የስድስተኛው ፓትርያርክ ቅድመ ምርጫ ሂደቶች

የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን ከምርጫው በፊት ሊከናወኑ የሚገባቸው ተግባራት በአስመራጭ ኮሚቴው እየተመራ ይገኛል፡፡ ሂደቱንም አስመራጭ ኮሚቴው ባወጣው መርሐ ግብር መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ አድባራትና ገዳማት፤ ከቤተ ክርስቲያናት፤ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ ከምእመናን፤ እንዲሁም ከውጭ ሀገራት በመራጭነት የተወከሉ መራጮች ከየካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

 

የካቲት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ መራጮች ከየሀገረ ስብከታቸው በመራጭነት መወከላቸውን የሚገልጽ ማስረጃ በመያዝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ የተገኙ ሲሆን በአስመራጭ ኮሚቴው በምርጫው ሂደት ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ መራጮችን በአግባቡ መመዝገብ እንዲቻል በምድብ እና በምድብ በመመደብ ምዝገባውን በማካሔድ የመራጭነት ካርዳቸውን ወስደዋል፡፡

የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ሁሉም መራጮች ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በጠቅላይ ቤተ ክህነት በመገኘት በምርጫው አካሔድ ላይ ሰፋ ያለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል በአስመራጭ ኮሚቴው ማብራሪያዎች ተሰጥተዋል፡፡ ማብራሪያውን የሰጡት የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ እና የአስመራጭ ኮሚቴው ሕዝብ ግንኙነት አቶ ባያብል ሙላቴ ናቸው፡፡

 

ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ ባስተላለፉት መልእክትም  “ቤተ ክርስቲያንን የሚመሩ አባት ለመምረጥና ምርጫውን ለማካሔድ አደራ ተሸክማችሁ የመጣችሁ በመሆኑ ምርጫውን በራሳችሁ ፈቃድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነጻ ሆናችሁ ቤተ ክርስቲንን ሊመሩ ይችላሉ የምትሏቸውን አባት እንድትመርጡ” ብለዋል፡፡ ለመራጮቹም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የሆነውንና ከአስመራጭ ኮሚቴው የቀረቡለትን አምስቱን ሊቃነ ጳጳሳት ተወያይቶ በእጩነት ለፓትርያርክነት  ለምርጫ ማቅረቡን የሚገልጸው ውሳኔ አንብበዋል፡፡

 

የአስመራጭ ኮሚቴው ሕዝብ ግንኙነት አቶ ባያብል ሙላቴ በሰጡት ሰፋ ያለ ማብራሪያም ”የምርጫውን ካርድ ካልያዛችሁ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት መግባት አትችሉም፡፡ ስለዚህ የምርጫ ካርዱን በጥንቃቄ መያዝ ይገባችኋል፡፡ ቢጠፋም ምትክ አንሰጥም” ያሉ ሲሆን የምርጫ ካርድ የያዙትም ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ ተጠቃለው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ በመገኘት እነሱን ለማስተናገድ በተመደቡ አገልጋዮች አማካይነት ካርዳቸውንና ማንነታቸውን ከተመዘገበው መዝገብ ላይ በማመሳከር የምርጫ ካርዱን በማስረከብ በተዘጋጀለት ሳጥን ውስጥ እንዲገባ ከተደረገ በኋላ የምርጫ ወረቀቱን በመቀበል ወደ አዳራሽ ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረግ አብራርተዋል፡፡

 

አቶ ባያብል ሙላቴ ማብራሪያቸውን በመቀጠል “ከጧቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ከአቃቤ መንበረ ፓትርያርኩ ጋር በመገኘት እንዲሁም ታዛቢዎች በተገኙበት በአቃቤ መንበረ ፓትርያርኩ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል አማካይነት መራጮች ቃለ መሐላ ይፈጽማሉ” ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ቃለ መሐላው ከተፈጸመ በኋላ ለመምረጥ ለእያንዳንዱ ቃለ መሐላ ለማስገባት እንደማይቻል ያስገነዘቡ ሲሆን “ደክማችሁ እንዳትመለሱ በሰዓቱ እንድትገኙ” በማለት ገልጸዋል፡፡

 

