‹‹ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ›› (ማቴ. ፲፮፥፲፰)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የዓመቱ የትምህርት ወቅት እየተገባደደ የፈተና ጊዜ ደርሶ እየተፈተናችሁ ያላችሁ ተማሪዎች አላችሁና ፈተና እንዴት ነው? መቼም በደንብ እንዳጠናችሁ ተስፋችን እሙን ነው! ወደፊት መሆን የምትፈልጉትን ለመሆን በትምህርታችሁ ጎበዝ መሆን አለባችሁ!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትርጉምና በመጀመሪያ ስለታነጸው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በጥቂቱ እንነግራችኋለን፤ መልካም ቆይታ!

ቅድስት አመተ ክርስቶስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ የትምህርት ወቅት አልቆ የፈተና ጊዜ በመድረሱ ለመፈተን ዝግጅት ላይ የሆናችሁም ሆነ የተፈትናችሁ በጥሩ ውጤት ወደ ቀጣዩ ክፍል እንደምትዘዋወሩ መልካም ምኞታችን ነው! ልጆች! በምድረ በዳና በተራራ በዋሻና በምድር ጉድጓድ ተቅበዘበዙ››  በማለት እንደገለጸው ዓለምን ንቀው በበረሃ በተጋድሎ ሕይወት የኖሩ ብዙ አባቶችና እናቶች አሉ፡: ለዛሬ የኑሯቸውን ፍሬ ተመልክተን፣ በእምነት እንመስላቸው፣ በምግባር እንከተላቸው ዘንድ ምሳሌ ከሚሆኑን ከቅዱሳን እናቶቻችን መካከል አንዷ ስለሆነችው ስለ ቅድስት አመተ ክርስቶስ ታሪክ በጥቂቱ ልንነግራችሁ ወደድን። መልካም ንባብ!

ቅዱሰ ኤጲፋንዮስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የዓመቱ የትምህርት ወቅት እየተገባደደ የፈተና ጊዜ እየደረሰ ነው፡፡ተፈትናችሁ በጥሩ ውጤት ወደ ቀጣዩ ክፍል ለመዘዋወር እየበረታችሁ ነውን? ልጆች! ‹‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ። የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው›› እንደተባልነው የኑሯቸውን ፍሬ ተመልክተን በእምነት እንመስላቸው፣ በምግባር እንከተላቸው ዘንድ ምሳሌ ከሚሆኑን ከቅዱሳን አባቶቻችን አንዱ ስለሆነው ስለቅዱስ ኤጲፋንዮስ ታሪክ በጥቂቱ ልንነግራችሁ ወደድን፤ መልካም ንባብ!

ቅዱስ ማርቆስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ምሕረት፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችን ተበሥሮልን ከዛሬ ዕለት ደረስን! በቸርነቱ ለዚህ ያደረሰን ፈጣሪ ይመስገን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላቸሁ የወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስን ታሪክ ነው፡፡

እንኳን ለበዓለ ትንሣኤ አደረሳችሁ!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? እንኳን ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ቸርነት የጾሙ ጊዜ ተፈጽሞ፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችን ለተበሠረበት ዕለት ደረስን! በቸርነቱ ለዚህ ያደረሰን ፈጣሪ ይመስገን!

ሰሙነ ሕመማት

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ሰነበታችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የዐቢይ ጾም ወቅትንስ እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ይህ ጾም ጠላታችን ዲያቢሎስ ያፈረበት፣ ትዕቢት፣ ስስት፣ፍቅረ ንዋይ ድል የተደረጉበት፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጹሞ እንጾም ዘንድ ባርኮ የሰጠን ታላቅ ጾም ነው፡፡ ታዲያ ይህን ወቅት መልካም ሥራ እየሠራን፣ ለሀገር፣ ለቤተ ክርስቲያን እየጸለያችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋ እናደርጋለን! መልካም!

ውድ የእግአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት በዐቢይ ጾም ስለሚገኙ ሳምንታት ስያሜ ባስተማርናችሁ መሠረት በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? አሁን ደግሞ ስለ ሰሙነ ሕማማት ጥቂት ልናካፍላችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ

የዐቢይ ጾምና ሳምንታቱ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ?! የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፤ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፡፡

ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ከጸሎትና ከስግደት ጋር እንዲሁም ትምህርት በማይኖረን በዕረፍት ጊዜያችን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ፣ ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!

ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜ ስለ ዐቢይ ጾምና በጾሙ ወቅት ስላሉት ሳምንታት እስከ እኩለ ጾም ድረስ ተመልክተናል፤ ለዛሬ ደግሞ ቀጥሎ ያለውን እንመለከታለን፤ መልካም ንባብ!!!

‹‹ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊትም ጾመ›› (ማቴ.፬፥፪)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የመንፈቀ ዓመቱ ትምህርት ተጠናቆ ፈተና ተፈትናችሁ ጥሩ ውጤት እንዳመጣችሁ ተስፋችን ነው፤ በርቱ!
ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ ዐቢይ ጾም ነው፤ ዐቢይ ማለት ታላቅ ማለት ነው፤ አባቶቻችን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት ከሰባት ዓመት በላይ የሆኑ ክርስቲያኖች ሁሉ እንዲጾማቸው የታወጁ ሰባት አጽዋማት አሉ፤ ከእነዚህ መካከል ደግሞ አንዱ ዐቢይ ጾም ነው::

ቃል ኪዳን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንጉሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…እናንት ልጆች የአባትን ተግሣጽ ስሙ፤ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ›› (መዝ.፬፥፩) በማለት እንደተናገረው የአባቶቻችሁን ተግሣጽ (ምክርና ቁጣ) ሰምታችሁ፣ በእግዚአብሔር ጥበቃ ከትላንት ዛሬ የደረሳችሁ ልጆች! ለዚህ ያደረሰንን እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ታሪክ ስለ እመቤታችን ቃል ኪዳን ነው፤ ቃል ኪዳን ማለት ‹‹ውል ወይም ስምምነት›› ማለት ነው፤ እግዚአብሔር ከአባቶቻችን ጋር በተለያየ ጊዜ ቃል ኪዳንን ገብቷል፤ እንደ ትእዛዙ ለሚኖሩ የሚፈልጉትን ሊያደርግላቸው ቃል ኪዳንን ሰጥቷቸዋል፤ በነቢዩ ሕዝቅኤል ‹‹የሰላምም ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር አደርጋለሁ፤ ዘለዓለም ቃል ኪዳን ይሆንላቸዋል፤ እኔም እባርካቸዋለሁ፤ አበዛቸውማለሁ፤ መቅደሴንም ለዘለዓለም በመካከላቸው አኖራለሁ…›› (ሕዝ.፴፯፥፳፮) በማለት ነግሮናል፡፡

ሀልዎተ እግዚአብሔር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው እየበረታችሁ ነውን? በርቱ!
ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለእግዚአብሔር መኖር (ሀልዎተ እግዚአብሔር) በተሰኘ ርእስ ይሆናል፤ እንደተለመደው በአጽንኦት (በትኩረት ሆናችሁ) እንድትማሩ አደራ እንላለን፡፡