‹‹አንተ ሰይጣን፤ ከአጠገቤ ሂድ!›› (ማቴ.፬፥፱)

መቈጣት ተገቢ የሚሆንበት ጊዜ አለ፤ ሊቃውንቱ እንዲህ ዓይነቱን ቊጣ ‹‹መዓት ዘበርትዕ›› ይሉታል፤ የሚገባ ቊጣ ማለታቸው ነው፡፡ ቊጣና ተግሣጽ ከሚያስፈልጋቸው ፍጥረታት አንዱ ሰይጣን ነው፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ይገባውና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቈጥቶ የሚያውቀው በአይሁድና በአጋንንት ላይ ነው፡፡ ሰይጣንን ተቈጥቶ ካስወገደበት ቀን አንዱ ይህ ዛሬ የምናነሣው ነው፡፡ ሰይጣን አፍሮ ከኛ የሚርቅባት ቀን ምንኛ የተባረከች ቀን ናት? ጌታ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ገባ፡፡ ካመኑ ከተጠመቁ በኋላ ወደ መንፈሳዊው ዓለም መጓዝ ይገባል ማለቱ ነው፡፡ ገዳም ገብቶ አርባ ቀንና አርባ መዓልት ጾመ ጸለየ፡፡ ሲጠመቅ በመጠመቁ ዋጋ የሚያገኝበት ሆኖ አይደለም፡፡ ውኆችን ለማክበር በጥምቀት ምእመናን እንዲወለዱ ጥምቀትን የጸጋ ምንጭ ሊያደርጋት ተጠምቋል እንዳልን በመጾሙና በመጸለዩም እንደ ኤልያስ ወደ ሰማይ ያረገ፣ እንደ ዳንኤል የአንበሳን አፍ የዘጋ፣ እንደ ሙሴም ሕግን የተቀበለበት አይደለም፡፡ ጾምና ጸሎት ዋጋ ማሰጠታቸውን አውቀው ከእሱ በኋላ የተነሡ ምእመናን እንዲይዙት ለማስተማር ነው፡፡ በዚያውም ላይ ጥንቱንም የጎዳን መብልና መጠጥ ነው፤ አሁንም ነፍሳችን የምትታደሰው በጾምና በጸሎት ስለሆነ ነው፡፡

የአሰቦት ቅድስት ሥላሴና የአባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም ደን ተቃጠለ

የአሰቦት ቅድስት ሥላሴና የአባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም ደን መንሥኤው ባልታወቀ እሳት መቃጠሉን የገዳሙ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ በመጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም የጀመረውን እሳት ለማጥፋት ርብርብ ቢደረገም ከሰው ዐቅም በላይ በመሆኑ ማጥፋት አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡ የገዳሙ መነኰሳት፣ ከሐረር፣ ድሬዳዋና አሰበ ተፈሪ የተሰባሰቡ ምእመናን እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ቃጠሎውን ለማስቆም ቢሞክሩም ጥረታቸው ባለመሳካቱ ደኑ በመቃጠል ላይ ይገኛል፡፡ አካባቢውም ንፋሳማ በመሆኑ በተለይም ምሽት ላይ የሚነፍሰው ኃይለኛ ንፋስ ቃጠሎውን በማባባሱ እሳቱ ደኑን ጨርሶ ወደ ገዳሙ በመድረስ እንዳያቃጥለውም ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረ የገዳሙ አበምኔት አባ ተክለ ማርያም አስታውቀዋል፡፡

‹‹እግዚአብሔርም የፈጠረው ሁሉ እጅግ ያማረ እንደሆነ ተመለከተ›› (ዘፍ.፩፥፴፩)

በባሕርዩ ክቡር የሆነው እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ ክቡር ነው። ይሁን እንጂ አበው በብሂላቸው ‹‹ከጣትም ጣት ይበልጣል›› እንዲሉ እጅግ የከበሩ ፍጥረታትም አሉ። ከእነዚህ እጅግ የከበሩ ፍጥረታት ከሚባሉት መካከል በቀዳሚነት የሚገኘው የሰው ልጅ ነው። ስለዚህ የሥነ ፍጥረትን ታሪክ የጻፈልን ሊቀ ነቢያት ሙሴ ሁሉንም ፍጥረታት ከፈጠረ በኋላ ‹‹መልካም እንደሆነ አየ›› እያለን ይመጣና ሰው ላይ ሲደርስ ግን ‹‹እጅግ መልካም እንደሆነ አየ›› በማለት ይደመድማል። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ‹‹ሰንበት ተዐቢ እምኵሉ ዕለት ወሰብእ ይከብር እምኵሉ ፍጥረት፤ ከዕለታት ሰንበት ትበልጣለች፤ ከፍጥረታትም ሁሉ ሰው ይበልጣል›› በማለት እንደነገረን የሰውን ልጅ እጅግ ክቡር ፍጥረት መሆኑን ያስረዳናል። የሰው ልጅ ክቡርነት በተመለከተ መጻሕፍት አምልተውና አስፍተው ይናገራሉ። (ዘፍ.፩፥፴፩)

