hawire ticket

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ሊካሔድ ነው

የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

hawire ticket

ማኅበረ ቅዱሳን በ2005 ዓ.ም. የሐዊረ ሕይወት /የሕይወት ጉዞ/ የተሰኘውና ወደ ቅዱሳን መካናት፤ አድባራትና ቤተ ክርስቲያናት የሚያካሄደውን የጉዞ መርሐ ግብር በሆለታ ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን መጋቢት 22 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደሚያካሄድ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ገለጹ፡፡

hawire 1

 

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በ2003 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን ለአራተኛ ጊዜ እንደሚከናወን የገለጹት ምክትል ዋና ጸሐፊው የትኬት ሽያጩንም ከሰኞ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በማኅበሩ የንዋያተ ቅድሳትና የኅትመት ውጤቶች መሸጫ ሱቆች፤ እንዲሁም በማኅበሩ ዋና ጽሕፈት ቤት እንደሚጀመር፤ የቲኬት ሽያጩንም ከጉዞው አሥር ቀን ቀደም ብሎ እንደሚጠናቀቅና በጉዞውም ከዚህ በፊት በተከታታይ ከተደረጉት ጉዞዎች በላቀ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ምእመናን ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ምእመናን አሳባቸውን ሰብስበው በተረጋጋ መንፈስ ሆነው ከበረከቱ ይሳተፉ ዘንድ የአጽዋማት ወቅቶች የተሻሉ በመሆናቸው ጉዞው መዘጋጀቱን አብራርተዋል፡፡

 

የጉዞውን ጠቀሜታ ሲገልጹም “ትልቁ ጠቀሜታው  ምእመናን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ዙሪያ ያሏቸው ጥያቄዎች ከታላላቅ ሊቃውንት መልስ የሚያገኙበት፤ እንዲሁም  የወንጌል ትምህርት ለምእመናን በስፋት የሚሰጥበት ነው” ብለዋል፡፡

 

hawire 2ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ  በደብረ ጽጌ ቅድስት ማርያም ገዳም፤ በፍቼ ቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን፤ እንዲሁም በበኬ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ምእመናን ከወዲሁ ትኬቱን በብር 120፡00 /አንድ መቶ ሃያ/ በመግዛት በጉዞው እንዲሳተፉ የማኅበሩ ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