የነነዌ ጾም

እግዚአብሔር አምላካችን ወዶ እና ፈቅዶ ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ለሆነው የነነዌ ጾም አድርሶናል፡፡ ሦስት ቀናት የሚጾመው ይህ ጾም የነነዌን ሕዝብ ከጥፋት መመለስ፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እንዲሁም የነቢዩ ዮናስን የዋህነት ያስረዳናል፡፡

ስእለት

ስእለት ማለት ልመና፣  ምልጃ፣ ጸሎት፣ ጥየቃ እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ ገልጸዋል፡፡ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ስእለት ይሳላሉ፡፡ ለምሳሌ ‹‹እግዚአብሔር የልቤን ጭንቀት ቢፈጽምልኝ እንዲህ አደርግለታለሁ፡፡ እመቤቴ ማርያም ስእለቴን ወይንም ልመናዬን ብትሰማኝ ለቤተ ክርስቲያን እንዲውል ጃን ጥላ አስገባለሁ››  ብለው ይሳለሉ፤ ወይንም አቅማቸው የፈቀደውን ነገር እንደሚሰጡ ቃል ይገባሉ፡፡ ስእለታቸውም ሲደርስ ‹‹እመቤታችን እንዲህ አድርጋልኛለች›› ብለው ለክብሯ መገለጫ ድባብ ወይንም የተሳሉትን ነገር ለቤተ ክርስቲያን ይሰጣሉ፡፡(ገጽ ፰፻፵፪)

ዶክተር ብርሃኑ ተሾመ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ!

ዶክተር ብርሃኑ ተሾመ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ፵፩ ዓመቱ ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞተ ተለይተዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም በደብረ ምጥማቃት ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል የካቲት ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፈጽሟል፡፡

‹‹አሁንስ ተስፋዬ ማነው? እግዚአብሔር አይደለምን?›› (መዝ.፴፰፥፯)

በእግዚአብሔር ተስፋ መኖር በእርሱ ላይ ሙሉ እምነት እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ እግዚአብሔር ከጎናችን ሲሆንም እያንዳንዳችን ከምናስበው ዳርቻ መድረስ እንችላለን፡፡ ስለዚህ ተስፋችን የሚወሰነው በአምላካችን ላይ ባለን የእምነት ጥንካሬ ነው፡፡ ተስፋ በሕይወታችን ውስጥ ወደፊታችን የምንራመድበት መወጣጫ ድልድይ፣ የኑሮአችን መሠረት እንዲሁም የደስታችን መጀመሪያ ነው፤ በተስፋ ኖረን ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት እንሸጋገራለንና፡፡

‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ ትጸድቃለህ፤ ከአነጋገርህ የተነሣ በቃልህ ይፈረድብሃልና›› (ማቴ. ፲፪፥፴፯)

በአንደበታችን የምንናገረው ነገር መልካም ሲሆን ጽድቅ ሆኖ እንደሚቆጠርልን ሁሉ መጥፎ ከሆነ ደግሞ ኃአጢት ይሆንና በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂ ያደርገናል፡፡ ኃጢአት በአብዛኛው ከንግግር የሚመነጭ ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው ‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ ትጸድቃለህ፤ ከአነጋገረህ የተነሣ በቃልህ ይፈረድብሃልና።›› ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከት ውስጥ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ ‹‹በወንድሙ ላይ በከንቱ የሚቈጣ ሁሉ እርሱ ይፈረድበታል፤ ወንድሙንም ጨርቅ ለባሽ የሚለው በአደባባይ ይፈረድበታል፡፡›› (ማቴ. ፲፪፥፴፯፣፭፥፳፪)

ቅዱስ ወንጌል

ወንጌል፡- ወንጌል የሚለው ቃል ‹‹ሄዋንጌሊዎን›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ እንደሆነና በግእዝ ቋንቋም ብሥራት፣ ምሥራች፣ አዲስ ዜና፣ መልካም ወሬ፣ ደስ የሚያሰኝ፣ ስብከት ማለት እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ይገልጻሉ፡፡ (በመጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ ገጽ ፫፻፺፬)

