‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)

ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡…ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡

የስሜት ሕዋሳቶቻችንና ክርስትና

ሰው በልዩ ልዩ ሁኔታዎች ውስጥ ሲገኝ የሚሰማውን ስሜት በስሜት ሕዋሳቱ አማካኝነት ይገልጣቸዋል፡፡ ደስታ፣ ቁጣ፣ ፍርሃት፣ ሕመም፣ ፍቅር እና የመሳሰሉት ስሜቶቻችን ናቸው፡፡ ሰው እነዚህን ስሜቶቹን በስሜት ሕዋሳቱ በዐይኑ፣ በእጁ፣ በእግሩ፣ በአንደበቱ፣ በፊት ገጽታውና በሰውነት እንቅስቃሴው ይገልጣል፡፡ እነዚህ ስሜቶች ከሚቀሰቀሱበት ሁነቶች፣ ድርጊቶችና ክስተቶች አንጻር በፍጥነት ምላሽ ሳይሰጥ ነገሮችን በዕርጋታ የሚመረምር ሰው በሳል ወይም ባለ አእምሮ ይባላል፡፡ በተቃራኒው ለጉዳዮች ፈጣን ምላሽ የሚሰጠውን ደግሞ ስሜታዊ እንለዋለን፡፡ ባለ አእምሮ ሰው በመረጋጋቱ ብዙ ሲያተርፍ ስሜታዊ ሰው ግን የሚያጸጽቱና ግላዊ፣ ማኅበራዊ እንዲሁም ሀገራዊ ጥፋቶችን የሚያስከትሉ ዋጋዎችን ይከፍላል፡፡ በመሆኑም መጽሐፍ “እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ” በማለት ያስተምረናል፡፡ (፩ኛጴጥ.፬፥፯-፰)

በዓለ ቅድስት ሥላሴ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? አሜን! የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን! በዓለ ቅድስት ሥላሴን በተመለከተ አጭር ጽሑፍ አቅርበንላችኋል፤

ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አባቶቻችን ሐዋርያትን ሰማዕትነት በተቀበሉበት ቀናት በዓላት ሰይማ ታከብራቸዋለች፡፡ እንዲሁም በስማቸው የተሰየመውን ጾም በመጾም አሠረ ፍኖታቸውን ይከተሉ ዘንድ ምእመናንን ታሳስባለች፡፡ በሐምሌ ፭ ቀን ደግሞ የደጋጎቹን ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስን በዓል ታደርጋለች፡፡ የእነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን በዓል መደረጉ በአንድ ቀን ሰማዕትነት በመቀበላቸው ነው፡፡

ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በተለምዶ የሰኔ ጾም እየተባለ የሚታወቀው ጾመ ሐዋርያት ሰኔ ፲፯ (ዐሥራ ሰባት) ቀን ተጀምሮ እስከዚህ ዕለት ደርሷል፡፡ ይህ ጾም ከሰባቱ የዐዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ አገልግሎታቸውን በጸሎትና በጾም ጀምረዋል፤ እኛም እነርሱን አብነት አድርገን በዓለ ጰራቅሊጦስ ከተከበረበት ማግሥት አንሥቶ እስከ ሐምሌ አራት ቀን ድረስ እንጾመዋን፡፡ከዚያም በኋላ ሐምሌ አምስት ቀን የጾሙ ፍቺ ይሆናል፡፡ በዚህም ቀን የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስ የዕረፍት በዓል ነው፡፡

መልካም ልጆች! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! ባለፈው ምሥጢረ ቁርባንን ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ የምሥጢረ ትንሣኤ ሙታንን ትምህርት እንማራለን፡፡ ተከታተሉን!

‹‹ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል›› (ሐዋ.፭፥፳፱)

መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ይህንን ቃል የተናገሩት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዓለም ለይቶ የጠራቸው፣ የመረጣቸው በመሆናቸው ነው። በዓለም እየተዘዋወሩ ቅዱስ ቃሉን በሚያስተምሩበት በስሙ ተአምራት በሚያደርጉበት ጊዜ ፈተና ነበረባቸው፤ እንቅፋት ያጋጥማቸው ነበረ። ብዙዎች በምቀኝነትና በቅናት እየተነሣሡ እንዳያስተምሩ ይከለክሏቸው ነበረ፤ ይናገሯቸውም ነበረ። በዚህ ሰዓት ነበር ቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባናል›› በማለት ያስተማሩት፤ እግዚአብሔር እንዲያስተምሩ አዟቸው ነበርና። (ሐዋ.፭፥፳፱)

‹‹በዚያን ጊዜ ይጾማሉ›› (ማቴ.፱፥፲፮)

 ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወስድበት ወራት ይመጣል፤ በዚያን ጊዜም ይጾማሉ›› (ማቴ.፱፥፲፴-፲፮)

‹‹ይፈኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ፤ አጽናኝ መንፈስ ይልክላችኋል›› (ዮሐ.፲፬፥፲፮)

የቤዛነት ሥራውን ከፈጸመ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ሲያርግ ለሐዋርያት የሰጣቸው ተስፋ አጽናኝና የእውነት መንፈስ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን አብ እንደሚልክላቸው፣ እርሱም አጽናኝ የሆነ ጰራቅሊጦስ እንደሆነ ለዘለዓለሙም ከእነርሱ ጋር እንደሚሆን ነግሯቸው ነበር፡፡ ጌታችን እንደተናገረውም በሰጣቸው ተስፋ መሠረት ባረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሣ ደግሞ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡

ምሥጢረ ጥምቀት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዓለ ሃምሳ ተብሎ የሚታወቀውን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? መቼም ልጆች! ጾም የለም ብላችሁ ጸሎት ተግቶ ከመጸለይ፣ ቤተ ክርስተያን በሰንበት በዕረፍት ጊዜያችሁ ሄዶ ማስቀደስን እንደማትዘነጉ ተስፋ እናደርጋለን! 

በዘመናዊ ትምህርታችሁም ሁለተኛው የመንፈቀ ዓመት እየተገባደደ በመሆኑ ለማጠቃለያ ፈተና የምትዘጋጁበት ወቅት በመሆኑ በርትታችሁ አጥኑ፤ መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ‹‹ምሥጢረ ጥምቀትን›› ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ምሥጢረ ጥምቀትን ቀጣይ ክፍለ ትምህርት እንማራለን፤ ተከታተሉን!

‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ›› (ማቴ.፯፥፲፫)

ወዳጄ ሆይ! የምትጓዝበትን መንገድ የማታውቅ ከሆነ ትጠፋለህና በየትኛው መንገድ ላይ ልትራመድ እንደሚገባህ ልታገናዝብ ያስፈልግሃል። በፊትህ ሰፊ፣ አታላይና ጠባብ መንገዶች አሉና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ በማለት አስጠንቅቋቸዋል። ‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና፤…፡፡›› (ማቴ.፯፥፲፫)