DSC09260

የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ ሁሉም በጸሎት እንዲያስብ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለፓትርያርክነት እጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

አስመራጭ ኮሚቴው በአንድ ሳምንት ውስጥ አከናወንኳቸው ያላቸውን ሥራዎች ባቀረበበት በዚሁ መግለጫ በርካታ ምእመናን ለቤተ ክርስቲያኒቱ 6ኛ ፓትርያርክ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉትን አባት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በፋክስ መልእክት በመላክ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጧል፡፡ ከካህናትና ምእመናን የተገኘው ጥቆማም ለአስመራጭ ኮሚቴው በግብአትነት የሚያገለግል ሲሆን ከየካቲት 9 -14 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያቀርብ መግለጫው አመልክቷል፡፡ የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ካህናትና ምእመናን እግዚአብሔርን በጸሎት እንዲጠይቁ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ አስመራጭ ኮሚቴው ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡

ከጋዜጠኞች ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል ምርጫው ከሌሎች ተጽእኖ ምን ያህል የፀዳ ነው? የሚለውን ለቀ ማዕምራን ፋንታሁን ሙጬ የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ምላሽ የሰጡ ሲሆን አስመራጭ ኮሚቴው ከሌሎች አካላት ተጽእኖ የጸዳና ራሱን ችሎ የተሰጡትን ኃላፊነቶች በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡  የአኀት ቤተ ክርስቲያንና የሲቪክ ማኅበራት ምርጫውን ለመታዘብ ይገኛሉ? የሚለውን ሲመልሱም ከአኀት ቤተ ክርስቲናት፤ ከአለም አብተ ክርስቲናት ምክር ቤት፤ ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ ከታዋቂ አገር ሽማግሌዎችና ከመንግስት አካላት በታዛቢነት እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

በስፋት ጥቆማ እየሰጡ የሚገኙት የአዲስ አበባ ካህናትና ምእመናን ናቸው፡፡ ሌሎቹ አህጉረ ስብከቶችስ? በሚል ለቀረበው ጥያቄም ሲመልሱ “በርቀት ምክንያት በአካል መቅረብ ያልቻሉ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ ላይ ሁለት ፋክስ ቁጥሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ ፋክሶቹም 24 ሰዓት በመስራት ከአውሮፓና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጥቆማዎችን እንደተቀበሉና በአካል ቀርበው ጥቆማቸውን የሚሰጡትንም በተዘጋጀው ቅጽ ላይ ሞልተው በታሸገው የጥቆማ መስጫ ሳጥን ውስጥ እያስገቡ ይገኛሉ” ብለዋል፡፡

በፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ ላይ እጩ የሚሆኑትን አባቶች ከተለዩ በኋላ ከምእመናን የሚቀርቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ለመቀበል የ15 ቀናት የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን አስመራጭ ኮሚቴው የገለጸው በሦስት ቀናት ልዩነት ፓትርያርክ ሆነው የሚመረጡት አባት እንደሚታወቁ ነው፡፡ ይህ አካሔድ ከሕገ ደንቡ ጋር አይጋጭም? የሚለውንም ሲመልሱ “ከምርጫ ሕገ ደንቡ ጋር ተያዞ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጸድቆ ለአስመራጭ ኮሚቴው የተሰጠ ተጨማሪ ሕግ አለ፡፡ አስመራጭ ኮሚቴውን በሚያስመርጥበት ወቅት ኮሚቴው ሊሰሯቸው የሚገባውን ተግባራት ቋሚ ሲኖዶስ እየተከታተለ አስፈላጊውን ለውጥ ማድረግ እንደሚችል የተገለጸበት ሕግ ነው፡፡ ይህንን ሕግ ተከትሎ የድርጊት መርሐ ግብር አዘጋጅቶ ነው አስመራጭ ኮሚቴው ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀረበው፡፡  ቋሚ ሲኖዶስ የቅዱስ ሲኖዶስም ምልዓተ ጉባኤ በሰጠው ሥልጣንና ውክልና መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ያቀረበውን የጊዜ ሰሌዳ ትክክል ነው ብሎ አጽድቆ ሰጥቶታል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ሕግ የማውጣትም ሆነ ሕግ የመለወጥ ስልጣን የለውም” በማለት የመለሱ ሲሆን ስለቀኑ ማጠር ሲያብራሩም ወደ አብይ ጾም የተቃረበ በመሆኑ ከዚያ በፊት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ግንዛቤ ተወስዶ እንደተከናወነ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ከ53ቱም አህጉረ ስብከቶች ለመራጭነት ይገኛሉ ተብሎ ይፋ የተደረገው 800 መራጮች ብቻ ናቸው ፡፡ ነገር ግን ሲሰላ ከዚያ በላይ ስለሚሆኑ እንዴት ይታያል? በማለት ለቀረበው ጥያቄም በፓትርያርክ ምርጫው ላይ በመራጭነት የሚሳተፉ ሰዎች 800 ይሆናል የሚለውም እንደ መነሻ የተያዘ እንጂ የመጨረሻ ቁጥር ያለመሆኑን ያብራሩ ሲሆን የአስመራጭ ኮሚቴው አባላትም ከጋዜጠኞች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተጨማሪ ምላሽ በመስጠት ተሳትፈዋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክን ጨምሮ 13ቱም አስመራጭ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል፡፡

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የካቲት 18 ቀን አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ለምእመናን በይፋ እንደሚገለጹ፤ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ የተመረጡት ፓትርያርክ በመገናኛ ብዙሃን እንደሚገለጽና የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. በዓለ ሲመት እንደሚከናወን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

የካቲት 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስሰ


DSC09260

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለፓትርያርክነትእጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