የምርጫ ወረቀቱ ምን እንደሚመስል ለመራጮች በግልጽ በማሳየት አቶ ባያብል ሙላቴ በሰጡት ማብራሪያም የአምስቱም እጩ ፓትርያርኮች ፎቶ ግራፍና ስም ጵጵስና በተሾሙበት ጊዜ ቅደም ተከተል መቀመጡን፤ መራጮችም በሚፈልጉት  እጩ ፓትርያርክ ፊት ለፊት ከፎቶ ግራፋቸው ትይዩ  ባለው ሳጥን መሰል ቦታ ውሰጥ አንድ ጊዜ ብቻ የ ምልክት በማድረግ ወረቀቱን አራት ቦታ በማጠፍ በተዘጋጀው ባለ መስታወት የምርጫ ሳጥን ውስጥ እንዲከትቱ በማሳሰብ ከ ምልክቱ ውጪ የምርጫ ወረቀቱ ላይ ምንም አይነት ምልክት ወይም ጽሑፍ መጻፍ እንደማይፈቀድና ተጽፎ ቢገኝ የምርጫ ወረቀቱ እንደሚሰረዝ  አሳስበዋል፡፡

 

ምርጫው ከተጠናቀቀ በኋላ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የምርጫው ታዛቢዎችና መራጮች ባሉበት በይፋ ሳጥኑ ተከፍቶ ቆጠራ እንደሚካሔድና ከፍተኛ ድምጽ ያገኙት አባት እዚያው አዳራሹ ውስጥ ሁሉም ባለበት ፓትርያርክ ሆነው መመረጣቸውን እንደሚያበስሩ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ሁለት አባቶች ተመሳሳይ ድምጽ ቢያገኙ በዕጣ እንደሚለዩ ገልጸዋል፡፡

ytenaten 058

አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ታወቁ

የካቲት 19 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ


ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ÷ አስመራጭ ኮሚቴ ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ÷ አምስቱ እጩ ፓትርያርኮችን ይፋ አደረገ፡፡

ytenaten  058ዛሬ ከስዓት በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ የአስመራጭ ኮሚቴ አባላት፣ እንዲሁም ከልዩ ልዩ የሚዲያ አካላት የተወከሉ ጋዜጠኞች በተገኙበት በተሰጠው መግለጫ ላይ፡-ብፁዕ አቡነ ማትያስ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የምዕራብና ደቡብ አዲስ አበባ የከፋ ሸካ ቤንች ማጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የወላይታና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለፓትርያርክነት እጩ ሆነው መቅረባቸው ተገልጧል፡፡

 

በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ አማካኝነት የቀረበው መግለጫ “መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን በዕጩነት ከቀረቡት ብፁዓን አባቶች መካከል ለመንጋው እረኛ እግዚአብሔር አምላክ እንዲሰጠን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ በጾምና በጸሎት ፈጣሪያቸውን እንዲጠይቁ” አሳስቧል፡፡ ከመግለጫው በኋላ ከጋዜጠኞች ለተነሡ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡

hawire ticket

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ሊካሔድ ነው

የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

hawire ticket

ማኅበረ ቅዱሳን በ2005 ዓ.ም. የሐዊረ ሕይወት /የሕይወት ጉዞ/ የተሰኘውና ወደ ቅዱሳን መካናት፤ አድባራትና ቤተ ክርስቲያናት የሚያካሄደውን የጉዞ መርሐ ግብር በሆለታ ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን መጋቢት 22 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደሚያካሄድ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ገለጹ፡፡

hawire 1

 

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በ2003 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን ለአራተኛ ጊዜ እንደሚከናወን የገለጹት ምክትል ዋና ጸሐፊው የትኬት ሽያጩንም ከሰኞ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በማኅበሩ የንዋያተ ቅድሳትና የኅትመት ውጤቶች መሸጫ ሱቆች፤ እንዲሁም በማኅበሩ ዋና ጽሕፈት ቤት እንደሚጀመር፤ የቲኬት ሽያጩንም ከጉዞው አሥር ቀን ቀደም ብሎ እንደሚጠናቀቅና በጉዞውም ከዚህ በፊት በተከታታይ ከተደረጉት ጉዞዎች በላቀ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ምእመናን ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ምእመናን አሳባቸውን ሰብስበው በተረጋጋ መንፈስ ሆነው ከበረከቱ ይሳተፉ ዘንድ የአጽዋማት ወቅቶች የተሻሉ በመሆናቸው ጉዞው መዘጋጀቱን አብራርተዋል፡፡

 

የጉዞውን ጠቀሜታ ሲገልጹም “ትልቁ ጠቀሜታው  ምእመናን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ዙሪያ ያሏቸው ጥያቄዎች ከታላላቅ ሊቃውንት መልስ የሚያገኙበት፤ እንዲሁም  የወንጌል ትምህርት ለምእመናን በስፋት የሚሰጥበት ነው” ብለዋል፡፡

