ሆሣዕና በአርያም

ሆሣዕና በአርያም . . . ሆሣዕና በአርያም

ለዳዊት ልጅ መድኃኔ ዓለም

በጌታ ስም የሚመጣ

ከምርኮ ሀገር ከባርነት የሚያወጣ

ኒቆዲሞስ

ኒቆዲሞስ ‹‹ቀናዕያንና ወግ አጥባቂዎች›› ከሚባሉት ፈሪሳውያን አለቆች አንዱ ነበር።…

‹‹አቤቱ፥ እስከ መቼ ፈጽመህ ትረሳኛለህ? እስከ መቼስ ፊትህን ከእኔ ትመልሳለህ?›› (መዝ. ፲፪፥፩)

አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር መኖራችንን የረሳን ይመስለናል፤ መከራ ውስጥ ሆነን እንዲሁም ሥቃያችን በዝቶ ልንቋቋመው ከምንችለው በላይ ሲሆንብን እግዚአብሔር እንደረሳን እናስባለን፡፡ ‹‹እግዚአብሔር በእውነት እኔን ያውቀኛል? ያስታውሰኛልን?›› ብለንም በመጠራጠር እራሳችንን እንጠይቃለን፤ ‹‹ዓለም ላይ ከሚኖረው ሕዝብም ለይቶ አያውቀኝም›› ወደ ማለትም እንደርሳለን፡፡ ሆኖም ግን በእግዚአብሔር ዘንድ እንኳን ሰው እንስሳም ይታወቃል፡፡ በሕይወታችን ውስጥም የሚያጋጥሙን ችግርና መከራ እንዲቀርፍልን ለእግዚአብሔር በመስጠት እንጸልይ፤ ከመከራም እንዲያሳርፈን እንማጸነው፡፡

‹‹ጌታውን ደስ ያሰኘ ታማኝና ቸር አገልጋይ ማነው?›› ቅዱስ ያሬድ

በዚህ ዘመን በየትኛውም መንገድ ቢሆን ታማኝነት የጠፋበት፣ እኛ ሰዎች በተለያዩ ነገሮች ራሳችንን በመተብተብ ከእግዚአብሔር ኅብረት ተለይተን ማገልገልን ለተወሰኑ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ብቻ የሰጠን ሁነናል፡፡ በዚህም በቤተክርስቲያንና በአማኞቿ ላይ ብዙ ችግሮች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆነናል፤ አሁንም ቢሆን ከተኛንበት መንቃት ያስፈልገናል፡፡

‹‹ተቈጡ፤ አትበድሉም›› (ኤፌ. ፬፥፳፮)

ቊጣ ተገቢ እንደሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በጻፈው መልእክቱ ‹‹ተቈጡ፤ አትበድሉም፤ ፀሐይ ሳይጠልቅም ቊጣችሁን አብርዱ›› በማለት ተናግሯል፡፡ ከሰዎች ጋር በሚኖረን ግንኙነት ውስጥ እውነት ሲጠፋ ወይንም ሐሰት ሲንሰራፋ ኃጢአትን በመንቀፍ መቈጣታችን ተገቢ ነው፡፡ ሰዎችን ከስሕተት እና ጥፋት ለመመለስ መቈጣት የተፈቀደ እንደሆነ በዚሁ እንረዳለን፡፡ ሆኖም ግን ከልክ ባለፈ ቊጣ የሰዎችን ስሜት በመጕዳት መበደል ኃጢአት ነው፡፡ ይህም ማለት ትክክል ያልሆነን ነገር ስንመለከትና ስንሰማ ወይንም ስሕተት ሲፈጸም አይተንና ሰምተን ብንቈጣ ተገቢ ሆኖ ሳለ የመቈጣታችን ስሜት ግን ለመፍትሔ እንጂ ለባሰ ጥፋት የሚዳርግ ከሆነ እንዲሁም የተቈጣንበት ነገር አግባብነት ከሌለው የማይገባ ቊጣ እንደሆነ መረዳት ይኖርብናል፤ የሚገባ ቊጣ ሲሆን ግን ትክክል መሆኑን በዚሁ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ (ኤፌ. ፬፥፳፮)

‹‹የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድነው?›› (ማቴ.፳፬፥፫)

በዓለም ፍጻሜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጻድቃንን በቀኙ ኃጥአንን ደግሞ በግራው ለይቶ እንደየሥራችን ሊፈርድ ይመጣልና ምልክቶቹን እናውቅ ዘንድ በወንጌል ተጽፎልናል፡፡

‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው፤ በመከራ ቀን መሸሸጊያ ነው›› (ናሆም ፩፥፯)

