‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)

ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡…ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡

በዓለ ቅድስት ሥላሴ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? አሜን! የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን! በዓለ ቅድስት ሥላሴን በተመለከተ አጭር ጽሑፍ አቅርበንላችኋል፤

ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አባቶቻችን ሐዋርያትን ሰማዕትነት በተቀበሉበት ቀናት በዓላት ሰይማ ታከብራቸዋለች፡፡ እንዲሁም በስማቸው የተሰየመውን ጾም በመጾም አሠረ ፍኖታቸውን ይከተሉ ዘንድ ምእመናንን ታሳስባለች፡፡ በሐምሌ ፭ ቀን ደግሞ የደጋጎቹን ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስን በዓል ታደርጋለች፡፡ የእነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን በዓል መደረጉ በአንድ ቀን ሰማዕትነት በመቀበላቸው ነው፡፡

አማናዊቷ መቅደስ!

የገሃነም ደጆች የማይችሏት ምን ቢጥሩ፣

እንዳትፈርስ አነጻት በይቅርታና በፍቅሩ፡፡

መሰብሰቢያ እንድትሆን ለአምልኮ መፈጸሚያ፣

ሕንጻዋንም ሲመሠርት በምድር ላይ መጀመሪያ፡፡

በተአምራት በእናቱ ስም  በሦስት አዕባን አቆመ፣

የአማናዊቷን መቅደስ ምሳሌዋን በራሷ ስም ሰየመ፡፡

በጴጥሮስ ዐለትነት በገባው ቃል እንደሚሠራት፣

መቅደሱን በእናቱ ስም በፊሊጵሲዩስ አቆማት፡፡

ከቅዱሳኑ ከምርጦቹ ከድንግል ከተቋሙ፣

የሚዘከሩበት ወዳጆቹ የሚጠራበትን  ቅዱስ ስሙ፣

ይድረሰው ግናይ ውዳሴ ለሰጠን መሥርቶ በደሙ!

‹‹ይፈኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ፤ አጽናኝ መንፈስ ይልክላችኋል›› (ዮሐ.፲፬፥፲፮)

የቤዛነት ሥራውን ከፈጸመ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ሲያርግ ለሐዋርያት የሰጣቸው ተስፋ አጽናኝና የእውነት መንፈስ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን አብ እንደሚልክላቸው፣ እርሱም አጽናኝ የሆነ ጰራቅሊጦስ እንደሆነ ለዘለዓለሙም ከእነርሱ ጋር እንደሚሆን ነግሯቸው ነበር፡፡ ጌታችን እንደተናገረውም በሰጣቸው ተስፋ መሠረት ባረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሣ ደግሞ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡

ርኅሩኁና የይቅርታ መልአክ

የርኅራኄ መዝገብ፣ ትሑት፣ ታዛዥና ለዘለዓለም ፈጣሪውን አመስጋኝ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ጌታ በሚያደርገው ቸርነት ላይ ለሰው አንድ ወገን የሚሆን መልአክ ነው፡፡ (ሄኖ.፮፥፭፣፲፪፥፭፣፲፥፲፪)

ማኅቶት!

ለጨለመው ሕይወት ሆኖለት ማኅቶት፣
በብርሃኑ ጸዳል ሰውሮት ከጽልመት ፡፡
የክህነትን ሥልጣን፣ ሥጋውና ደሙን ፣ የንስሐን መንገድ፣
በፍቅሩ ለግሶ መዳንን ለሚወድ፡፡

ያናገረው ትንቢት የሰጠው ምሳሌ፣ በአማን ተፈጽሞ፣
በይባቤ መልአክ በዕልልታው ደግሞ፣
እያለ ከፍ ከፍ ረቆ ያይደለ! እያዩት በርቀት፣
ዐረገ ወደ ላይ ወደ ክቡር መንበሩ ሰማየ ሰማያት፡፡

የአምላክ እናት መገለጥ!

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ‹‹በዓለ ደብረ ምጥማቅ›› አደረሳችሁ!

አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለ መታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁላችንም ታላቅ በዓልን እናደርጋለን።

‹‹ታመመ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ›› (የዘወትር ጸሎት)

ጌታ ሰው በመሆኑ የሰውን ልጅ ከኃጢአት፣ ከሞት እና ከሰይጣን ባርነት ነጻ አወጣው። እነዚህ ድል የተነሡትም ፍጹም እስከ መስቀል ሞት በደረሰ መታዘዝ፣ ቅዱስ በሆነ ሕማሙ፣ አዳኝ በሆነ ሞቱና፣ በትንሣኤው ኃይል ነበር።

‹‹እባክህ አሁን አድነን!››

ግሩም አምላክ በትሕትና ከተገለጠባቸው ዕለታት አንዱ የሆነው ድንቅ ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን‹‹ሆሣዕና››በመባል ይታወቃል፡፡ሆሣዕና መተርጉማነ አበው በአንድምታቸው‹‹ሆሣዕና በአርያም በሰማይ ያለ መድኃኒት››ብለው ተርጒመውልናል፤