 

hawire 2ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ  በደብረ ጽጌ ቅድስት ማርያም ገዳም፤ በፍቼ ቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን፤ እንዲሁም በበኬ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ምእመናን ከወዲሁ ትኬቱን በብር 120፡00 /አንድ መቶ ሃያ/ በመግዛት በጉዞው እንዲሳተፉ የማኅበሩ ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ማዕከሉ ዐውደ ጥናት ሊያካሂድ ነው

የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ


የጥናትና ምርመር ማዕከል በሁለት ታላላቅ ርእሶች ላይ ያዘጋጀውን ዐውደ ጥናት  የካቲት 23 ቀን 2005 ዓ.ም በብሔራዊ ሙዚየም አዲሱ አዳራሽ ውስጥ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡

 

የጥናትና ምርምር ማዕከሉ ምክትል ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰይፉ አበበ  ለመካነ ድራችን በሰጡት መገለጫ “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን፣ የዓድዋ ድልና አንድምታው፤ እንዲሁም በጦርነቱ የተዘረፉ ቅርሶችን ከማስመለስ አንጻር የቤተ ክርስቲያኒቷ ድርሻ በሚሉ ሁለት ርዕሶች ላይ ትኩረት አድረጎ የሚቀርብ ነው፡፡” ካሉ በኋላ የዐውደ ጥናቱ የትኩረት አቅጣጫዎችን ሲጠቁሙ “ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት እንዳትገዛ፣ ነጻነቷ የተጠበቀ ሉአላዊት ሀገር እንድትሆን ከጦርነቱ ጀምሮ እስከ ድሉ የነበራትን ሚና፣ እንዲሁም በዓድዋና በማይጨው በልዩ ልዩ ጊዜያት በወራሪዎች የተዘረፉ ቅርሶችን ከማስመለስ አንጻር የቤተ ክርስቲያኒቱ ድርሻን ማመላከት የጥናቱ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው፡፡” ብለዋል፡፡

 

በስተመጨረሻም ምክትል ዳይሬክተሩ ሁሉም ምእመናን ቅዳሜ የካቲት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ጀምሮ በሚከናወነው በዚሁ ዐውደ ጥናት ላይ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር እሁድ ይጀምራል

የካቲት  13 ቀን 2005 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስ

በማኅበረ ቅዱሳን ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል እየተዘጋጀ የሚቀርበው የቴሌቪዥን መርሐ ግብር እሑድ የካቲት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3፡30 – 4፡00 ሰዓት ድረስ በናይል ሳት ኢቢኤስ ላይስርጭቱን እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡

ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የቴሌቪዥን ስርጭቱ እንደሚጀመር ብንዘግብም በኢቢኤስ የስርጭት መቋረጥ ምክንያት ሳይተላለፍ መቆየቱ ያታወሳል፡፡ በአሁኑ ወቅት  በኢቢኤስ ላይ የተከሰቱት ችግሮች የተቀረፉ በመሆናቸው በየሳምንቱ እሁድ ከጠዋቱ 3፡30 – 4፡00 ሰዓት ፤ እንዲሁም በድጋሚ በየሳምንቱ ሐሙስ ከጠዋቱ 1፡00 – 1፡30 ሰዓት የሚተላለፍ መሆኑን የቴሌቪዥን ክፍሉ አስተባባሪ የሆኑት ዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ ገልጸዋል፡፡

በምእመናን በጉጉት ይጠበቅ የነበረው ይህ መርሐ ግብር በተደጋጋሚ በተከሰተው ችግር ምክንያት በመቋረጡ ዝግጅት ክፍሉ ይቅርታ እየጠየቀ ከእሑድ የካቲት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ መከታተል እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡

DSC09260

የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ ሁሉም በጸሎት እንዲያስብ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለፓትርያርክነት እጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

አስመራጭ ኮሚቴው በአንድ ሳምንት ውስጥ አከናወንኳቸው ያላቸውን ሥራዎች ባቀረበበት በዚሁ መግለጫ በርካታ ምእመናን ለቤተ ክርስቲያኒቱ 6ኛ ፓትርያርክ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉትን አባት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በፋክስ መልእክት በመላክ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጧል፡፡ ከካህናትና ምእመናን የተገኘው ጥቆማም ለአስመራጭ ኮሚቴው በግብአትነት የሚያገለግል ሲሆን ከየካቲት 9 -14 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያቀርብ መግለጫው አመልክቷል፡፡ የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ካህናትና ምእመናን እግዚአብሔርን በጸሎት እንዲጠይቁ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ አስመራጭ ኮሚቴው ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡

ከጋዜጠኞች ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል ምርጫው ከሌሎች ተጽእኖ ምን ያህል የፀዳ ነው? የሚለውን ለቀ ማዕምራን ፋንታሁን ሙጬ የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ምላሽ የሰጡ ሲሆን አስመራጭ ኮሚቴው ከሌሎች አካላት ተጽእኖ የጸዳና ራሱን ችሎ የተሰጡትን ኃላፊነቶች በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡  የአኀት ቤተ ክርስቲያንና የሲቪክ ማኅበራት ምርጫውን ለመታዘብ ይገኛሉ? የሚለውን ሲመልሱም ከአኀት ቤተ ክርስቲናት፤ ከአለም አብተ ክርስቲናት ምክር ቤት፤ ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ ከታዋቂ አገር ሽማግሌዎችና ከመንግስት አካላት በታዛቢነት እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

በስፋት ጥቆማ እየሰጡ የሚገኙት የአዲስ አበባ ካህናትና ምእመናን ናቸው፡፡ ሌሎቹ አህጉረ ስብከቶችስ? በሚል ለቀረበው ጥያቄም ሲመልሱ “በርቀት ምክንያት በአካል መቅረብ ያልቻሉ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ ላይ ሁለት ፋክስ ቁጥሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ ፋክሶቹም 24 ሰዓት በመስራት ከአውሮፓና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጥቆማዎችን እንደተቀበሉና በአካል ቀርበው ጥቆማቸውን የሚሰጡትንም በተዘጋጀው ቅጽ ላይ ሞልተው በታሸገው የጥቆማ መስጫ ሳጥን ውስጥ እያስገቡ ይገኛሉ” ብለዋል፡፡

በፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ ላይ እጩ የሚሆኑትን አባቶች ከተለዩ በኋላ ከምእመናን የሚቀርቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ለመቀበል የ15 ቀናት የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን አስመራጭ ኮሚቴው የገለጸው በሦስት ቀናት ልዩነት ፓትርያርክ ሆነው የሚመረጡት አባት እንደሚታወቁ ነው፡፡ ይህ አካሔድ ከሕገ ደንቡ ጋር አይጋጭም? የሚለውንም ሲመልሱ “ከምርጫ ሕገ ደንቡ ጋር ተያዞ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጸድቆ ለአስመራጭ ኮሚቴው የተሰጠ ተጨማሪ ሕግ አለ፡፡ አስመራጭ ኮሚቴውን በሚያስመርጥበት ወቅት ኮሚቴው ሊሰሯቸው የሚገባውን ተግባራት ቋሚ ሲኖዶስ እየተከታተለ አስፈላጊውን ለውጥ ማድረግ እንደሚችል የተገለጸበት ሕግ ነው፡፡ ይህንን ሕግ ተከትሎ የድርጊት መርሐ ግብር አዘጋጅቶ ነው አስመራጭ ኮሚቴው ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀረበው፡፡  ቋሚ ሲኖዶስ የቅዱስ ሲኖዶስም ምልዓተ ጉባኤ በሰጠው ሥልጣንና ውክልና መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ያቀረበውን የጊዜ ሰሌዳ ትክክል ነው ብሎ አጽድቆ ሰጥቶታል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ሕግ የማውጣትም ሆነ ሕግ የመለወጥ ስልጣን የለውም” በማለት የመለሱ ሲሆን ስለቀኑ ማጠር ሲያብራሩም ወደ አብይ ጾም የተቃረበ በመሆኑ ከዚያ በፊት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ግንዛቤ ተወስዶ እንደተከናወነ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ከ53ቱም አህጉረ ስብከቶች ለመራጭነት ይገኛሉ ተብሎ ይፋ የተደረገው 800 መራጮች ብቻ ናቸው ፡፡ ነገር ግን ሲሰላ ከዚያ በላይ ስለሚሆኑ እንዴት ይታያል? በማለት ለቀረበው ጥያቄም በፓትርያርክ ምርጫው ላይ በመራጭነት የሚሳተፉ ሰዎች 800 ይሆናል የሚለውም እንደ መነሻ የተያዘ እንጂ የመጨረሻ ቁጥር ያለመሆኑን ያብራሩ ሲሆን የአስመራጭ ኮሚቴው አባላትም ከጋዜጠኞች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተጨማሪ ምላሽ በመስጠት ተሳትፈዋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክን ጨምሮ 13ቱም አስመራጭ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል፡፡

