timiket05

የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ

ጥር 11 ቀን 2005 ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

timiket05

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ የሚከበረው የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በድምቀት ተከበረ፡፡ ጥር10 ቀን 2005 ዓ.ም. ከዋዜማው ጀምሮ  በተከናወነው የከተራ በዓል ታቦታት ከመንበራቸው በመውጣት ምእመናንን እየባረኩ በብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ቀሳውስት፤ በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችና ምእመናን ታጅበው ወደ ጥምቀተ ባህር በማመራት በድምቀት ተከብሯል፡፡

በተለይም በአዲስ አበባ የአስራ አንድ አድባራትና ገዳማት ታቦታት በቀሳውስት ሽብሸባና ዝማሬ፤ በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዝማሬ፤ በምእመናን እልልታ ታጅበው አመሻሽ ላይ  ጃን ሜዳ ወደሚገኘው ጥምቀተ ባህር ደርሰዋል፡፡

 

በሌሎችም አካባቢዎች ተዘዋውረን እንደተመለከትነው በቅዱስ ራጉኤል፤ በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፤ በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና በጎላ ቅዱስ ሚካአል፤ በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ  እንዲሁም በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድኋድ በነበረው ሥነ ሥርዓት ሃማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ ወጣቶች ታቦታቱ የሚያልፉበትን መንገድ ምንጣፍ በማንጠፍ፤timiket05 youthቄጤማ በመጎዝጎዝ ቀሳውስቱና መዘምራን በዝማሬ ፤ ምእመናን በሆታና በእልልታ አጅበው አቅራቢያቸው ወደሚገኘው ጥምቀተ ባህር አምርተዋል፡፡

ጃንሜዳ በነበረው ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናል፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የአድባራትና ገዳማት ተወካዮች ፤ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ በበአሉ ላይ ለመገኘት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ የአገር ጎብኚዎች፤ የተዘጋጀላቸውን ቦታ በመያዝ ሥነ ሥርዓቱን የተከታተሉ ሲሆን የ2005 ዓ.ም. ተረኛ የሆነው የገነተ ኢየሱስና ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንዲሁም የቤተክርስቲያኑ ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በየተራ ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡

 

በመቀጠልም እለቱን በማስመልከት በአቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ የደቡብና ምዕራብ አዲስ አበባ እንዲሁም የከፋ ሸካ ቤንች ማጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እለቱን በማስመልከት ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል፡፡

ብፁዕነታቸው በሰጡት ቃለ ምዕዳን “የእግዚአብሔር ቸርነት ሰፊ ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልዑለ ባሕርይውን ዝቅ6 አድርጎ ወደ ባሕረ ዮርዳኖስ ዮሐንስ ወዳለበት ቦታ ለመጠመቅ መጥቷል፡፡ ዮሐንስን አጥምቀኝ ማለቱ ለእኛ አብነት ለመሆንና ለቤተ ክርስቲያን ሥርዓትን ለመመሥረት ሲል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ፡፡ ዮሐንስ ወደ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሔዶ አጥምቆት ቢሆን ኖሮ ምእመናን ቀሳውስቱን እቤታችን ድረስ መጥታችሁ አጥመቁን እንጂ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንሔድም ባሉ ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የሌላት እንዳትሆን ሥርዓትን ለማስተማር ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ባሕር፤ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ” ብለዋል፡፡

 

በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ “ጥምቀትን በየዓመቱ የምናከብረው እግዚአብሔርን ለማመስገን ነው፤ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ የሚመግብ እርሱ ነውና፡፡ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ የሰጠ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ ነውና ከሦስቱ አካል አንዱ አካል መሆኑን በአደባባይ የገለጠበት ታላቅ የቤተ ክርስቲያናችን በዓል ነው” በማለት እለቱን በማስመልከት የገለጹ ሲሆን በብፁዕነታቸው ቡራኬ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡

 

ከበዓሉ ፍጻሜ በኋላ ካነጋርናቸው የውጪ ዜጎች መካከል፤ “ሚስተር ጆራ እባላለሁ፡፡ የመጣሁት ከስዊድን ነው፡፡ ክርስቲያን ነኝ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ የመጣሁት ከአስራ አራት አመት በፊት ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ለብዙ ጊዜያት ኢትዮጵያ መጥቼ የኢትዮጵያን የጥምቀት በዓል አክብሬያለሁ፡፡ ይህንን ሥነ ሥርዓት ባየሁ ቁጥር ሁልጊዜ እደነቃለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ፍፁም የተለየ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ያላት ሀገር ናት፡፡ በመላው ዓለም እንደዚህ ዓይነት ደማቅ ክብረ በዓል የሚያከብር የለም፡፡ በጣም የተለየ ነው፡፡ ይህንንም በማየቴ በጣም ተደስቻለሁ” በማለት ነበር የተሰማውን ስሜት የገለጸው፡፡

timiket 2005 mezemiran

የበዓሉ ሥነ ሥርዓት ምሽቱን በመቀጠል ትምህርት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት የተሰጠ ሲሆን በእለቱ ተረኛ በሆኑት በገነተ ኢየሱስና በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያሬዳዊ ዝማሬ ቀርቧል፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን መዝሙር ክፍል አባላትም በተለያዩ ቋንቋዎች ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ መሳሪያዎች ማሰልጠኛ ክፍል አባለት በገና በመደርደር በዓሉን አድምቀውታል፡፡ በተጨማሪም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዜማዊ ድራማ በምሽቱ ለነበረው ምእመን በማቅረብ ሲያገለግሉ አምሽተዋል፡፡ሌሊቱንም በሊቃነ ጳጳሳት እየተመራ ጸሎቱ የቀጠለ ሲሆን የቅዳሴ ሥርዓቱ ተከናውኗል፡፡

 

ከለሊቱ 12፡30 ሰዓት ጀምሮ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ጴጥሮስ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይ ክቡር አቶ ታደሰ በንቲ፤ በኢትዮጵያ የግብጽ አምባሳደር፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ አገር ጎብኚዎች፤ የየአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ምእመናን በተገኙበት የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን በማስመለከት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ መርሐ ግብሩ ተጀመረ፡፡ ጸበሉም ተባርኮ ለምእመናን በመርጨት የበዓሉ ሥነ ሥርዓት ቀጠለ፡፡

 

በዋዜማው ያሬዳዊ ዝማሬ በማቅረብ የበዓሉ ድምቀት የነበሩት የገነተ ኢየሱስና ቅደስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንዱሁም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ያሬዳዊ ዝማሬ ያቀረቡ ሲሆን የአጫበር ቆሜ ወረብም የመርሐ ግብሩ አንድ አካል ነበር፡፡

