በዓለ ጥምቀት

የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ! ልጆች! የጌታችንን የልደት በዓልን እንዴት አሳለፋችሁ? በሰላም እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው፤ ትምህርትስ እንዴት ነው? የግማሽ መንፈቀ ዓመት ፈተናም እየደረሰ ነውና በርትታችሁ አጥኑ!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ዛሬ ደግሞ ስለ ጥምቀት በዓል እንማማራለን፡፡ ጥምቀት ማለት ‹‹አጥመቀ- አጠመቀ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ‹‹መነከር፣ መድፈቅ፣ በተባረከው ውኃ ጸበል ውስጥ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ›› ማለት ነው፤ እንግዲህ በዛሬ ትምህርታችን ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት እንመለከታለን፡፡

‹‹እነሆ በኤፍራታ ሰማነው በዱር ውስጥም አገኘነው›› (መዝ.፻፴፩፥፮)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ! እግዚአብሔር አምላካችን የተመስገነ ይሁን! ዛሬ የምናስተምራችሁ ስለ ጌታችን አምላካችን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነው፡: በጥሞና ተከታተሉን!

የቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› (መዝ.፳፪፥፲) በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን፤ አሜን!

የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለተከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹… እግዚአብሔር ሕፃናትን ይጠብቃል…›› በማለት እንደተናገረው በእግዚአብሔር ጥበቃ በሰላምና በጤና እንደቆያችሁልን ተስፋችን የታመነ ነው፡፡ (መዝ.፻፲፬፥፮)

ጾም

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡ ባላችሁበት ሆናችሁ ትምህርታችሁን  በጥሞና ተከታተሉ!
ልጆች! ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው ትምህርት ስለ ጾም ነው፡፡ በመጀመሪያ ጾም ምን ማለት እንደሆነ እና እናንተ ሕፃናት ከሰባት ዓመት ዕድሜያችሁ ጀምሮ እንዴት መጾም እንዳለባችሁ እናስተምራችኋለን፡፡

ጸሎት በቤተ ክርስቲያን

የተወዳዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡ በቤታችሁ ሆናችሁ ትምህርታችሁን በጥሞና ተከታተሉ!

ልጆች ዘወትር ጸልዩ!

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡

ልጆች የዛሬ ትምህርታችን ስለጸሎት ነው፤ በመጀመሪያም የቃሉን ትርጉም እንመልከት፡፡…

ማማተብ

ሰላም ልጆች እንደምን አላችሁ? ደኅና ናችሁ? መቼም እግዚአብሔር ይመስገን እንዳላችሁ  ተሰፋ አደርጋለሁ፡፡ ልጆች ምንጊዜም ቢሆን እግዚአብሔርን ማመስገን መዘንጋት የለብንም እሺ?  ምክንያቱም እኛ ሰዎች የተፈጠርነው  ለምስጋና ስለሆነ ነው፡፡ ስለሆነም ልጆች በዚህ ክፍል በአጭሩ ሰለ ማማተብ እንማማራለን፡፡ እስኪ ስለማማተብ ምን ታውቃላችሁ ልጆች? የማማተብ ትርጉሙስ ምንድ ነው ትላላችሁ? እንግዲያውስ ዛሬ ስለማማተብ አጭር መርጃ ይዠላችው ቀርቤለሁ፤ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ፡፡

ፈረሰኛው ቅዱስ ጊዮርጊስ

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? ደህና ናችው? እግዚያብሔር ይመስገን እንዳላችሁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ልጆች! ትምህርት እንዴት ነው? ከዓለማዊው ትምህርታችሁ ጎን ለጎን እናንተን ያስተምራል እንዲሁም በምግባር ያንጻል ብለን ያሰበነውን ታሪክ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ልጆች በዚህ ዕትማችን ይዘንላችሁ የቀርብነው የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን ታሪክ ነው፡፡ ከታሪኩ ብዙ እንደምትማሩ ተስፋ እናደርጋለን፤ በጽሞና እንድታነቡም ተጋብዛችኋል፤ መልካም ንባብ ይሁንላችው፡፡