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የካቲት 18 ቀን አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ለምእመናን በይፋ እንደሚገለጹ፤ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ የተመረጡት ፓትርያርክ በመገናኛ ብዙሃን እንደሚገለጽና የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. በዓለ ሲመት እንደሚከናወን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

የካቲት 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስሰ


DSC09260

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለፓትርያርክነትእጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

 

አስመራጭ ኮሚቴው በአንድ ሳምንት ውስጥ አከናወንኳቸው ያላቸውን ሥራዎች ባቀረበበት በዚሁ መግለጫ በርካታ ምእመናን ለቤተ ክርስቲያኒቱ 6ኛ ፓትርያርክ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉትን አባት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በፋክስ መልእክት በመላክ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጧል፡፡ ከካህናትና ምእመናን የተገኘው ጥቆማም ለአስመራጭ ኮሚቴው በግብአትነት የሚያገለግል ሲሆን ከየካቲት 9 -14 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያቀርብ መግለጫው አመልክቷል፡፡ የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ካህናትና ምእመናን እግዚአብሔርን በጸሎት እንዲጠይቁ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡  እጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

 

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ አስመራጭ ኮሚቴው ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡

 

ከጋዜጠኞች ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል ምርጫው ከሌሎች ተጽእኖ ምን ያህል የፀዳ ነው? የሚለውን ለቀ ማዕምራን ፋንታሁን ሙጬ የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ምላሽ የሰጡ ሲሆን አስመራጭ ኮሚቴው ከሌሎች አካላት ተጽእኖ የጸዳና ራሱን ችሎ የተሰጡትን ኃላፊነቶች በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡  የአኀት ቤተ ክርስቲያንና የሲቪክ ማኅበራት ምርጫውን ለመታዘብ ይገኛሉ? የሚለውን ሲመልሱም ከአኀት ቤተ ክርስቲናት፤ ከአለም አብተ ክርስቲናት ምክር ቤት፤ ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ ከታዋቂ አገር ሽማግሌዎችና ከመንግስት አካላት በታዛቢነት እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

 

በስፋት ጥቆማ እየሰጡ የሚገኙት የአዲስ አበባ ካህናትና ምእመናን ናቸው፡፡ ሌሎቹ አህጉረ ስብከቶችስ? በሚል ለቀረበው ጥያቄም ሲመልሱ “በርቀት ምክንያት በአካል መቅረብ ያልቻሉ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ ላይ ሁለት ፋክስ ቁጥሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ ፋክሶቹም 24 ሰዓት በመስራት ከአውሮፓና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጥቆማዎችን እንደተቀበሉና በአካል ቀርበው ጥቆማቸውን የሚሰጡትንም በተዘጋጀው ቅጽ ላይ ሞልተው በታሸገው የጥቆማ መስጫ ሳጥን ውስጥ እያስገቡ ይገኛሉ” ብለዋል፡፡

 

በፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ ላይ እጩ የሚሆኑትን አባቶች ከተለዩ በኋላ ከምእመናን የሚቀርቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ለመቀበል የ15 ቀናት የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን አስመራጭ ኮሚቴው የገለጸው በሦስት ቀናት ልዩነት ፓትርያርክ ሆነው የሚመረጡት አባት እንደሚታወቁ ነው፡፡ ይህ አካሔድ ከሕገ ደንቡ ጋር አይጋጭም? የሚለውንም ሲመልሱ “ከምርጫ ሕገ ደንቡ ጋር ተያዞ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጸድቆ ለአስመራጭ ኮሚቴው የተሰጠ ተጨማሪ ሕግ አለ፡፡ አስመራጭ ኮሚቴውን በሚያስመርጥበት ወቅት ኮሚቴው ሊሰሯቸው የሚገባውን ተግባራት ቋሚ ሲኖዶስ እየተከታተለ አስፈላጊውን ለውጥ ማድረግ እንደሚችል የተገለጸበት ሕግ ነው፡፡ ይህንን ሕግ ተከትሎ የድርጊት መርሐ ግብር አዘጋጅቶ ነው አስመራጭ ኮሚቴው ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀረበው፡፡  ቋሚ ሲኖዶስ የቅዱስ ሲኖዶስም ምልዓተ ጉባኤ በሰጠው ሥልጣንና ውክልና መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ያቀረበውን የጊዜ ሰሌዳ ትክክል ነው ብሎ አጽድቆ ሰጥቶታል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ሕግ የማውጣትም ሆነ ሕግ የመለወጥ ስልጣን የለውም” በማለት የመለሱ ሲሆን ስለቀኑ ማጠር ሲያብራሩም ወደ አብይ ጾም የተቃረበ በመሆኑ ከዚያ በፊት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ግንዛቤ ተወስዶ እንደተከናወነ ገልጸዋል፡፡

