ነቢዩ ሳሙኤል

ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ወገን ከሆኑት ከአባቱ ሕልቅና እና ከእናቱ ሐና የተወለደው  ሳሙኤል የእግዚአብሔር ነቢይ እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠቅሳሉ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ተጽፏል፤ ‹‹ሕልቅናና ሐናም ማልደው ተነሥተው ለእግዚአብሔር ሰግደው ሄዱ፤ወደ ቤታችውም ወደ አርማቴም ደረሱ፤ ሕልቅናም ሚስቱን ሐናን ዐወቃት፤ እግዚአብሔርም አሰባት፤ ፀነሰችም፡፡ የመውለጃዋም ወራት በደረሰ ጊዜ ሐና ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርስዋም ‹‹ከሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ለምኜዋለሁ›› ስትል ስሙን ‹ሳሙኤል› ብላ ጠራችው፡፡›› (፩ኛሳሙ.፩፥፲፱-፳)

‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ›› (ሉቃ.፳፬፥፵፱)

የሰላም አምላክ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያርግበት ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ›› በማለት ከነገራቸው በኋላ እንዳረገ ቅዱሱ መጽሐፍ ይገልጻል፡፡ (ሉቃ.፳፬፥፵፱) በዕርገቱ ዕለትም ለሐዋርያቱ በገባላቸው ቃል መሠረት ተሰብስበው በአንድነት ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ዕለት ጧት በሦስት ሰዓት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ መጣና የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በሁሉም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ መንፈስ ቅዱስም ባደላቸው መጠን በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መናገር ጀመሩ። (ሐዋ.፪፥፩-፬) ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ ‹‹በዓል ጰራቅሊጦስ›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይከበራል፡

ዕርገት

አምላካችን እግዚአብሔር ምሉዕ በኩለሄ (ሁሉን የሞላና በሁሉም ቦታ የሚኖር) በመሆኑ በባሕርይው መውጣት መውረድ የለበትም::‹ወረደ፣ ተወለደ› ሲባል ፍጽም ሰው መሆኑን የትሕትና ሥራ መፈጸሙን ከመናገር ውጪ ከዙፋኑ ተለየ ማለት እንዳልሆነ ሁሉ ዐረገ ወጣ ሲባልም  ከሰማያዊዉ ዙፋኑ ተለይቶ ነበር ማለት አይደለም::በምድር ላይ ሊሠራ ያለውን ሁሉ መፈጸሙን ያመለክታል እንጂ::ጌታችን በዕርገቱ ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን የተለየበት ጊዜ የለም።ነገር ግን ዕርገቱ በሥጋው የተደረገውን ዕርገቱን ያመለክታል።ይህም ዕርገት ቅዱስ ሥጋው በምድር የስበት ቁጥጥር የማይዘው ለመሆኑ አስረጅ ነዉ።አምላካዊ ሥልጣኑንም ያሳያል።

ጥንተ ስደት

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት እናቱ እመቤታችን ድንግል ማርያም፣ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ወደ ግብፅ የተሰደደበት ዕለት ግንቦት ፳፬ በቅድስት ቤተ ክርስተያናችን ይከበራል፡፡ ጌታችንም በአረጋዊ ዮሴፍ በትር ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ዳግመኛም እመቤታችንና የተወደደ ልጇን መድኃኒዓለምን በእጆቹ ሥራ ይመግባቸው የነበረና እነርሱንም ከኄሮድስ ለማዳን ብዙ ሰማዕትንት የተቀበለ ጻድቁና የ፹፫ ዓመቱ አረጋዊ ዮሴፍ ግብፅ የገባበትና ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ዕለት ነው፡፡

በዓለ ደብረ ምጥማቅ

የክርስተያን ወገን ሁሉ አምላክን የወለደች እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ፡፡

በዓለ ቅዱስ ያሬድ

ኢትዮጵያዊው ሊቅ የዜማ ደራሲ ቅዱስ ያሬድ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተሠወረበት ቀን ግንቦት ፲፩ የከበረ በመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ታከብረዋለች። ይህ ቅዱስ ከአባ ጌዴዎን ዘመዶች ወገን ነው። እርሱም በኢትዮጵያ ሀገር ከታነጹት አብያተ ክርስቲያናት ለምትቀድም ከአክሱም ካህናት ውስጥ ነው፡፡ እርሷም አስቀድሞ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት በውስጥዋ የተከበበና አምላክን በወለደች በእመቤታችን በከበረች ድንግል ማርያም ስም የከበረች ናት::

ዕረፍቱ ለቅዱስ አትናቴዎስ

ቅዱስ አትናቴዎስ የተወለደው ግብጽ ውስጥ እስክንድርያ ነው:: ሐናፊ ከሚባል የእስላም ነገድና ከአረማውያን ወገን በመሆኑ በልጅነቱ ክርስትናን መማር አልቻለም ነበር::አንድ ቀን ግን ክርስቲያን ሕፃናት እርስ በእርሳቸው እየተጫወተ ተመለከተ። ጨዋታቸውም የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በመሥራት ስለነበር ከመካከላቸው ዲያቆናትንና ኤጲስ ቆጶሳትን ሲመርጡ እንዲያጫውቱት ለመናቸው። ነገር ግን ‹‹አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋር አትደመርም›› በማለት ከለከሉት፡፡አትናቴዎስም ‹‹ክርስቲያን እሆናለሁ›› ባላቸው ጊዜ ሕፃናቱ ደስ ተሰኝተው ማዕረጋቸውን ለመለየት ዕጣ ተጣጣሉ::ለአንዱ ቄስ፣ ለአንዱም ዲያቆን መሆን ሲደርሳቸው ለአትናቴዎስ ፓትርያርክ መሆን ስለ ደረሰው ሌሎቹ ሕፃናት ይሰግዱለት ጀመር::…

ልደታ ለማርያም

በግንቦት አንድ ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች። እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡

ቅዱስ ማርቆስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ምሕረት፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችን ተበሥሮልን ከዛሬ ዕለት ደረስን! በቸርነቱ ለዚህ ያደረሰን ፈጣሪ ይመስገን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላቸሁ የወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስን ታሪክ ነው፡፡

ምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም

ምስካዬ ኀዙናን መድኃኒዓለም በታሪካዊ ሂደቱና በአገልግሎቱ የተለያዩ ሥራዎችን በመጀመር ለሌሎች ቤተ ክርስቲያናት አርአያ የሆነ ገዳም ነው፡፡