 

አስመራጭ ኮሚቴው በአንድ ሳምንት ውስጥ አከናወንኳቸው ያላቸውን ሥራዎች ባቀረበበት በዚሁ መግለጫ በርካታ ምእመናን ለቤተ ክርስቲያኒቱ 6ኛ ፓትርያርክ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉትን አባት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በፋክስ መልእክት በመላክ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጧል፡፡ ከካህናትና ምእመናን የተገኘው ጥቆማም ለአስመራጭ ኮሚቴው በግብአትነት የሚያገለግል ሲሆን ከየካቲት 9 -14 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያቀርብ መግለጫው አመልክቷል፡፡ የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ካህናትና ምእመናን እግዚአብሔርን በጸሎት እንዲጠይቁ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡  እጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

 

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ አስመራጭ ኮሚቴው ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡

 

ከጋዜጠኞች ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል ምርጫው ከሌሎች ተጽእኖ ምን ያህል የፀዳ ነው? የሚለውን ለቀ ማዕምራን ፋንታሁን ሙጬ የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ምላሽ የሰጡ ሲሆን አስመራጭ ኮሚቴው ከሌሎች አካላት ተጽእኖ የጸዳና ራሱን ችሎ የተሰጡትን ኃላፊነቶች በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡  የአኀት ቤተ ክርስቲያንና የሲቪክ ማኅበራት ምርጫውን ለመታዘብ ይገኛሉ? የሚለውን ሲመልሱም ከአኀት ቤተ ክርስቲናት፤ ከአለም አብተ ክርስቲናት ምክር ቤት፤ ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ ከታዋቂ አገር ሽማግሌዎችና ከመንግስት አካላት በታዛቢነት እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

 

በስፋት ጥቆማ እየሰጡ የሚገኙት የአዲስ አበባ ካህናትና ምእመናን ናቸው፡፡ ሌሎቹ አህጉረ ስብከቶችስ? በሚል ለቀረበው ጥያቄም ሲመልሱ “በርቀት ምክንያት በአካል መቅረብ ያልቻሉ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ ላይ ሁለት ፋክስ ቁጥሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ ፋክሶቹም 24 ሰዓት በመስራት ከአውሮፓና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጥቆማዎችን እንደተቀበሉና በአካል ቀርበው ጥቆማቸውን የሚሰጡትንም በተዘጋጀው ቅጽ ላይ ሞልተው በታሸገው የጥቆማ መስጫ ሳጥን ውስጥ እያስገቡ ይገኛሉ” ብለዋል፡፡

 

በፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ ላይ እጩ የሚሆኑትን አባቶች ከተለዩ በኋላ ከምእመናን የሚቀርቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ለመቀበል የ15 ቀናት የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን አስመራጭ ኮሚቴው የገለጸው በሦስት ቀናት ልዩነት ፓትርያርክ ሆነው የሚመረጡት አባት እንደሚታወቁ ነው፡፡ ይህ አካሔድ ከሕገ ደንቡ ጋር አይጋጭም? የሚለውንም ሲመልሱ “ከምርጫ ሕገ ደንቡ ጋር ተያዞ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጸድቆ ለአስመራጭ ኮሚቴው የተሰጠ ተጨማሪ ሕግ አለ፡፡ አስመራጭ ኮሚቴውን በሚያስመርጥበት ወቅት ኮሚቴው ሊሰሯቸው የሚገባውን ተግባራት ቋሚ ሲኖዶስ እየተከታተለ አስፈላጊውን ለውጥ ማድረግ እንደሚችል የተገለጸበት ሕግ ነው፡፡ ይህንን ሕግ ተከትሎ የድርጊት መርሐ ግብር አዘጋጅቶ ነው አስመራጭ ኮሚቴው ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀረበው፡፡  ቋሚ ሲኖዶስ የቅዱስ ሲኖዶስም ምልዓተ ጉባኤ በሰጠው ሥልጣንና ውክልና መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ያቀረበውን የጊዜ ሰሌዳ ትክክል ነው ብሎ አጽድቆ ሰጥቶታል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ሕግ የማውጣትም ሆነ ሕግ የመለወጥ ስልጣን የለውም” በማለት የመለሱ ሲሆን ስለቀኑ ማጠር ሲያብራሩም ወደ አብይ ጾም የተቃረበ በመሆኑ ከዚያ በፊት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ግንዛቤ ተወስዶ እንደተከናወነ ገልጸዋል፡፡

 

በመጨረሻም ከ53ቱም አህጉረ ስብከቶች ለመራጭነት ይገኛሉ ተብሎ ይፋ የተደረገው 800 መራጮች ብቻ ናቸው ፡፡ ነገር ግን ሲሰላ ከዚያ በላይ ስለሚሆኑ እንዴት ይታያል? በማለት ለቀረበው ጥያቄም በፓትርያርክ ምርጫው ላይ በመራጭነት የሚሳተፉ ሰዎች 800 ይሆናል የሚለውም እንደ መነሻ የተያዘ እንጂ የመጨረሻ ቁጥር ያለመሆኑን ያብራሩ ሲሆን የአስመራጭ ኮሚቴው አባላትም ከጋዜጠኞች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተጨማሪ ምላሽ በመስጠት ተሳትፈዋል፡፡

 

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክን ጨምሮ 13ቱም አስመራጭ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል፡፡

 

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የካቲት 18 ቀን አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ለምእመናን በይፋ እንደሚገለጹ፤ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ የተመረጡት ፓትርያርክ በመገናኛ ብዙሃን እንደሚገለጽና የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. በዓለ ሲመት እንደሚከናወን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