 

በመጨረሻም ከ53ቱም አህጉረ ስብከቶች ለመራጭነት ይገኛሉ ተብሎ ይፋ የተደረገው 800 መራጮች ብቻ ናቸው ፡፡ ነገር ግን ሲሰላ ከዚያ በላይ ስለሚሆኑ እንዴት ይታያል? በማለት ለቀረበው ጥያቄም በፓትርያርክ ምርጫው ላይ በመራጭነት የሚሳተፉ ሰዎች 800 ይሆናል የሚለውም እንደ መነሻ የተያዘ እንጂ የመጨረሻ ቁጥር ያለመሆኑን ያብራሩ ሲሆን የአስመራጭ ኮሚቴው አባላትም ከጋዜጠኞች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተጨማሪ ምላሽ በመስጠት ተሳትፈዋል፡፡

 

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክን ጨምሮ 13ቱም አስመራጭ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል፡፡

 

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የካቲት 18 ቀን አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ለምእመናን በይፋ እንደሚገለጹ፤ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ የተመረጡት ፓትርያርክ በመገናኛ ብዙሃን እንደሚገለጽና የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. በዓለ ሲመት እንደሚከናወን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

te 2

ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ መረጃዎችን የመስጠት አቅሟን ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቆመ

የካቲት 5 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

te 2በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል አስተባበሪነት “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስስቲያን ተልዕኮ በሉላዊቷ ዓለም እና በዘመናዊው ማኅበረሰብ” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀረበ፡፡

 

በማኅበሩ ሕንፃ ውስጥ የካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ጥናታዊ ጽሑፉን ያቀረቡት አቶ ፋንታሁን ዋቄ ሲሆኑ ቀሲስ ዶክተር ደረጀ ሺፈራው መርሐ ግብሩን መርተውታል፡፡ አቶ ፋንታሁን ዋቄ በጥናታቸው ላይ ዘመናዊነትና መዘመን ምንድነው? ዘመናዊነትና መዘመን ለዓለማውያንና ለኦርቶዶክሳዊያን ክርስቲያኖችምን የተለየ ትርጉም ይኖረዋል? የዓለም ተለዋዋጭነት /Dynamizm/ ፍጥነት መገንዘብ፤ ለኦርቶዶክሳዊው ክርስትና ሉላዊነት ምን ይጠቅማል? የቤተ ክርስቲያን መዘመን እንዴት፤ ለምን? በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ ሰፊ ትንታኔ ሰጥተዋል፡፡

 

ጥናት አቅራቢው ዘመናዊነትን “ስፋትና ጥልቀት ያላቸው ኢኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ፤ ፖለቲካዊና ባሕላዊ የለውጥ ሂደቶች ድምር ውጤት የሆነ የኅብረተሰብ ለውጥ ነው በማለት ይሞግታሉ፡፡ ስለዚህ ዘመናዊነት አዲስነት፤ ያለፈውን መተው፤ መለወጥ፤ አሁን የተሻለ የሚሰኘውን ማድረግና መሆን”ተብሎ ሊተረጎም ይችላል በማለት የጠቀሱ ሲሆን በመንፈሳዊው እይታ ኅብረተሰብ በፈጣሪ ፈቃድ መኖር የሚገባውና በምድር ላይ የእግዚአብሔር መንግሥት መገለጫ ምሳሌ የሆነ አኗኗር ሊኖረው ያስፈልጋል፡፡ኅብረተሰብ ዘመነ ሲባልም ከዚህ አንጻር ሊታይ እንደሚገባው ገልጸዋል፡፡ዘመናዊነት ሦስት መልክ አለው ይላሉ፡፡ ማለትም በአስተሳሰብ /አዕምሯዊና መንፈሳዊ/ ፤ በአኗኗር እና በአዕምራዊ ጥበብ በሚገኝ ቁሳዊ ውጤት መራቀቅ ተብሎ ሊለካ ፤ሊተነተን እንደሚችል ያብራሩ ሲሆን አያይዘውም የቤተ ክርስቲያን መዘመንን መለኪያ ሲተነትኑ “በየትውልዱና በየዘመኑ የሰው ልጅ ሕገ እግዚአብሔርን የሚጻረር አስተሳሰብ ፤እምነትና አኗኗርን በመተው ክርስቶስን ወደ መምሰል ሕይወት እንዲመጣ በቴክኖሎጂ፤ በተቋም አቅም በአስተዳደር ወዘተ ይህንን ተልዕኮ ለማስፈጸም በሚያስችል ደረጃ መዘጋጀት የአፈጻጸም ዘመናዊነት ሊባል ይችላል፡፡” በማለት በጥናታቸው አመልክተዋል፡፡

