የተስፋው ቃል

በአንዲት ፍሬ ቅጠል ሕይወትን አጥቼ
ርስቴን ተነጠኩ የሞት ሞትን ሙቼ
በግዞት ተነዳሁ በድቅድቅ ጨለማ
ወደ ፍዳ መንደር ወደ ሞት ከተማ…

ልደቱ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት

ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሆኖ የሥላሴን መንበር ያጠነው ጻድቁ አባት አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱበት ዕለት የተቀደሰች ናት፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ለአባታቸው ካህኑ ጸጋ ዘአብና ለእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ ባበሠራቸው መሠረትም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ ኢቲሳ በሚባል ቦታ በታኅሣሥ ፳፬፤ ፲፪፻፲፪ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ በሦስተኛው ቀን እሑድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ አንዱ አብ ቅዱስ ነው፤ አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው፤ አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ!›› (ማቴ.፯፥፲፭)

ነቢይ ማለት ተነበየ፣ ተናገረ ከሚለው የግእዝ ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም ወደፊት ስለሚሆነውና ስለሚመጣው አስቀድሞ መናገር፣ መተንበይ ማለት ነው፡፡ ከዚህም በተመሳሳይ ‹ናቪ› ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተገኘ ስያሜ ነው፤ መምራት፣ ማብሠር፣ መምከር፣ መንገር የሚል ትርጓሜም አለው፡፡ ይህ ቃል ወደ ግሪክ ሲተረጎም ‹ፕሮፌቴስ› ወይንም ‹ፕሮ› እና ‹ፌሚ› ከሚሉት ጥምር-ቃላት የተገኘ በመሆኑ ‹ፕሮ› ቅድሚያ፣ ከአንድ ነገር በፊት ማለትን ሲያመለክት ‹ፌሚ› ደግሞ መናገር፣ ማብሠርና ማሳወቅ ማለት እንደሆነ መምህር ብዙነሽ ስለሺ ‹ትምህርተ ሃይማኖት› በተሰኘው መጽሐፋቸው ውስጥ ገልጸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ‹ፕሮፌቴስ› የወደፊቱን ነገር አስቀድሞ መናገር፣ ማብሠር ወይም ማሳወቅ የሚል ትርጓሜ እንዳለው እንረዳለን፡፡ ምዕራባውያን በመጽሐፍ ቅዱሳቸው ውስጥ ቃሉን ‹ፕሮፌት› በሚለው ሲጠቀሙ የሴሜቲክ ቋንቋ ዘር የሆነው ግእዝ ከዕብራይስጡ ቃል ‹ናቪ› የሚቀራረብ ትርጓሜ በመውሰድ ነቢይ የሚለውን ቃል ይጠቀማል፡፡ (ትምህርተ ነቢያት ገጽ ፲፩)