ጽድቅ

ጽድቅ ማለት እውነት፣ ርግጥ፣ ቅንነት እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ መጽሐፋቸው ውስጥ ገልጸዋል፡፡ በመጽሕፍ ቅዱስ ላይ እንደተጻፈው ደግሞ ሰው በእግዚአብሔር ታምኖ በፊቱም ክብርና ሞገስ የሚያስገኝለት በጎ ሥራ ጽድቅ ይባላል፡፡ ‹‹መጽሐፍ፥ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ፤ ጽድቅ ሆኖም ተቈጠረለት የሚለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ፤ ሰው በሥራ እንደሚጸድቅ በእምነት ብቻም እንዳይደለ ታያለህን? እንዲሁ ዘማይቱ ረአብ ደግሞ ጕበኞችን ተቀብላ፥ በሌላ መንገድ ባወጣቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን? ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው›› እንዲል፤ (ገጽ ፯፻፵፮፣ ያዕ. ፪-፳፬-፳፮)

ቃና

ጥምቀት

በዘመነ ሥጋዌ በናዝሬት ከተማ፤ ዮርዳኖስ ወንዝ የእስራኤል ሕዝብ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ተራ ይዘው በሚጠብቁበት ጊዜ እርሱ እንዲህ እያለ ይሰብክ ነበር፤ ‹‹እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው መቅሠፍት ታመልጡ ዘንድ ማን ነገራችሁ? እንግዲህ ለንስሓ የሚያበቃችሁን ሥራ ሥሩ፤ አብርሃም አባታችን አለን በማለት የምታመልጡ አይምሰላችሁ፤ እግዚአብሔር ከእነዚህ ድንጋዮች የአብርሃም ልጆችን ማንሣት እንደሚችል እነግራችኋለሁ፡፡ እነሆ፥ ምሳር በዛፎች ላይ ተቃጥቶአል፤ መልካም ፍሬ የማያፈራውን ዛፍ ሁሉ ይቈርጡታል፤ ወደ እሳትም ይጥሉታል፡፡›› (ሉቃ.፫፥፯-፱)

ሕዝቡም ምን ቢያደርጉ እንደሚሻል በተራ በተራ ይጠይቁት ጀመር፤ እርሱም ለእያንዳንዱ ሲመልስ፤ ሁለት ልብስ ያለው አንዱን ለሌለው እንዲሰጥ፣ ለተራበ እንዲያበላ፣ ቀራጮችን ደግሞ ከታዘዙት አትርፈው አንዳይውስዱ እንዲሁም ጭፍሮችን በማንም ላይ ግፍ እንዳይፈጽሙ እየመከረ አጠመቃቸው፡፡ እነርሱም በልባቸው እጅግ እያደነቁ ከጌታችን ኢየሱስ ጋር መሰሉት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን እንዲህ አላቸው ‹‹እኔ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ግን የሚበልጠኝ የጫማውን ማሰሪያ እንኳን ልፈታለት የማይገባኝ ይመጣል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ፣ በእሳትም ያጠምቃችኋል፡፡›› (ሉቃ.፫፥፲፮-፲፯)

ሕዝቡ ሁሉም ከተጠመቁ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሊጠመቅ ወደ እርሱ ሲጠጋ ቅዱስ ዮሐንስ ግን ‹‹እኔ በአንተ ልጠመቅ እሻለሁ፤ አንተ ወደ እኔ ትመጣለህን?›› በማለት ከለከለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ አሁንስ ተው፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናልና›› አለው፡፡ እርሱም ተወው፤ ጌታችን ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያውኑ ከውኃ ወጣ፤ በዚይች ቅጽበትም ሰማይም ተከፈተ፤ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥ አየ፡፡ እነሆም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይህ ነው የሚል ድምጽ ከሰማይ መጣ፡፡›› (ማቴ.፫፥፲፫-፲፯)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ልጁ መሆኑን እግዚአብሔር አብ ልጄ ብሎ መሰከረ፤ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወረደ፤ ወልደ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ተጠምቆ በፅንፈ ዮርዳኖስ ታየ፡፡
እግዚአብሔር አምላክም ለአዳም የገባለነትን ቃል ለመፈጸም አንድ ልጁን ልኮ ከኃጢአት ባርነት አወጣው፡፡ ስለዚህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው አዳምን እና ሔዋንን ከባርነት ነፃ ለማውጣትና ድኅነት ሊሆናቸው ነውና በጥምቀቱ ጊዜ በዮርዳኖስ ወንዝ በሰይጣን ተቀብሮ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤያቸውን ቀደደላቸው። ይህንንም ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት ተናግሮታል። ‹‹እናንተም በበደላችሁና ሥጋችሁን ባለመገረዝ ሙታን በሆናችሁ ጊዜ፥ ከእርሱ ጋር ሕይወትን ሰጣችሁ። በደላችሁን ሁሉ ይቅር አላችሁ። በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰ፤…።›› (ቆላ.፪፥፲፫-፲፬)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለነፍሳችን ድኅነት ይሆነን ዘንድ ተጠምቆ አርአያ ሆኖናል፡፡ በጥምቀቱም ጥምቀትን ባርኮልናል፤ በኦሪት ጥምቀት ሥጋን እንጂ ነፍስን አይፈውስምና እርሱ በተጠመቀው ጥምቀታችን ተባረከልን፡፡
እኛም ስንጠመቅ በአዳም በደል ተወስዳ የነበረች ልጅነታችን ተመልሶ፣ የዕዳ ደብዳቤያችንም እንዲደመሰስልን አስረዳን፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም ቀደማዊና ደኃራዊ እንደሌለው እንደተመሰከረ እኛም ስንጠመቅ ከሥላሴ መወለዳችን ይረጋገጥልና፡፡ (ዮሐ. ፫፥፭፣ የሐዋ. ፪፥፴፰፣ ቆላ. ፪፥፲፩-፲፬)