 

ሴኩላር ሂዩማኒዝም/ዓለማዊነት/ በተመለከተም  ሲያብራሩ “በእግዚአብሔር መኖር ከማያምን ሳይንሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ የሚመነጭ የኑሮ ፍልስፍና አኗኗር ነው፡፡መሠረቱም የዳርዊን የዝግመተ ለውጥ ሳይንስና በኒውተን የተፈጥሮ ሳይንስ መንጭቶ የመንፈሳዊው ዓለም መኖርን የማይቀበል ትምህርት ሲሆን፤ ዘመናዊው ማኅበራዊ ሳይንስ የዚህ ማእቀፈ እሳቤ ሰለባ ነው፡፡ በዛሬው ዓለም መዘመን እጅጉን የተቆራኘው ከሴኩላር ሂውማኒዝም/ዓለማዊነት/ ጋር ነው፡፡ ሥልጣኔ ፤እድገት፤ መሻሻል፤ ማወቅ፤ ሰው መሆን ሁሉ በሴኩላር ሂውማኒዝም ማዕቀፈ አሳቤ የሚመራ በመሆኑ መደበኛ ትምህርት ፤ ዘመናዊው ሥርዓተ መንግሥት ፤ የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት፤ የአስተዳደር መመሪያ ሁሉ በሴኩላር ሂዩማኒዝም መሥፈርት የሚመዘን ነው” በማለት ይገልጹታል፡፡

 

የሉላዊነት አጀማመርን በተመለከተም እንደየ ማዕቀፈ እሳቤው ወይም መሠረተ ፍልስፍናው ዘመን መነሻ እንደሚለያይና የሕገ እግዚአብሔር ሉላዊነት ለአዳም በኤደን የተሰጠችው ብቸኛዋ ሉላዊሕግ እንደነበረችየገለጹት የጥናቱ አቅራቢ አቶ ፋንታሁን ክርስትናም በዚህች በተከፋፈለች ዓለም ውስጥ ሉላዊ ሕግ ትሆን ዘንድ በጌታችን ዓለምን ሁሉ ደቀ መዛሙርቴ አድርጉ ብሎ ባዘዘ ጊዜ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

 

አቶ ፋንታሁን በጥናታቸው መዘመንን በክርስቲያናዊ ትምህርትና መዘመን በሴኩላር ሂዩማኒዝም እይታ ያላቸውን ልዩነቶችን በማነጻጸርና በመተንተን ያቀረቡ ሲሆን በተለይም ሃይማኖት የሰዎችን ራስን የመግለጽ ዝንባሌ በማገድ ልማትና እድገት ላይ እንቅፋት ይሆናል፤ መንፈሳዊነት ሲጸና ድህነት ይሰፍናል በሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ ሴኩላር ሂዩማኒዝም /ዓለማዊነት/ መንፈሳዊነትን እንደሚዋጋ አብራርተዋል፡፡

 