ዝማሬው  እንደተጠናቀቀ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል አቃቤ መንበረ ፓትርያርክ መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የሰቲት ዑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እለቱን በማስመልከት ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡ ባሰተላለፉት ትምህርትም “በዓላችን የሰላማችን ፤የአንድነታችን ምልክት ነው፡፡ መሠረቱም ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ አደባባይ ተገኝቶ የእኛን ችግር ያስወገደበት ፤ ነፃነታችንን ያገኘንበት፤ የኀጢዓት ደብዳቤያችን የተቀደደበት፤ዮርዳኖስን ተሻግረን በአንድነት ድኅነት መንግስተ ሰማያትን ያየንበት እለት ነው፡፡ ዛሬ በአንድነት በዘመነ ፍዳ የተዘጋው ጆሯችን የአብ ድምጽ የሰማበት ቀን ነው፡፡” ብለዋል፡፡

 

በመቀጠል የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንabune petros the greece እየተስፋፋች ነው፡፡ በዓሉ እጅግ የደመቀ ነው፡፡ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ እጅግ የደመቀ በዓል ስላዘጋጃችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ” በማለት ደስታቸውን የገለጹ ሲሆን የግብጽ አምባሳደር፤ አንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይ ክቡር አቶ ታደሰ በንቲ ንግግር አድርገዋል፡፡

 

በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምዕዳን “እኛ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ የምናከብረው የጥምቀት በዓል ብሔራዊ በዓላችን ነው፡፡ መገለጫችንም ነው፡፡ ድኅነተ ስጋ ወነፍስ ያገኘንበት ቀን በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ” ብለዋል፡፡

 

በብፁዕነታቸው ቡራኬም የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ በጥር 12 ከሚከብሩት የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት በስተቀር ከየአድባራቱና ገዳማት ወደ ጥምቀተ ባሕር መጥተው የነበሩት ታቦታት በመጡበት ሁኔታ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ዘማርያን እንዲሁም በምዕመናን ታጅበው ምዕመናንንና አካባቢውን እየባረኩ በድምቀት እንደወጡ በድምቀት ተመልሰዋል፡፡

 

የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ
በእንዳለ ደምስስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ የሚከበረው የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በድምቀት ተከበረ፡፡ ጥር10 ቀን 2005 ዓ.ም. ከዋዜማው ጀምሮ  በተከናወነው የከተራ በዓል ታቦታት ከመንበራቸው በመውጣት ምእመናንን እየባረኩ በብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ቀሳውስት፤ በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችና ምእመናን ታጅበው ወደ ጥምቀተ ባህር በማመራት በድምቀት ተከብሯል፡፡
በተለይም በአዲስ አበባ የአስራ አንድ አድባራትና ገዳማት ታቦታት በቀሳውስት ሽብሸባና ዝማሬ፤ በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዝማሬ፤ በምእመናን እልልታ ታጅበው አመሻሽ ላይ  ጃን ሜዳ ወደሚገኘው ጥምቀተ ባህር ደርሰዋል፡፡
በሌሎችም አካባቢዎች ተዘዋውረን እንደተመለከትነው በቅዱስ ራጉኤል፤ በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፤ በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና በጎላ ቅዱስ ሚካአል፤ በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ  እንዲሁም በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድኋድ በነበረው ሥነ ሥርዓት ሃማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ ወጣቶች ታቦታቱ የሚያልፉበትን መንገድ ምንጣፍ በማንጠፍ፤ ቄጤማ በመጎዝጎዝ ቀሳውስቱና መዘምራን በዝማሬ ፤ምእመናን በሆታና በእልልታ አጅበው አቅራቢያቸው ወደሚገኘው ጥምቀተ ባህር አምርተዋል፡፡
ጃንሜዳ በነበረው ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናል፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የአድባራትና ገዳማት ተወካዮች ፤ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ በበአሉ ላይ ለመገኘት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ የአገር ጎብኚዎች፤ የተዘጋጀላቸውን ቦታ በመያዝ ሥነ ሥርዓቱን የተከታተሉ ሲሆን የ2005 ዓ.ም. ተረኛ የሆነው የገነተ ኢየሱስና ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንዲሁም የቤተክርስቲያኑ ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በየተራ ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡
በመቀጠልም እለቱን በማስመልከት በአቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ የደቡብና ምዕራብ አዲስ አበባ እንዲሁም የከፋ ሸካ ቤንች ማጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እለቱን በማስመልከት ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል፡፡
ብፁዕነታቸው በሰጡት ቃለ ምዕዳን “የእግዚአብሔር ቸርነት ሰፊ ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልዑለ ባሕርይውን ዝቅ አድርጎ ወደ ባሕረ ዮርዳኖስ ዮሐንስ ወዳለበት ቦታ ለመጠመቅ መጥቷል፡፡ ዮሐንስን አጥምቀኝ ማለቱ ለእኛ አብነት ለመሆንና ለቤተ ክርስቲያን ሥርዓትን ለመመሥረት ሲል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ፡፡ ዮሐንስ ወደ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሔዶ አጥምቆት ቢሆን ኖሮ ምእመናን ቀሳውስቱን እቤታችን ድረስ መጥታችሁ አጥመቁን እንጂ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንሔድም ባሉ ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የሌላት እንዳትሆን ሥርዓትን ለማስተማር ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ባሕር፤ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ” ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ “ጥምቀትን በየዓመቱ የምናከብረው እግዚአብሔርን ለማመስገን ነው፤ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ የሚመግብ እርሱ ነውና፡፡ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ የሰጠ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ ነውና ከሦስቱ አካል አንዱ አካል መሆኑን በአደባባይ የገለጠበት ታላቅ የቤተ ክርስቲያናችን በዓል ነው” በማለት እለቱን በማስመልከት የገለጹ ሲሆን በብፁዕነታቸው ቡራኬ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡
ከበዓሉ ፍጻሜ በኋላ ካነጋርናቸው የውጪ ዜጎች መካከል፤ “ሚስተር ጆራ እባላለሁ፡፡ የመጣሁት ከስዊድን ነው፡፡ ክርስቲያን ነኝ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ የመጣሁት ከአስራ አራት አመት በፊት ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ለብዙ ጊዜያት ኢትዮጵያ መጥቼ የኢትዮጵያን የጥምቀት በዓል አክብሬያለሁ፡፡ ይህንን ሥነ ሥርዓት ባየሁ ቁጥር ሁልጊዜ እደነቃለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ፍፁም የተለየ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ያላት ሀገር ናት፡፡ በመላው ዓለም እንደዚህ ዓይነት ደማቅ ክብረ በዓል የሚያከብር የለም፡፡ በጣም የተለየ ነው፡፡ ይህንንም በማየቴ በጣም ተደስቻለሁ” በማለት ነበር የተሰማውን ስሜት የገለጸው፡፡
የበዓሉ ሥነ ሥርዓት ምሽቱን በመቀጠል ትምህርት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት የተሰጠ ሲሆን በእለቱ ተረኛ በሆኑት በገነተ ኢየሱስና በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያሬዳዊ ዝማሬ ቀርቧል፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን መዝሙር ክፍል አባላትም በተለያዩ ቋንቋዎች ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ መሳሪያዎች ማሰልጠኛ ክፍል አባለት በገና በመደርደር በዓሉን አድምቀውታል፡፡ በተጨማሪም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዜማዊ ድራማ በምሽቱ ለነበረው ምእመን በማቅረብ ሲያገለግሉ አምሽተዋል፡፡
ሌሊቱንም በሊቃነ ጳጳሳት እየተመራ ጸሎቱ የቀጠለ ሲሆን የቅዳሴ ሥርዓቱ ተከናውኗል፡፡
ከለሊቱ 12፡30 ሰዓት ጀምሮ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ጴጥሮስ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይ ክቡር አቶ ታደሰ በንቲ፤ በኢትዮጵያ የግብጽ አምባሳደር፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ አገር ጎብኚዎች፤ የየአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ምእመናን በተገኙበት የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን በማስመለከት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ መርሐ ግብሩ ተጀመረ፡፡ ጸበሉም ተባርኮ ለምእመናን በመርጨት የበዓሉ ሥነ ሥርዓት ቀጠለ፡፡
በዋዜማው ያሬዳዊ ዝማሬ በማቅረብ የበዓሉ ድምቀት የነበሩት የገነተ ኢየሱስና ቅደስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንዱሁም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ያሬዳዊ ዝማሬ ያቀረቡ ሲሆን የአጫበር ቆሜ ወረብም የመርሐ ግብሩ አንድ አካል ነበር፡፡
ዝማሬው  እንደተጠናቀቀ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል አቃቤ መንበረ ፓትርያርክ መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የሰቲት ዑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እለቱን በማስመልከት ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡ ባሰተላለፉት ትምህርትም “በዓላችን የሰላማችን ፤የአንድነታችን ምልክት ነው፡፡ መሠረቱም ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ አደባባይ ተገኝቶ የእኛን ችግር ያስወገደበት ፤ ነፃነታችንን ያገኘንበት፤ የኀጢዓት ደብዳቤያችን የተቀደደበት፤ዮርዳኖስን ተሻግረን በአንድነት ድኅነት መንግስተ ሰማያትን ያየንበት እለት ነው፡፡ ዛሬ በአንድነት በዘመነ ፍዳ የተዘጋው ጆሯችን የአብ ድምጽ የሰማበት ቀን ነው፡፡” ብለዋል፡፡
በመቀጠል የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እየተስፋፋች ነው፡፡ በዓሉ እጅግ የደመቀ ነው፡፡ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ እጅግ የደመቀ በዓል ስላዘጋጃችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ” በማለት ደስታቸውን የገለጹ ሲሆን የግብጽ አምባሳደር፤ አንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይ ክቡር አቶ ታደሰ በንቲ ንግግር አድርገዋል፡፡
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምዕዳን “እኛ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ የምናከብረው የጥምቀት በዓል ብሔራዊ በዓላችን ነው፡፡ መገለጫችንም ነው፡፡ ድኅነተ ስጋ ወነፍስ ያገኘንበት ቀን በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ” ብለዋል፡፡
በብፁዕነታቸው ቡራኬም የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ በጥር 12 ከሚከብሩት የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት በስተቀር ከየአድባራቱና ገዳማት ወደ ጥምቀተ ባሕር መጥተው የነበሩት ታቦታት በመጡበት ሁኔታ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ዘማርያን እንዲሁም በምዕመናን ታጅበው ምዕመናንንና አካባቢውን እየባረኩ በድምቀት እንደወጡ በድምቀት ተመልሰዋል፡፡