ጥምቀት ለክርስቲያኖች ሁለተኛ ልደታቸው ነው፡፡ ከሥጋ የተወለደ ሁሉ ወደ ፈቃደ ሥጋው ስለሚያደላ መንፈሳዊ ልደት ያስፈልገዋል፡፡ ‹‹ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ወደ የእግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡›› (ዮሐ. ፫፥፫-፭)
በዘመነ ብሉይ ይፈጸም የነበረው ጥምቀት የንስሓ ጥምቀት ነበር፡፡ በሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ንስሓ ግቡ ኃጢአታችሁ ይሠረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ›› ብሏቸው እንደተናገረው ጥምቀት ኃጢአትን ያስተርይልናል፡፡ (ሐዋ. ፪፥፴፯-፴፰)
በሐዲስ ኪዳን የሚፈጸመው ግን የልጅነት ጥምቀት ነው፤ ይህን ተከትሎ ወንድ ልጅ በዐርባ ሴት ልጅ በሰማንያ ቀን ይጠመቃሉ፡፡ የዚህም ምክንያት አዳም በተፈጠረ በ፵ ቀኑ፣ ሔዋንም በተፈጠረች በ፹ ቀኗ ወደ ርስታቸው ገነት እንደገቡ ሕፃናትም በ፵ እና በ፹ ቀናቸው ተጠምቀው የሰማያዊት ኢየሩሳሌም አምሳል ወደሆነችው ወደ ቤተ ክርስቲያን ይገባሉ፡፡
በተጨማሪም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እኛ ሁላችን በሞቱ እንደተጠመቅን ሁላችሁ ይህን ዕወቁ፤ እኛ ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን? እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደተነሣ እንዲሁ እኛ በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን›› በማለት በጥምቀት ክርስቶስን እንደምንመስለው ተናግሯል፡፡ ‹‹ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን›› የሚለውን በገቢር ለመግለጽ እንዲሁም ‹‹በጥምቀት ደግሞ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር ሥራ በማመናችሁ ከእርሱ ጋር ተነሳችሁ›› ያለውን እንዲሁ በድርጊት ለማሳየት ነው፡፡ (ሮሜ ፮፥፫-፬፣ቆላ. ፪፥፲፪)