‹‹የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ›› (ዮሐ.፪፥፲፮

በኢየሩሳሌም፤ ምኵራብ ተብሎ በተሰየመው የዐቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት ዕለተ እሑድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ፤ አይሁድ ንጉሥ ናቡከደነፆር ቤተ መቅደስን ካፈረሰባቸው በኋላ ሕገ ኦሪትን መማሪያ እና መጸለያ ስፍራ በማጣታቸው የሠሩት አዳራሽ ምኵራብ ነበርና፡፡ በዚያም ጌታችን በሬዎችንና በጎችን፥ ርግቦችንም የሚሸጡትን፥ ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው ባገኘ ጊዜ ያየውን ባለመውደዱ የገመድ ጅራፍ ካዘጋጀ በኋላ በጎችንና በሮዎችን እንዲሁም ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣቸው፤ የሻጮቹንም ገንዘብ በተነባቸው፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፤ ርግብ ይሸጡ የነበሩትን ደግሞ፤ ‹‹ይህን ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ አላቸው፡፡›› (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)

ቅድስት

ቅድስት የሚለው ቃል ትርጉሙ ‹‹የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች›› ማለት ነው። ሥርወ ቃሉም ‹‹ተቀደሰ›› ሲሆን ፍቺው ደግም ‹‹ክቡር፣ ምስጉን፣ ምርጥ›› ማለት ነው፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጾም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፯፻፹፬)

‹‹ኢየሱስን በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው ይህ ነው›› (ራእ. ፲፬፥፲፪)

በዮሐንስ ራእይ ላይ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ኢየሱስን በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው ይህ ነው›› በማለት የተናገረው ኃይለ ቃል የመጨረሻውን ዘመን አስጨናቂ እና ፈታኝ መሆን እንዲሁም ክርስቲያኖች ይህን ተረድተው በትዕግሥት መጽናት እንደሚገባቸው ለማስረዳት ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ቁጥር ፲፩ ላይ ለአውሬውና ለምስሉ የሚሰግዱ፣ የስሙንም ምልክት የሚጽፉ ሁሉ ቀንና ሌሊት ዕረፍት እንደሌላቸው፣ ሕዝብንና አሕዛብን ስለሚፈትነው፣ በመጨረሻ ዘመን ስለሚነሣው አውሬ እና በእርሱም ምክንያት ብዙዎች ወደ ዘለዓለማዊ እሳት እንደሚጣሉም ይገልጻል፡፡ (ራእ. ፲፬፥፲፪)

ዐቢይ ጾም

ዐቢይ ማለት ታላቅ የከበረ ማለት ሲሆን ዐቢይ ጾም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ በገዳመ ቆሮንቶስ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት ከቆመ ሳያርፍ ከዘረጋ ሳያጥፍ በትኅርምት የጾመው ታላቅ ጾም ነው፡፡ በተለይም የዲያብሎስን ሦስቱን ፈተናዎች ውድቅ ያደረገበት፤ በፍቅረ ንዋይ የመጣውን በጸሊዐ ንዋይ በትዕቢት የመጣውን በትሕትና በስስት የመጣውን በቸርነት ድል ያደረገበትም ነው፡፡ (ማቴ. ፬፥፩)

‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› (ሚል ፫፥፯)

የሰው ልጆችን ጥፋት የማይወደው ፈጣሪያችን እግዚአብሔር በንስሓ እንድንመለስ ይሻል፤ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› ብሎም ዘወትር ወደ እርሱ ይጠራናል፡፡ (ሚል ፫፥፯)

‹‹በወንድማማችነትም ፍቅርን ጨምሩ›› (፪ ጴጥ. ፩፥፯)

በክርስቲያናዊ ሕይወት ውስጥ ፍቅር ልባዊ መዋደድ ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ፍቅር ሲገልጽ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹ፍቅር ያስታግሣል፤ ፍቅር ያስተሳዝናል፤ ፍቅር አያቀናናም፤ ፍቅር አያስመካም፤ ፍቅር ልቡናን አያስታብይም፡፡ ብቻዬን ይድላኝ አያሰኝም፤ አያበሳጭም፤ ክፉ ነገርንም አያሳስብም፡፡ ጽድቅን በመሥራት ደስ ያሰኛል እንጂ፥ ግፍን በመሥራት ደስ አያሰኝም፡፡ በሁሉ ያቻችላል፤ በሁሉ ያስተማምናል፤ በሁሉም ተስፋ ያስደርጋል፥ በሁሉም ያስታግሣል፤ ፍቅር ለዘወትር አይጥልም፡፡›› (፩ ቆሮ. ፲፫፥፬-፰)

‹‹አቤቱ፥ እንደ አዘዝህ ዛሬ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ›› (ሉቃ.፪፥፳፱)

ቅዱስ ስምዖን ይህን ቃል የተናገረው በ፭፻ ዓመቱ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መወለድ በክንዱ ታቅፎ ከመሰከረ በኋላ ከፈጣሪው እግዚአብሔር ዘንድ መኖርንም ተመኝቶ በተማጸነበት ጊዜ ነው፡፡ ይህም የሆነው እንዲህ ነበር፤ …