለት ቅዱስነታቸው ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ሁኔታ እየታየ ያለውንና በሕገ ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ወጣቶች ፍልሰትና እልቂትን ለመከላከል ሕዝቡ ልጆቹን ማስተማር እንዳለበትም በመልእክታቸው ጠቁመዋል፡፡
በወሊድ ወቅት ለሞት የሚጋለጡ እናቶችና ሕፃናትን አስመልክቶም በሀገራችን የእናቶችና ሕፃናት ሞት ለመቀነስና ለመከላከል ታስቦ እየታካሔደ ያለውን እንክብካቤ የተሳካ ይሆን ዘንድ ሁሉም ሊደግፈውና በመርሐ ግብሩ ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
     

new 4 1new 4 2

tekelala gu

ማኅበረ ቅዱሳን የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤውን አካሔደ

ነሐሴ 27 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

tekelala gu 

  • ማኅበሩ አዲስ ዋና ጸሓፊ መርጧል፡፡

በማኅበረ ቅዱሳን በየ ስድስት ወሩ አንድ ጊዜ የሚያካሒደውን የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ ከነሐሴ 25 እስከ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. አካሔደ፡፡ የስድሰት ወራት የማኅበሩን የሥራ አፈጻጸም በመገምገም አጽድቋል፡፡

tekelala gu 2በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርትና ሥልጠና ማእከል ለሁለት ቀናት በቆየው መርሐ ግብር የስድስት ወራት የሥራ አመራር ቃለ ጉባኤ ቀርቦ የጸደቀ ሲሆን፣ የሥራ አመራር ጉባኤ ጽ/ቤት፣ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ ጽ/ቤት፣ የኤዲቶሪያል ቦርድ ጽ/ቤትና የኦዲትና ኢንስፔክሽን አገልግሎት ሪፓርቶች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸው ጸድቀዋል፡፡ በተጨማሪም በማእከላት የፋናንስ አያያዝ ፕሮጀክት በ2006 ዓ.ም. ዕቅድና ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ተወያይቷል፡፡

ማኅበሩን በዋና ጸሓፊነት ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲመሩ የነበሩት ዲያቆን ሙሉጌታ ኃይለ ማርያም በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት የአገልግሎት ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው ጠቅላላ ጉባኤው አዲስ ዋና ጸሓፊ መርጧል፡፡ በዚህም መሠረት የልማት ተቋማት አስተዳደር ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩትን አቶ ተሰፋዬ ቢሆነኝን ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት ማኅበሩን በዋና ጸሐፊነት እንዲያገለግሉ መርጧቸዋል፡፡