‹‹ያመነ የተጠመቀ ይድናል፤ ያላመነ ያልተጠመቀ ይፈረድበታል›› እንደተባለው ከገሃነመ እሳት ፍርድ እንድናለን። ሰው ክርስቲያን ይባል ዘንድ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ማግኘት አለበት፡፡ ይህም በልጅነት የሚያገኘው በረከት በተቀደሰ ውኃ በመጠመቁ ነው፡፡ ካልሆነ ግን የእርኩስ መፈንስ ማደሪያ ወይንም መናፈቅ ይሆናል ማለት ነው፡፡ (ማር. ፲፮ ፥ ፲፮)
በእምነት ለተጠመቀ ሰው ግን ጥምቀት ፈውሰ ሥጋን እንዲሁም ፈውሰ ነፍስን ይሰጣል፤ ምክንያቱም እምነት ኃይልን ታደርጋለችና ጥምቀት ድኅነት መሆኑን አምነን ከተጠመቅን ኃጢአታችን ይሠረይልናል፤ ይህም ጌታችን ጥምቀትን ባርኮ ስለሰጠን በምሥጢረ ጥምቀት የምንረዳው ነው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ የጥምቀትን ሥርዓት ከመሰረተልን በኋላ ደቀ መዛሙርቱን በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም የሰውን ዘር እንዲያጠምቁ አዟቸዋል፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተከታዮች በሙሉም በምሥጢረ ጥምቀት እንደምንረዳው ሥርዓቱን ጠብቀን እንጠመቃለን፤ ይህም ሥርዓት ከዋዜማው ከተራ ጀምሮ የሚፈጸም ነው፡፡ (ማቴ. ፳፰፥፲፱-፳)
የጥምቀት በዓል በእነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት እና ተግባር የሚያመለክቱ ብዙ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓቶች ይከናወናሉ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጠፋውን ፍጥረቱን ፍለጋ ወደ ዓለም እንዴት እንደወረደ የሚገልጹ ያሬዳዊ ዝማሬዎች እና መዝሙሮች በከተራ ይዘመራሉ፡፡

ሁሉም የቃል ኪዳኖች (ታቦቶች) በእያንዳንዱ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በአቅራቢያው ውኃ ወዳለበት ወደ ጅረት ገንዳ ይሄዳሉ፡፡ የዚህም ምሥጢር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከኢየሩሳሌም ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ እንዴት እንደሄደ የሚያሳይ ነው፤ አንድ ሌሊት ማሳለፉ ጌታችን በትህትና የእርሱን ተራ መጠበቁን የሚያሳይ ነው፡፡ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ከተጠመቁት ሕዝቦች መካከል ተጠምቋልና፡፡ ይልቁንም ተራውን በመጠበቅ የትህትናን ተግባር አሳይቶናል፡፡ ታቦታቱም ከሕፃናት፣ ከወላጆች፣ ከወጣቶች፣ ከአረጋዊያን፣ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች፣ ከቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እና ከሌሎችም ምእመናን ጋር በሁሉም ክርስቲያኖች ይታጀባሉ፡፡

ሌሊቱን በውዳሴ በማኅሌት ካሳለፉ በኋላ ውኃው በፓትርያኩ፣ በሊቀ ጳጳሳት እና በካህናት ከመባረኩ በፊት ማለዳ ቅዳሴ ይጀምራል፤ ምእመናንም የቅዳሴ አካል ለመሆን ቀደም ብለው ይገኛሉ፡፡ ሃይማኖት አባቶችም ውኃውን በአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ከባረኩት በኋላ ወደ ተሰበሰቡት ክርስቲያኖች በብዛት ውኃውን ለመርጨት ዝግጅት ያደርጋሉ፡፡

በዚያን ጊዜ ክርስቲያኖች በሺዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በፊት በዓይነ ኅሊናቸው ወደኋላ በመመለስ የጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት በማሰብ ከተረጩ በኋላ በደስታ ታቦታቱን በኅብረት ወደየቤተ ክርስቲያን በማጀብ ይጓዛሉ፤ ካህናቱም የያሬድን ዝመሬ በመዘመር በዓሉን ያከብራሉ፡፡

ሕፃናት፣ ወጣቶች እንዲሁም አረጋዊያን በሙሉ በዝማሬው ይሳተፋሉ። የቅዱሱ ታቦትም በደኅና ወደ መንበሩ ሲመለስ ሕዝቡ በመንፈሳዊ ደስታ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን በዚህ አስደናቂ እና መንፈሳዊ ክርስቲያናዊ ምግባር አማካኝነት የእግዚአብሔርን ልጅ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወደሱን የቀጠልን ሲሆን ለመጪው ትውልድም ይህንኑ እንድናስተላልፍ በእምነት እና ሃይማኖት ልንጸና ይገባል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ በጥምቀቱ ፈውሰ ሥጋንና ፈውሰ ነፍስን ያድለን ዘንድ ፍቃዱ ይሁንልን፤ አሜን!

ልደተ ክርስቶስ

‹‹እነሆ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፡፡…››