 

001a

ወቅታዊውን ጉዳይ አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ አወጣ

ጥር 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖአምላክ

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ወቅታዊውን ጉዳይ በማስመልከት፤ ትናንት ረቡዕ ጥር 8 ቀን 2005 ዓ.ም ባወጣው ባለ 5 ገጽ መግለጫ፥ በ3 ዐበይት ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጎ  ውሳኔ አሳልፏል፡፡

 

ቅዱስ ሲኖዶስ የመከረባቸውን አጀንዳዎችና ያተላለፈውን ውሳኔ የያዘው የመግለጫውን ሙሉ ቃል  አቅርበነዋል፡፡

001a002b003c004d005e

የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑ ተገለጸ

ጥር 8 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

tsadekana 2 1በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የምትገኘው ታሪካዊቷና ተአምረኛዋ የደብረ ምጥማቅ የጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እሰከ 25 ሚሊዮን ብር በሚደርስ ወጪ የቤተ ክርስቲያኑን ሕንፃ እየተገነባ መሆኑን  በአዲስ አበባ የተቋቋመው የሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ ገለጸ፡፡

ደብረ ምጥማቅ  የጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን በዘመናዊ መልክ ለመገንባት እንዲቻል አዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ በሚገኘው ደሳለኝ ሆቴል ታኅሣሥ  21 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የገቢ ማሰባበሰቢያና የምክክር መርሐ ግብር የተዘጋጀ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የማእከላዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል፡፡ ብፁዕነታቸው መርሐ ግብሩን በጸሎት ከከፈቱ በኋላ በሰጡት ቃለ ምዕዳን “የዚህ ታላቅና ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ ላይ መሣተፍ ባለ ታሪክ ከማድረጉም ባሻገር የቀደሙ ነገሥታትን አርዓያ መከተል ነው፡፡ በዚህም መሠረት ቤተ ክርስቲያኑን ተባብረን እንድንሠራውና የታሪኩ ተካፋይ እንድንሆን ከእኛ ይጠበቃል” ብለዋል፡፡

የደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና የጻድቃኔ ቅድስት ማርያም መካነ ቅዱሳን አንድነት ገዳም አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ፊሊጶስ አባተ “ምእመናን ወደ ገዳማችን እየመጡ ጸበሉን እየተጠመቁና እየጠጡ፤ እምነት እየተቀቡ፤ በጸሎት እየተጉ ድኅነትን ያገኛሉ፡፡ ገዳሙ ታላቅ የበረከት ቦታ ነው፡፡ ይህንን የቤተ ክርስቲያን ሥራ ምእመናን አቅማቸውን የፈቀደላቸው ያህል በገንዘብ፤ በጥሬ እቃ አቅርቦት፤ በጉልበትም ሆነ በእውቀታቸው እንዲራዱንና የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ እንጠይቃለን“ በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

tsadekana 2 2በአዲስ አበባ የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢንጂነር አማረ አበበ ባቀረቡት ሪፖርትም ቤተ ክርስቲያኑ ከተሠራ ረጅም ዘመናትን ማስቆጠሩ፤ ጣሪያው ማፍሰሱ፤ በደርግ ዘመነ መንግሥት በነበረው ጦርነት አደጋ ስለደርሰበት፤ እንዲሁም ከተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የሚመጡ ምእመናን ቁጥር ከፍተኛ መሆኑና ቤተ ክርስቲያኑ በመጥበቡ ምክንያት በአዲስ  መልክ ለመገንባት ታስቦ ወደ ሥራ ለመግባት እንደቻሉ ገልጸዋል፡፡ በዚህም መሠረት የቤተ ክርስቲያኑ የመሠረት ሥራ ተጠናቆ ወደ ዋናው ግንባታ የተገባና ሥራውን በተቀላጠፈ ሁኔታ ለማከናወን እንዲቻል የምክክር መርሐ ግብር እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ ከሦስት መቶ በላይ ጥሪ የተደረገላቸው ምእመናን የተገኙ ሲሆን በቤተ ክርስቲያኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል፡፡ ጥሪ ለተደረገላቸው ምእመናንም የእራት ግብዣ ተደርጎላቸዋል፡፡ በመጨረሻም ምእመናን የቃል ኪዳን ሰነድ ሞልተው  ከ1ሚሊዮን በላይ በጥሬ ብር፤ እንዲሁም በጥሬ እቃዎች አቅርቦት ቃል ኪዳን እንደተገባ ሰነድ ለማሰባበሰብ መቻሉን ከኮሚቴው አባላት ለማወቅ ተችሏል፡፡

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ሰላ ድንጋይ የሚገኘው የደብረ ምጥማቅ ማርያምና የጻድቃኔ ቅድስት ማርያም መካነ  ቅዱሳን አንድነት ገዳም በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በንጉሥ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ አማካይነት እንደተመሠረተ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ቤተ ክርስቲያኑን ሊያሠሩ የቻሉበት ዋነኛ ምክንያትም፤ በግብፅ ሀገር ሃይማኖት፤ ዘር፤ ቀለም ሳትለይ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትገለጽ የነበረችበት ቤተ ክርስቲያን እሰላሞች በማቃጠላቸው እጅግ አዝነው ስለነበር በኢትዮጵያ ውስጥ ሰሜን ሸዋ ላይ ቤተ ክርስቲያኑን እንዳሠሩ የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡

በንጉሥ ዘርዐ ያዕቀብ የተመሠረተው ይህ ገዳም አሁንም ባለንበት ዘመን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በሕልም፤ በራዕይና በተከስቶ እየተገለጸች ምእመናንን እየተራዳች፤ በስሟ ከፈለቀው ጸበል እየጠጡና እየተጠመቁ ከተለያዩ ደዌያት በመፈወስ ላይ ናቸው፡፡

የቤተ ክርስቲያኑን ሕንፃ ሥራ መርዳት ለሚፈልጉ ሁሉ በስልክ ቁጥር 0911243678፤ 0911207804፤ 0911616880፤ ደውለው ማነጋገር የሚችሉ ሲሆን በተጨማሪም ለሕንፃው ሥራ መፋጠን በባንክ መርዳት ለሚፈልጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አራት ኪሎ ቅርንጫፍ የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ በባንክ ቁጥር 1000033548625 መላክ እንደሚቻል ኮሚቴው አሳስቧል፡፡

abunehizkiel

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ለዕርቀ ሰላሙ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚመክር ታወቀ

ጥር 3 ቀን 2005 ዓ.ም.

 

abunehizkielየቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ጥር 6 ቀን 2005 ዓ.ም. የሚካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ለዕርቀ ሰላሙ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚመክር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፣ የደቡብና ምዕራብ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከትና የከፋ ሸካ ቤንች ማጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል በተለይ ለስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ገለጹ፡፡

 

ለዕርቀ ሰላሙ ድርድር ወደ አሜሪካ የተላኩት አባቶች ተልእኳቸውን ፈጽመው በሰላም ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ያስታወሱት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የተላኩት አባቶች በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ በመሆኑ እነዚሁ አባቶች በዕርቀ ሰላም ድርድር ወቅት የደረሱበትን የውሳኔ አሳብና ተያያዥ ጉዳዮች ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ጥር 6 ቀን 2005 ዓ.ም. በሪፓርት መልክ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡

 

ቅዱስ ሲኖዶስ ለዕርቀ ሰላሙ ቅድሚያ እንደሚሰጥና ለውጤታማነቱ እየሠራ መሆኑን የሚገልጹት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ዕርቀ ሰላሙ እንዲወርድ በራችንን ከፍተን እየጠበቅን ነው፡፡ በውጭ ያሉ አባቶችም ወደ አገራቸው በሰላም ገብተው ከእኛው ጋር አንድ ሆነው በፓትርያርክ ምርጫው በመራጭነትም ሆነ በተወዳዳሪነት ሊሳተፉ ይችላሉ ብለዋል፡፡

 

የፓትርያርክ ምርጫን ከዕርቀ ሰላሙ ጎን ለጎን ለማካሄድ የታሰበው ቤተ ክርስቲያኒቱ ያለ አባት፣ ምእመኑም ያለ እረኛ ተበትነው እንዳይቀሩ እንደሆነ የሚገልጹት ብፁዕነታቸው እኛም ለመንጋችን እናስባለን እንራራለን፡፡ አንድነትም እናመጣለን፡፡ ምእመኑ ተለያይቶ እንዳይቀርና በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር እንዲሆን መለያየትን ለማስወገድ እንጥራለን ብለዋል፡፡

 

ዋናው ቁም ነገር ዕርቀ ሰላም ነው የሚሉት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ለስኬታማነቱ በሽምግልናው ሂደት የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች ተጨምረውበት የዕርቀ ሰላሙ ድርድር እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡

 

ከዚሁ ጋር አያይዘው የፓትርያርክ ምርጫ ደንብ መጽደቁን የሚገልጹት ብፁዕነታቸው ሥልጣኑ የምልዐተ ጉባኤው ስለሆነ በተጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ዳግም ሊታይ እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

 

