ሥነ ፍጥረት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ዐቢይ ጾምን እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ባለፈው ትምህርታችን ዕድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ማንኛውም ክርስቲያን ጾምን መጾም እንዳለበት በተማርነው መሠረት እንደ ዓቅማችሁ እየጾማችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው! መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፡፡ ባለፈው “የእግዚአብሔር ባሕርያት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር ስለፈጠራቸው ፍጥረታት እንማራለን!

የእግዚአብሔር ባሕርያት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን!  እንኳን ለታላቁ ዐቢይ ጾም አደረሳችሁ! በዚህ ጊዜ ግን ልጆች ከሰባት ዓመት ጀምሮ መጾም እንደሚጀመር እናስታውሳችሁ! መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፡፡ ባለፈው “ሀልዎተ እግዚአብሔር” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ የእግዚአብሔር ባሕርያት ምን እንደሆኑ እንማራለን!-

ሀልዎተ እግዚአብሔር

ዲያቆን ተስፋዬ ቻይ 

የካቲት ፳፮፤፳፻፲፮ ዓመተ ምሕረት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? የግማሽ ዓመት ትምህርት ተጀምሯልና በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በነበረው የትምህርት ወቅት ደከም ያለ ውጤት ያስመዘገባችሁበትን ትምህርት በደንብ ትኩረት ሰጠታችሁ በመማር ማሻሻል ይገባል! ቤተ ክርስቲያን በመሄድም መንፈሳዊ ትምህርት መማርንም አትዘንጉ! ደግሞም ፳፻፲፮ ዓ.ም. (የሁለት ሺህ ዐሥራ ስድስት) ዐቢይ ጾም መጋቢት ሁለት ይጀምራልና ከምንጊዜውም በተለየ መልኩ በጸሎት መትጋት አለብን፡፡  ዕድሜያችን ከሰባት ዓመት በላይ የሆነን ደግሞ እንደ አቅማችን መጾም አለብን! መልካም!!!

ልጆች! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! በባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን “ሃይማኖት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ “ሀልዎተ እግዚአብሔር” ማለትም ዓለምን ሁሉ የፈጠረ የአምላካችን የእግዚአብሔር መኖር በምን እንደሚታወቅ እንማራለን፤ ተከታተሉን!

“ሀልዎት” ማለት “መኖር” ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፫፻፸) ሀልዎተ እግዚአብሔር ስንል ደግሞ የእግዚአብሔር መኖር ማለታችን ነው፤ ባለፈው ትምህርታችን ላይ ሁሉን ያስገኘና የፈጠረ እግዚአብሔር መሆኑን ያወቅነው በሃይማኖት እንደሆነ እንደተማራችሁት ዛሬ ደግሞ “የእግዚአብሔር መኖር በምን ይታወቃል የሚለውን በተወሰነ መልኩ እንማማራለን፡፡

የአምላካችን የእግዚአብሔር መኖር ከሚታወቅባቸው ነገሮች አንዱ ሥነ ፍጥረት ነው፤ ለዚህ ዓለም ፈጣሪ (አስገኚ) አለው፤ የሚታየውን እንደገናም እኛ የማናያቸውን ፍጥረታት ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ጻድቁ ኢዮብ እንዲህ ሲል መስክሯል፤ ‹‹አሁን ግን እንስሶችን ጠይቅ፤ ያስተምሩህማል፤ የሰማይንም ወፎች ጠይቅ፤ ይነግሩህማል፤ ወይንም ለምድር ተናገር፤ እርስዋም ታስተምርሃለች…፡፡›› (ኢዮብ ፲፪፥፯) አያችሁ ልጆች! እግዚአብሔር የሁሉ ፈጣሪ መሆኑን እንስሳትም እንኳን ምስክር ይሆነናሉ፡፡

ሌላው ደግሞ ልጆች! ነቢዩ ኢሳይያስ አምላካችን እግዚአብሔር ፍጥረታትን እንደፈጠረ እንዲህ ነግሮናል፤ ‹‹…ሠሪውም እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ ስለሚመጣው ነገር ጠይቁኝ፤  …እኔ ምድርን ሠርቻለው፤ ሰውንም በእርሷ ላይ ፈጥሬአለሁ፤ እኔ በእጄ ሰማያትን ዘርግቻለው…፡፡››     (ኢሳ. ፵፭፥፲፩-፲፪)

ደግሞም መጽሐፍ ቅዱስን ገና ስንገልጠው ባለው በኦሪት ዘፍጥረት ላይ እንዲህ የሚል ቃል አለ፤ ‹‹በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ…፡፡›› (ዘፍ.፩፥፩) እንግዲህ ልጆች! እግዚአብሔር የዚህ ዓለም ፈጣሪ እንደ ሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ማስረጃዎች አሉ፤ ለግንዛቤ ያህል ግን ይህን አቀረብን፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እግዚአብሔር ለመኖሩ ሌላው ምስክር ደግሞ ፍጥረታትን ስንመለከት ሁሉም ሥርዓታቸውን ጠብቀው መንቀሳቀሳቸውን ስንረዳ ነው፡፡ ለምሳሌ ፀሐይን ብንወስድ ጠዋት ከምሥራቅ ወጥታ ማታ በምዕራብ ትጠልቃለች፤ ጨለማና ብርሃን፣ ሌሊትና ቀንም፣ ክረምትና በጋም ይፈራረቃሉ፤ የእነዚህ ፍጥረታት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዳለ ያስረዳሉ፤ እኛም የሰው ልጆች እግዚአብሔር እንዳለ ምስክሮች ነን፡፡