እግዚአብሔር አምላክ የሰዎችን ደኅነትን የሚሻ መልካም አባት በመሆኑ ልጆቹን ከመከራ ይሸሽጋል፡፡ በዘመነ ኦሪት እስራኤላውያን በግብፅ በባርነት ሲኖሩ ከመከራ ሠውሯቸዋል፤ ነፃ ሊያወጣቸውም ፈቅዶ ነቢዩ ሙሴን እንዲህ አለው፤ ‹‹እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ከግብፃውያንም ተገዥነት አወጣችኋለሁ፥ ከባርነታችውም አድናችኋለሁ፤ በተዘረጋ ክንድ፤ በታላቅ ፍርድም እታደጋችኋለሁ፥ ለእኔም ሕዝብ እንድትሆኑ እቀበላችኋለሁ፥ አምላክም እሆናችኋለሁ፤ እኔም ከግብፃውያን ባርነት ያወጣኋችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደሆንሁ ታውቃላችሁ፡፡›› (ዘፀ. ፮፥፮-፯)

መፃጒዕ

በዘመነ ሥጋዌ በኢየሩሳሌም ውስጥ ይኖሩ የነበሩ በተለያየ ሕመም ይሠቃዩ የነበሩ ሰዎች ለመፈወስ የሚሰበሰቡባት ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፡፡ አምስትም መመላለሻ ነበራት፡፡  በዚያም ብዙ ድውያን ይተኛሉ፤ ከእነርሱም ውስጥ የታወሩ፣ አንካሾች፣ የሰለሉ፣ ልምሹ የሆኑ፣ በየእርከን እርከኖች ላይ ይተኙ ነበር፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም ውኃውን ለመቀደስ በሚወርድ ጊዜ ድምፁ እስኪያስተጋባ ድረስ ውኃው ይናወጣል፡፡ ድውያኑም በዚያ ሥፍራ ተኝተው የውኃውን መናወጥ ይጠባበቃሉ፡፡ ምክንያቱም በዕለተ ሰንበት (ቀዳሚት) ውኃው ሲናወጥ ቀድሞ ወደ ውኃው የገባ አንድ ሰው ከደዌው ይፈወስ ነበርና፡፡…

የሻጮችና የለዋጮች ወንበር የሞላው ቤተ መቅደስ

ጥንቱን ለልማዱ የቤተ መቅደስ መሠራት ምክንያቱ ሰዎችን ለመቀደስ፣ ሕያዊት ነፍስ የተሰጠቸው ሥጋዊ ደማዊ ፍጥረት ሁሉ ጸሎቱን አድርሶ መሥዋዕቱን አቅርቦ ከእግዚአብሔር ምሕረት ሊቀበልበት አልነበረምን? ‹‹ለዘለዓለም ስሜ በዚያ ያድር ዘንድ ይህን የሠራኸውን ቤት ቀድሻለሁ ዓይኖቼና ልቤም በዘመኑ ሁሉ በዚያ ይኖራሉ›› ብሎ የመረጠው የነገሥታት ንጉሥ የእግዚአብሔር ልዩ ሥፍራ ነው ቤተ መቅደስ፡፡ መቅረዙና ጠረጴዛው የመሥዋዕቱም ኅብስት ነበረበት፤ የወርቁ ማዕጠንት፣ ሁለንተናዋም በወርቅ የተለበጠች የኪዳን ጽላት፣ በውስጧም መናን የተሸከመችው መሶበ ወርቅና ክህነት የጸናባት የአሮን በትር እንዲኖሩ ታዝዞ ነበር፡፡  በምድራውያን ሰዎች መካከል እንደ ምሰሶ የሚቆመው ካህን ገብቶ የሚያጥንበት ይህ ቤተ መቅደስ ምንኛ የከበረ ነው? ለሰዎች ሁሉ ራዕይን አይቶ የሚነግራቸው ባለ ራዕይ ነቢይ የማይታጣበት፣ ሊቀ ካህናቱ የሚደገፈው ያቁም፣ ንጉሡ የሚደገፈው በለዝ የሚባሉት ምሰሶዎች የሚገኙበትም ነው፡፡ ያዕቆብ እንዳለው ይህ ቤተ መቅደስ የሰማይ ደጅ ነው እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ (፩ ነገ. ፱÷፫፣ ዕብ. ፱÷፪፣ ዘፍ. ፳፰÷፲፯)

‹‹የሚራሩ ብፁዓን ናቸው›› (ማቴ.፭፥፯)

መራራት ማለት ምሕረት ማድረግ፣ ቸርነት፣ ለተጨነቀ ወይም ለተቸገረ ማዘንና ርዳታን መስጠት፣ ይቅር ማለት፣ ማዘን፣ ወዘተ ሲሆን ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ ተብሎ በሁለት ሊከፈል ይችላል።