  • ምንጭ፡- ስምዐ ጽድቅ 20ኛ ዓመት ቁጥር 8፣ 2005 ዓ.ም.
abune_nathnael

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡

ታኅሣሥ 26 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ


abune_nathnaelየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልእክት “በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ እንዲሁም የሕግ ታሪሚዎች ሆናችሁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት እንኳን ለ2005 ዓ.ም. የጌታችን የአምላካችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዐለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡” ካሉ በኋላ “በጌታችን ቤዛነት እንድን ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮአልና፤ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር በዚህ አውቀናል፡፡ እግዚአብሔር ከፍጡራን ሁሉ የተለየና ከአእምሮ በላይ የሆነ መለኮታዊ ኀይል ያለው አምላክ በመሆኑ የባሕርዩን ጥልቅነት በምልአት ማወቅ ፈጽሞ የማይቻል ቢሆንም እርሱ ራሱ በገለጸልን መጠን የተወሰኑ ነገሮችን እናውቃለን፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ “እግዚአብሔር ፍቅር ነው” ብሎ ምልአተ ፍቅሩን ካስረደ በኋላ በማስረጃ ሲያብራራ ቤዛ ሆኖ የሰውን ልጅ ያድን ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮአልና ፍቅሩን በዚህ አውቀናል” ይላል፡፡ እግዚአብሔር በልጁ መሥዋዕትነት ዓለምን ለማዳን ያደረገው ፍቅር ከሌላው ሁሉ የበለጠ በመሆኑ ልቆ ተነገረ እንጂ የእግዚአብሔር ፍቅር ከፍጡራን የተለየበት ጊዜ እንደሌለ ሁላችንም እናውቃለን፤ በስፋትም ልንገነዘብ ይገባልና፡፡” ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እግዚአብሔር ለፍጥረቱ በፍቅር ከሰጣቸው ስጦታዎች ሁሉ በቤተልሔም ለዓለም ስለሰጠው ስጦታ ሲናገሩ “የቤተልሔም ስጦታ ከስጦታዎች ሁሉ እጅግ በጣም የላቀ ነው፡፡ ምክንያቱም ሌሎች ስጦታዎች ከፍጥረቶቹ የሚገኙ የፍጥረት ውጤት ስጦታዎች ሲሆኑ የቤተልሔም ስጦታ ግን አንድ ልጁን ነውና” ብለዋል፡፡ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በማጠቃለያ መልእክታቸው “እግዚአብሔር እኛን ይህን ያህል ከወደደን እኛም እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል፤ ከልደተ ክርስቶስ የምንማረው ትምህርት ወገንን ሁሉ ማለትም በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን የሰው ዘር ሁሉ መውደድና መርዳት ነው፡፡… ባለንበት ዘመን በተለያየ ምክንያት እናትና አባትን ያጡ፣ የወገንን ፍቅርና እንክብካቤ የሚሹ ብዙ የእግዚአብሔር ልጆች በየሠፈሩ አሉ፡፡ ለበዐል መዋያ ያዘጋጀነውን ኅብስተ በረከት ከተቸገሩት ሕፃናትና የሚላስ የሚቀመስ ካጡ ወገኖች ጋር በመሆን በኅብረት መመገብ ይገባናል፡፡ ይህን ስናደርግ በፍጹም ፍቅሩ የወደደንን እግዚአብሔርን በቤታችን ውስጥ እየጋበዝን እንደሆነ እርግጠኞች መሆን አለብን፡፡ “ተርቤ አብልታችሁኛልና ኑ ወደ እኔ” የሚል ቃል ኪዳን እንዳለበትም እናስታውስ፡፡” ብለዋል፡፡

በስልታዊ ዕቅድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ

ታኅሣሥ 22 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ


ማኅበረ ቅዱሳን ከ2005 ዓ.ም – 2008 ዓ.ም ድረስ የሚተገበረውን የ4 ዓመት ስልታዊ ዕቅድ ዙሪያ በ6 ማእከላት ማስተባበሪያ አማካኝነት ለሁሉም ማእከላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ምክክር መሰጠቱ ተገለጸ፡፡

ዲ/ን አንዱአምላክ ይበልጣል የሀገር ውስጥ ማእከላትና ግቢ ጉባኤያት ማደራጃና ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ሓላፊና ምክትል ዋና ጸሐፊ እንደተናገሩት መቀመጫቸው ባሕር ዳር፣ መቀሌ፣ ጅማ፣ ሓዋሳ፣ ድሬደዋና አዲስ አበባ ላይ በሆኑ 6 የማእከላት ማስተባበሪያ ቢሮዎች አማካኝነት ለሁለት ቀናት በስልታዊ ዕቅድ ወሳኝ ጉዳዮች፣ ዓላማ፣ ግቦችና ስልቶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ የተሰጠ ሲሆን በሀገር ውስጥ ባሉ 44 ማእከላት የማእከላቱ ድርሻ ላይ ምክክር ተደርጓል ብለዋል፡፡

 

የስልታዊ ዕቅድ የግንዛቤ ማስጨበጫውን ተከትሎም የአባላት አሳብ መስጫ፣ ቅሬታ አቀራረብና አፈታት ሥርዓትና የግንዛቤ ምክክርና የግቢ ጉባኤያት የገንዘብና የንብረት አጠቃቀም መመሪያ ላይ ውይይት ተደርጓልም በማለት ተናግረዋል፡፡

 

ለሁለት ቀናት በተደረገው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ላይ 44 ማእከላት የ6ቱ የማእከላት ማስተባበሪያ አማካኝነት ሁለት ተወካዮች የተገኙ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን ከጥር 1 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲሱ ስልታዊ ዕቅድ አገልግሎቱን እንደሚጀምር ዲ/ን አንዱአምላክ አስረድተዋል፡፡

የጥናትና ምርምር ማእከሉ ያዘጋጀው የጥናት ጉባኤ ተራዘመ

ታኅሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.

በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል ታኅሣሥ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. “በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የፓትርያርክ ምርጫና የአባቶች እርቀ ሰላም” በሚል መሪ ቃል አዘጋጅቶት የነበረው የጥናት ጉባኤ ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ ሲሆን የሚካሄድበትን ጊዜ ወደፊት የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

eg 1

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የልምድ ልውውጥ አደረጉ

ታኅሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ኅሩይ ባየ

eg 1

ከታኅሣሥ 11-15 ቀን 2005 ዓ.ም. ለአምስት ተከታታይ ቀናት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የልምድ ልውውጥ አደረጉ፡፡ የልምድ ልውውጡ የተከናወነው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲሆን በአምስቱ ዕለታት በየቀኑ እስከ አንድ ሺሕ ለሚሆኑ የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች መካፈላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

ታኅሣሥ 11 ቀን 2005 ዓ.ም. በጉባኤው መክፈቻ ዕለት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ እና የኢሊባቡርና ጋምቤላ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የቅዱስ ሲኖዶስ ልዩ ጸሐፊና የአዲስ አበባ ምዕራብ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የበላይ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቢመን የላዕላይ ግብፅ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ቄስ ዳውድ ለሜይ የግብፅ መንበረ ማርቆስ ካቴድራል ካህን፣ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዲያቆናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የአድባራት የስብከተ ወንጌል ክፍል ሓላፊዎች፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅና የቅዱስ ጳውሎስ ሰዋሰወ ብርሃን ከፈተኛ ትምህርት ቤት ደቀ መዛሙርት፣ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ተገኝተዋል፡፡

