መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
ቅዱስነታቸው በጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
ቅዱስነታቸው በጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል እየተዘጋጀ የሚቀርበው የጥናትና ምርምር ጉባኤ ታኅሣሥ 22/2015 ዓ.ም በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ 3ኛ ፎቅ በርካታ ምእመናን በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በዕለቱ ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፤ ከእነዚህም “ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና እና እስልምና በኢትዮጵያ ዕቅበተ እምነታዊ ጉዳዮች” በሚል የቀረበው አንዱ ነው። ኢትዮጵያ ሀገራችን በ6ኛ መ/ክ የነበራት ግዛትና ተጽእኖ እስከ ዓረቢያን ምድር የሰፋ እንደነበረ የተለያዩ ድርሳናት እንደሚመሰክሩ በጥናቱ መግቢያ ተጠቁሟል። ይህን የግዛት ወሰን ተከትሎ በአቅራቢያ ከሚገኙ የዓረብ ሀገራት ጋር በተለያዩ መንገዶች ለመገናኘት በር ከፍቷል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በቀድሞው አጠራር ጎንደር ክፍለ ሀገር በአሁኑ በደቡብ ጎንደር ዞን በአንዳቤት ወረዳ ልዩ ስሙ አረጊት ኪዳነ ምሕረት ገዳም አካባቢ ከአባታቸው ከብላታ ፈንታ ተሰማና ከእናታቸው ከወ/ሮ ለምለም ገሠሠ በ ፲፱፻፴ ዓ.ም ተወለዱ፡፡
የአሰቦት ቅድስት ሥላሴና የአባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም ደን መንሥኤው ባልታወቀ እሳት መቃጠሉን የገዳሙ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ በመጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም የጀመረውን እሳት ለማጥፋት ርብርብ ቢደረገም ከሰው ዐቅም በላይ በመሆኑ ማጥፋት አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡ የገዳሙ መነኰሳት፣ ከሐረር፣ ድሬዳዋና አሰበ ተፈሪ የተሰባሰቡ ምእመናን እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ቃጠሎውን ለማስቆም ቢሞክሩም ጥረታቸው ባለመሳካቱ ደኑ በመቃጠል ላይ ይገኛል፡፡ አካባቢውም ንፋሳማ በመሆኑ በተለይም ምሽት ላይ የሚነፍሰው ኃይለኛ ንፋስ ቃጠሎውን በማባባሱ እሳቱ ደኑን ጨርሶ ወደ ገዳሙ በመድረስ እንዳያቃጥለውም ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረ የገዳሙ አበምኔት አባ ተክለ ማርያም አስታውቀዋል፡፡
ዶክተር ብርሃኑ ተሾመ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ፵፩ ዓመቱ ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞተ ተለይተዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም በደብረ ምጥማቃት ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል የካቲት ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፈጽሟል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኢሬኔጅ የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ።
የ፳፻፲፫ መስቀል ደመራ በዓል የኮሮና በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ አምስት ሺህ ተሳታፊዎች ብቻ በተገኙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ተከብሯል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን የፀጥታ ሥጋት እንዳለባቸው ለዝግጅት ክፍላችን ተናገሩ፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የሀዋሳ ማእከል ሕግና ዕቅበተ እምነት አገልግሎት ዋና ክፍል ተጠሪ የነበሩት አቶ አስማማው ታመነ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በደረሰባቸው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው እንዳለፈ የሀዋሳ ማእከል አስታወቀ፡፡