የዘመነው ሴኩላር ሂዩማኒዝም ቤተ ክርስቲያንን ለመዋጋት ቴክኖሎጂን፤ ኢኮኖሚን፤ ትምህርትን፤ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ፤ የመንግሥታትte 1 ሕጎችን፤ መገናኛ ብዙኀንን በትጋት በመጠቀም ላይ እንደሚገኝና ፤በአንጻሩ ቤተ ክርስቲያን ከእነዚህ ተቋማትና ቴክኖሎጂዎች ራሷን በማግለል ትጠቃለች፡፡ይህንን ጥቃት ለመቀልበስ ቤተ ክርስቲያን ተገዳዳሪ ሉላዊ ኃይል ለማድረግ በተለያዩ አውዶች በተሰሚነትና በከፍተኛ አቅም ለማሳተፍ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ በመግለጽ የጥናታቸውን ማጠቃለያ ያሉትን  አቅርበዋል፡፡ ባቀረቡት ማጠቃለያም ክርስትና ሉላዊ ሆኖየሚቀጥለው የቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ማዕቀፈ እሳቤ ክርስቶሳዊ ማድረግና ማእቀፈ አሳቤውን የሚገልጽ አኗኗር ተግባራዊ ማድረግ፤ በማንኛውም የዘመናዊ ትምህርት የሚያድጉ የቤተ ክርስቲያን ልጆቿ በቂ የሆነ ክርስቲያናዊ ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ፤ ራሷን በመሠረታዊ ፍላጎቶች በመቻልና ከጥገኝነት የማላቀቅ ዕድሎችን ማስፋት፤በሴኩላር ሂዩማኒዝም ማዕቀፈ እሳቤ አመንጪነት የሚፈሰውን የመረጃ ጎርፍ የሚመጥን ክርስቲያናዊ መረጃ የመስጠት ዝግጅት ማጎልበት፤ ለምግባር እንቅፋት የሆኑ የዕለት ተዕለት ኑሮ ጥያቄዎችን በግልጽ በመመለስ ክርስቲያኖች የተበታተነ የግል ውሳኔእንዳይከተሉ መርዳት፤ የተቀደሰ ቤተሰብ አስተዳደርን በሚመለከት የሴኩላር ፍትሕ ዳኝነትን ከቤተ ክርስቲያን አንጻር እንዲያውቁ ማድረግና የመሳሰሉትን ጠቅሰዋል፡፡

 

ጥናታዊ ጽሑፉ እንደተጠናቀቀ ሰፋ ያለ ውይይት የተካሔደ ሲሆን ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሾች ተሰጥተዋል፡፡

asmerach com

ስድስተኛው ፓትርያርክ የሚመረጡበት ጊዜ ይፋ ተደረገ

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላ

 

asmerach comስድስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ለማስመረጥ የተቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ ከምርጫው ሂደት ጋርና  በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ምርጫው ተከናውኖ፣ በዚሁ ዕለት ምሽት 12 ሰዓት ላይ፤ ውጤቱ ለሕዝቡ ይፋ እንደሚደረግ አስታውቋል፡፡

 

መራጮች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ከጥንታውያን ገዳማትና አድባራት፤ ከካህናት፤ ከምእመናን፤ ከሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና ከማኅበረ ቅዱሳን አባላት የተወከሉ ሲሆኑ ጠቅላላ ቁጥራቸው 800 መሆኑን ያስታወቀው መግለጫው፡- በመጨረሻ እጩ ሆነው የሚቀርቡ አምስት እጩ ፓትርያርኮች የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረጉ አመልክቷል፡፡ የምርጫውን ሂደት ለማስፈጸም የወጣው መግለጫ “ምእመናን ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናቸው ማንነታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ በመያዝ ለእጩነት የሚያስቡትን አባት አስመራጭ ኮሚቴው ጽ/ቤት ድረስ በአካል በመቅረብ እንዲሁም ከሀገር ውጪ የሚገኙ በፋክስ ቁጥር 0111567711 እና 0111580540 ከየካቲት 1 እስከ 8 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲጠቁሙ”  ጥሪውን አቅርቧል፡፡

 

ስድስተኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን የሚመረጡት አባት እሑድ የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም በዓለ ሢመቱ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም መግለጫው አመልክቷል፡፡

 

ከየሀገረ ስብከቱ በመራጭነት የተወከሉ ሰዎች የካቲት 19 ቀን 2005 ዓ.ም አዲስ አበባ እንዲገቡ ያዘዘው የአስመራጭ ኮሚቴው መግለጫ እግዚአብሔር አምላካችን የወደደውንና የፈቀደውን በመንበሩ ያስቀምጥ ዘንድ ካህናትና ምእመናን ከየካቲት 1 እስከ 8 ቀን ድረስ አምላካቸውን በጸሎት እንዲጠይቁ ለአንድ ሱባኤ የሚቆይ የጸሎት ጊዜ መታወጁን አስታውቋል፡፡

 

p1p2p3p4p5

 

tinat ena miriemer 05 2005

የጥናት መድረክ

tinat ena miriemer 05 2005