 

eg 3 2“ተዘከር ማኅበረከ ዘአቅደምከ ፈጢረ ወአድኀንከ በትረ ርስትከ ደብረ ጽዮን ዘኀደርከ ውስቴታ… አስቀድመህ የፈጠርሃትን ማኅበርህን የተቤዥሃትንም የርስትህን በትር በእርስዋ ያደርህባት የጽዮንን ተራራ አስብ” /መዝ.73፥2/ የሚለው የዳዊት መዝሙር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅድሳን ገዳም ዲያቆናት ተሰብኮ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አምስት በብፁዕ አቡነ ናትናኤል ከተነበበ በኋላ የኪዳን ጸሎት ደርሷል፡፡ በመቀጠልም ዐቃቤ ርእሰ መንበሩ ግብፅና ኢትዮጵያ እኅትማማች ዓብያተ ክርስቲያናት መሆናቸውን አስታውሰው የቆየ ቤተሰባዊ ግንኙነታቸውን አጠናክረው በመቀጠል የልምድ ልውውጥ ለማድረግ የመጡ ግብፃውያንንና የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን አመስግነዋል፡፡

 

ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በመሸፈን በአሜሪካና በግብፅ የሚገኙ የበጎ ፈቃደኛ አገልጋዮች ልዑካንን በመመደብ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት አምስት ቀናት የልምድ ልውውጥ እንዲደረግ ላደረገችው አስተዋጽኦ ምሥጋናቸውን የገለጡት የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የኤች አይቪ መከላከያና መቆጣጠሪያ መምሪያ ሓላፊ ቄስ ሶምሶን በቀለ ልማት ኮሚሽኑ በማስተባበር እና የቋሚ ተሳታፊ ሠልጣኞችን የትራንስፓርት ወጪ መሸፈኑን ገልጠዋል፡፡

 

በሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያተኮረው የልምድ ልውውጥ በከፍተኛ መነቃቃትና ፍላጎት ተካሂዷል፡፡ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት እነዚህን ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለማስተማር ያላቸው ብቃት እንደተጠበቀ መሆኑን የገለጡት ቄስ ዳውድ ለሜይ በሥርዓት አፈጻጸሙ ላይ የልምድ ልውውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል በተጨማሪም ምእመናን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት፣ የሚታይና የማይታይ ጸጋ ለማግኘት እነዚህ ምሥጢራት ከሕይወታቸው ጋር አስተሳስረው ሁል ጊዜ በማንኛውም ቦታ በየትኛውም ጊዜ የምስጢራት ተካፋይ መሆን እንደሚያስፈልግ ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው ልዑኩ በአጽንኦት ገልጠዋል፡፡

 

“ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለእኛ አዲስ ናቸውን?” የሚሉ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች አሳባቸውን ያቀረቡ ሲሆን ቄስ ዳውድ በምሳሌ እንዳስረዱት በጉባኤ የተገኘ አንድን ሕፃን ልጅ ጠርቼ አባትህ አለ? ብዬ ብጠይቀው ካለ አለ ማለቱ አይቀርም አሁንም ተጨማሪ ጥያቄ እንድጠይቀው ፍቀድልኝ አሉ አባትህ ስንት ብር በኪሱ ይዟል? አላውቅም አለ፡፡ የት ነው የሚሠራው? አላውቅም፡፡ ደመወዙ ስንት ነው? አላውቅም፡፡ የሚገርም ነው ሕፃኑ አባቱን ያውቃል ስለ አባቱ ግን የማያውቀው ብዙ ነገር አለ፡፡ … በማለት ምላሻቸውን በምሳሌ አስቀምጠዋል፡፡ በዚህ መነሻነት ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በጥልቀትና በዝርዝር ማወቅ የተለያዩ ነገሮች መሆናቸውን በማብራራት ይልቁንስ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመጠንከር፣ ከዲያብሎስ ቀስት ለማምለጥ፣ በመንፈስ ቅዱስ ለመቃኘት፣ ምስጢራቱን ማወቅ ሳይሆን መጠቀም እንዲገባ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኩል የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት፣ ከአዲስ አበባ ደቡብ ሀገረ ስብከት የተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከማኅበረ ቅዱሳን ዘማርያን ያሬዳዊ መዝሙር ያቀረቡ ሲሆን ሦስት ወጣቶችም በገና እየደረደሩ ዝማሬያቸውን አቅርበዋል፡፡

 

eg 3 1የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዝማሬ ስሰማ ንጉሥ ዳዊት በዓይነ ኅሊናዬ፤ ይመጣል በመጽሐፍ ቅዱስ የተዘረዘሩት የዜማ ዕቃዎች መልካቸቹውን ሳይቀይሩ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገሩ መዝለቃቸውን አድንቀው ለወደፊት ይህ ትውፊት ሳይቋረጥ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ በእነሱ በኩል ከሁለት የዘለለ የዜማ ዕቃ እንደሌላቸው ያስታወሱት ቄስ ዳውድ የእኛ ዜማ ጣዕም እጅግ የሚመስጥ ደስ የሚል እንደሆነ ሳይሸሽጉ ተናግረዋል፡፡ በዝማሬያችን የተመሰጡት ግብፃውያን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በፍጹም ተመስጦ ለመዘመር ሲሞክሩ ታይተዋል፡፡

 

የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን በመወከል ዲያቆናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዝማሬ አቅርበዋል፡፡ በአረብኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተለያዩ መዝሙራትን በማቅረብ የዝማሬውን መልእክት ቄስ ዳውድ አብራርተዋል፡፡

 

በአጠቃላይ በጉባኤው የተለያዩ ጥያቄዎች ተነሥተዋል፡፡ ተገቢና ግልጽ ምላሾች ተሰጠተዋል፡፡ ሆኖም በሁለቱ ዓብያተ ክርስቲያናት ያለው መሠረታዊ አንድነት የዶግማ እንጂ የሥርዐት ስላልሆነ በልምድ ልውውጡ የተገለጡ እንግዳ ሥርዓቶች ከኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንፃር መታየት እንዳለባቸው ሊቃውንቱ አሳስበዋል፡፡ ትምህርተ ኖሎት፣ ሐዋርያዊ ተልእኮ፣ በጎ አስተዳደርና የግጭት አፈታትን በሚመለከቱ የጥናት ጽሑፎች በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ቀርቦ ሰፊ ውይይትና በቂ ግንዛቤ ተገኝቶበታል፡፡

 

የልምድ ልውውጡ በጎ ገጽታ እንዳለው እና ለወደፊቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዕለቱ ከተሰጡ አስተያየቶች ለመረዳት ተችሏል፡፡

men 16

ሥልጠናው የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ

ታኅሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

men 16

ማኅበረ ቅዱሳን ከታኅሣሥ 6-11 ቀን 2005 ዓ.ም. ከ65 በላይ ለሚሆኑ የገዳማት አበመኔቶች፣ እመምኔቶችና ተወካዮች “የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማሳካት የገዳማት ድርሻ” በሚል መሪ ቃል የግማሽ ቀን ዐውደ ጥናትና በዩኒቨርስቲ ምሁራን፤ በቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ እንዲሁም በተጋባዥ ምሁራን ለአምስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡

 

ሥልጠናው ያተኮረው፡-

  • ገዳማት ያላቸውን ልዩ ልዩ ሀብታት ምንድናቸው? እንዴትስ ጥቅም ላይ ይውላሉ?

  • የአካባቢ ጥበቃ /ከብዝሃ ሕይወት ጋር በተያያዘ/

  • የሥራ ፈጠራ ክህሎትና የገቢ ማስገኛ እቅድ ዝግጅት

  • የቅርስ አጠባበቅ፣ ገዳማት ከቅርስ ጉብኝት እንዴት ተጠቃሚ ማድረግ ይችላል?

  • የቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ ለማሳካት የገዳማትና የመነኮሳት ድርሻ

  • የገዳማት አስተዳደር ለማጠናከር የሰው ኀይል አጠቃቀም

  • የመረጃ ልውውጥና የውሳኔ አሰጣጥ

  • የሀብት ቁጥጥርና አስተዳደር ምን መምሰል ይኖርበታል?

  • የፕሮጀክት ጥናትና የፕሮጀክት ትግበራ . . . ወዘተ በሚሉ ዋና ዋና ርዕሰ ጉደዮች ላይ በስፋት ሥልጠናው ተሰጥቷቸዋል፡፡

 

በሥልጠናው ላይ የቡድን ውይይት በማድረግ፣ ገዳማት ከገዳማት ተሞክሮና ልምድ ልውውጥ፣ እንዲሁም የእርስ በርስ የመተዋወቅ ሥራዎች ለመሥራት ተችሏል፡፡

 

በሥልጠናው ላይ ያገኙትን ግንዛቤ ለመገምገምም በቅዱሳት መካናት ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የተዘጋጀ ፈተና የተሰጣቸው ሲሆን በውጤታቸው መሠረት ብልጫ ላመጡ 3 መነኮሳት የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገድል ተሸልመዋል፡፡ ሥልጠናውንም ወስደው በማጠናቀቃቸው ሁሉም ሰልጣኞች ከብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡

 

በመዝጊያ መርሐ ግብሩ ላይ ሥልጠናውን የወሰዱት የገዳማት አበምኔቶች፤ እመምኔተችና ተወካዮች ሥልጠናው ከፍተኛ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው በመግለጽ የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡

 

በአቋም መግለጫቸውም፡-

  1. ገዳማውያንና ገዳማውያት ገዳማት ያላቸውን የተፈጥሮ ሀብት በመጠቀም እራሳቸውን ችለው ሌላውን እንዲረዱ፤

  2. በገዳማት የሚገኙ ቅርሶችን በአግባቡ በመያዝና በመጠበቅ ለትውልድ ማስተላለፍ እንዲችሉ፤

  3. የቁሪት ገዳማት ወደ አንድነት ገዳማዊ ሥርዓት እንዲመጡ /እንዲገቡ/ የሚደረግበት መንገድ እንዲመቻች፤

  4. ገዳማውያን እና መነኮሳት ለተልዕኮ ከገዳማቸው በሚወጡ ጊዜ ተልዕኮአቸውን ፈፅመው እስኪመለሱ ድረስ የሚቆዩበት ማረፊያ ቤት በወረዳ በዞን እና በአዲስ አበባ ላይ እንዲመቻች ቢደረግ፤

  5. በየገዳማቱ የሚገኙ ነገር ግን ያልታተሙ የቅዱሳን አባቶች የገድል መጻሕፍት እንዲታተሙ ቢደረግ

  6. በኢትዮጵያ ያሉ ገዳማት ወጥ በሆነ አንድ ሥርዓተ ገዳም እንዲተዳደሩ ቢሆን፤

  7. ያለ በቂ ሥራ ወይም ምክንያት ከገዳም ወደ ገዳም በመዘዋወር እና ከተማ በመምጣት እና በመቀመጥ ስም የሚያጎድፉ መነኮሳት በሚመለከተው አካል ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ቢደረግ፤

  8. ቅድሳት ስዕላትን እና መስቀል ይዘው በየመንገዱ በቤተ ክርስቲያን ስም መለመኑ እንዲቆም እንዲደረግ፤ ያለ አግባብ ለዚሁ ጉዳይ ፈቃድ የሚሰጡ አካላትም እንዲታቀቡ እንዲደረግ፤

  9. በየገዳማቱ ያሉት የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዲጠናከሩ እና ባልተቋቋሙባቸው ገዳማት የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዲቋቋም ቢደረግ፤

  10. የኢትዮጵያ ገዳማት በገዳማት መምሪያው አማካይነት ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ እንድንሰበሰብ እና እንድንወያይ ቢደረግ፤

  11. የገዳማውያን ጉዳይ በገዳማውያን አባቶች እንዲታይ ቢደረግ፤

  12. ገዳማት ከሚሠሩት የልማት ሥራ ለመንግሥት ከሚከፍሉት ግብር ነፃ የሚሆኑበት መንገድ ቢመቻች፤

  13. በመጨረሻም ከመመሪያው ሥር ሆኖ ስለገዳማት መጠናከርና ለችግሮቻቸው መፈትሔ የሚሰጥ 12 አባላት ያሉት አንድ ዐቢይ ጉባኤ /ኮሚቴ/ የመረጥን ስለሆነ እንዲፀድቅልን በማለት በአንድ ድምፅ ተስማምተን አቋም ይዘናል፡፡ በማለት የአቋም መግለጫቸውን አሰምተዋል፡፡

 

በማቅኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ዳይሬክተር ዲ/ን አእምሮ ይሔይስን የሥልጠናውን ውጤት በማስመልከት ጠይቀናቸው ሲመልሱም  “ሥልጠናው ወደፊት በገዳማት ላይ ለምንሠራቸው ሥራዎች በር የከፈተ ነው፡፡ ከመነኮሳቱ ግብረ መልስ እንደተረዳነው ሥልጠናው ጥሩ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው አመላክቶናል፡፡ በተሻለ ሁኔታና ባቀድነው መሠረት ተከናውኗል፡፡ ወደፊትም አሠልጥነን የምንለቃቸው ሳይሆን ለመነሻ የሚሆን ከየገዳማቱ ምን ሊሠራላቸው እንደሚፈልጉ ከሰጡን መረጃ ተነሥተን ጥናቶችን በማጥናት እገዛ እናደርጋለን፤ ክትትላችንንም እንቀጥላለን፡፡” በማለት ገልጸዋል፡፡

 

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

 

ከመርሐ ግብሩ መጠናቀቅ በኋላ በሥልጠናው ስላገኙት እውቀትና የተሰማቸውን ስሜት እንዲገልጹልን ገዳማውያን አባቶችን የጠየቅናቸው ሲሆን የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተውናል፡፡

 

ስለ ሥልጠናው ከገደማውያን አባቶች አንደበት

  • “ለገዳማት ልማት ትልቅ ለውጥ ነው፡፡ እስከ ዛሬ እንደዚህ ዓይነት ሥልጠና አጋጥሞን አያውቅም፡፡ እስከ ዛሬ እንዴት ናችሁ? ብሎ የሚጠይቀን አልነበረም፡፡ አሁን የሚጎበኘን አካል ያገኘንበት ነው፡፡ ከሥልጠናው ጠቃሚ እውቀት አግኝተናል፡፡”

አባ ወ/ገብርኤል ንጋቱ ከሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ወገራ የቅድስት ማርያም ወአቡነ ምእመነ ድንግል አንድነት ገዳም አበምኔት

 

  • “በዚህ ሥልጠና ለየት ያለ እውቀት አግኝቻለሁ ፤ ያላወቅሁትን እንዳውቅ የራሴንም ገዳም እንድመለከት አድርጎኛል፡፡ የተማርኩተን ለገዳማውያኑ በማሳወቅ የልማት ሥራዎችን እንዴት መተግበር እንደሚቻልና ገዳማችንን እንዴት መሳደግ እንደምንችል ተገንዝቤያለሁ፡፡”

አባ ኢሳያስ ወልደ ሰንበት የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅድስ ገዳም አበምኔት

 

  • “ማኅበረ ቅዱሳን ፋና ወጊ የሆነና ገዳማትን ያሰባሰበ ጉባኤ በማዘጋጀቱ ታላቅ ደስታ ተሰምቶናል፡፡ በገዳማችን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች አሉ፡፡ በልማት ራሳችንን የቻልንበት ሁኔታ ላይ ነን፡፡ የገዳማት አንድነትና ትስስር የሚያጠናክርና መፃያትን ጊዜያት እንድንመለከት አስችሎናል፡፡”

አባ ተክለ ሥላሴ ገብረ ሕይወት የምሥራቅ ሸዋ ጮባ በዓታ ለማርያም ገዳም አበመኔት

 

  • “ገዳሙ የአንድነት ገዳም ነው፡፡ ብዙ መጻሕፍትንና ቅርሶችን አጠቃሎ የያዘ ነው፡፡ አምስት ጳጳሳትን የፈራ ገዳም ነው፡፡ በሥልጠናው መካፈሌ ለቅርሶቻችን አያያዝ ጠቃሚ መረጃ አግኝቼበታለሁ፡፡”

አባ ዘመንፈስ ቅዱስ ረዳ ከትግራይ አክሱም ጭህ ሥላሴ የአንድነት ገዳም አበምኔት

 

  • “በገዳማችን 5 መነኮሳትና 6 ዲያቆናት ብቻ ነን ያለነው፡፡ ገዳሙ ጥንታዊ ነው፡፡ ያገኘነው እውቀት የሚያስደስት ነው፡፡ ውኃ አለን፡፡ በመስኖ ተጠቅመን የልማት ሥራዎችን ለመሥራት ያበረታታናል፡፡ እስካሁን በመስኖ ተጠቅመን ያከናወነው ነገር የለም፡፡”

መምህር ገብረ ማርያም ግደይ የትግራይ ተንቤን እንዳጨጌ ደብረ ፅጌ ኪዳነ ምሕረት ገዳም አበምኔት

 

  • “ከሥልጠናው በየበኩላችን በየገዳማቱ በልማትም ሆነ በመንፈሳዊ ሕይወት ለውጥ የምናመጣበትና የቤተ ክርስቲያንን ትውፊት በጠበቀ መልኩ እንዴት መለወጥ እንዳለብን አስገንዝቦኛል፡፡ ለገዳሙ መነኮሳት የተማርኩትን አስተምራለሁ፡፡ አደራ ተሸክሜአለሁና፡፡”

አባ ወልደ ሠማዕት አብርሃም ከዋልድባ አብረንታት ቤተ ሚናስ ማኅበር የገዳሙ አርድዕትና ተወካይ

 

  • “እየወሰድን ያለው ሥልጠና ቤተ ክርስቲያናችን በፍቅርና በሰላም በልማት ላይ ትኩረት አድርጋ እንድትኖር የሚያመላክት ትጥቅ ነው የገበየሁት፡፡ ይህንን ተሞክሮ የቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ የኢትዮጵያ ገዳማትን ሁሉ አሰባስቦ ጠንካራ ሥራ መሥራት ይገባል፡፡”

አባ አብርሃም ወልደ ኢየሱስ የምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም አበምኔት


  • “ሥልጠናው ገዳማት እርስ በርሳችን እንድንተዋወቅ አድርጎናል፡፡ እንደ 120 ቤተሰቦች ነው የሆንነው፡፡ ገዳማት ከገዳማት መተዋወቅ የአንዱን ተሞክሮ ሌላው መስማትና መመልከት መቻሉ ለወደፊት የተሻለ ነገር እንድንሠራ ያደርገናል፡፡”

ቆሞስ ደሴ ዓለም የጎጃም ደጋ ዳሞት ደብረ ፀሐይ ዋልጣ ቅድስት ማርያም ገዳም አበምኔት

 

ማኅበረ ቅዱሳን ይህንን መርሐ ግብር በሚያካሒድበት ወቅት ከገዳማውያን አባቶች በረከት ያገኙ ዘንድ በመስተንግዶ እንዲራዱ ለማኅበራትና ለምእመናን ባደረገው ጥሪ መሠረት መንፈሳዊ ማኅበራትና በጎ አድራጊ ምእመናን ምላሻቸውን በመስጠት የመነኮሳቱንና መነኮሳይያትን እግር በማጠብ፤ የምግብና መጠጥ ወጪ በመሸፈንና በማስተናገድ ከፍተኛ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ማኅበራትና ምዕመናን ላበረከቱት ድጋፍ ማኅበሩ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