ልጆች! ሃይማኖት ያለው ሰው እግዚአብሐር እንዳለ ያምናል፤ ይመሰክራልም፤ አንዴ ምን ሆነ መሰላችሁ? የእግዚአብሔር ወዳጅ አብርሃም አባታችን ቤተ ሰቦቹ ጣዖት የሚያመልኩ ነበሩ፡፡ ጣዖት ታውቃላችሁ አይደል ልጆች? ጣዖት ማለት ሰዎች ድንጋይ ጠርበው አልያም ደግሞ እንጨት አለዝበው የሚሠሩትና አምላክ ነው ብለው የሚያምኑት ማለት ነው፡፡ ታዲያ አብርሃም አባቱ ታራ የሠራውን ጣዖት እንዲሸጥ ወደ ገቢያ ላከው፡፡ አብርሃምም ዓይን እያለው የማያይ፣ ጆሮ እያለው የማይሰማ፣ እግር እያለው የማይሄድ ጣዖት የሚገዛ እያለ በገቢያ መሐል መዞር ጀመረ፡፡

ይገርማችኋል ልጆች! ሰው ሁሉ እርሱ ያላመነበትን እርሱ ያቃለለውን ማን ይገዛዋል እያሉ ሳይገዙት ቀሩ፤ አብርሃምም አባቱ እየሠራ የሚሸጠውን ጣዖት “አምላክ ከሆንክ አብላኝ፤ ርቦኛል፤ አጠጣኝ፤ ጠምቶኛል” አለው፤ ግን ምንም አልመለሰለትም፤ ግዑዝ ነገር (መናገር የማይችል) ነበርና፤ አብርሃምም ጣዖቱ አምላክ አለመሆኑን ተገነዘበ፡፡ ወዲያውኑ በደንጊያ ቀጠቀጠው፤ ከዚያም የሁሉን ፈጣሪ መፈለግ ጀመረ፤ነፋስን፣ እሳትን ፀሐይን፣ ጨረቃን ፣ ወንዙን፣ ተራራውን ሁሉ በየተራ እያፈራረቀ አምላክ መሆናቸውን ተመራመረ፡፡ አንዱ አንዱን ሲያሸንፈው፣ አንዱ በአንዱ ሲተከ ተመለከተ፡፡ የዚህን ጊዜ የእነዚህ ሁሉ ፈጣሪ እንዳለ ተገነዘበና “የፀሐይ አምላክ ተናገረኝ” ብሎ ለመነ ( ጸለየ)፡፡ እግዚአብሔርም ድምጹን አሰማው፤ ጣዖት ከሚመለክበትም ከተማ ተለይቶ እንዲወጣ ነገረው፡፡ አብርሃምም ከዚያ ከተማ እግዚአብሔር ወደ ነገረው ቦታ ሄደ፡፡ (ዘፍ.፲፩፥፳፰ አንድምታው)

ውድ እግዚአብሔር ልጆች! እግዚአብሔርን በዓይናችን ማየት ባይቻለንም በሥነ ፍጥረቱ በቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነት፣ በውስጣችን ባለው ኅሊናችን መኖሩን እናውቃለን፡፡ ቀን ፀሐይን ያወጣልናል፤ በክረምት ዝናም ይሰጠናል፤ የተዘራው ዘር እንዲያድግ ፍሬን እንዲይዝ ያደርግልናል፡፡ ክረምትና በጋን ያፈራርቃል፡፡ እኛንም ይመግበናል፤ ከጠላታችን ዲያብሎስ ይጠብቀናል፤ ሁሉን የፈጠረ፣ ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር መኖሩን ማመን መልካም ሥራን በመሥራት፣ ሕጉን ትእዛዙን በመጠበቅ ልንኖርና ልንመሠክር ያስፈልጋል፤ እግዚአብሔር መኖሩን ለሰዎች መልካም በማድረግ፣ አታድርጉ የተባልነውን ባለማድረግ፣ አድርጉ ተብለን የታዘዝነውን መልካም ነገር ደግሞ በማድረግ በእግዚአብሔር ማመናችንን መመስከር አለብን ፤ ቸር ይግጠመን!!!

ስብሐት ለእግዚአብሔር

ወለወላዲቱ ድንግል

ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!!!

ሃይማኖት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! ብዙ ጊዜ እንደምንነግራችሁ አሁን ያላችሁበት ዕድሜ በምድራዊ ኑሮ ለነገ ማንንታችሁ መሠረት የምትጥሉበት ስለ ሆነ ጨዋታ እንኳን ቢያምራችሁ ቅድሚያ የምትሰጡት ለትምህርት መሆን አለበት! መልካም!
አሁን ሃይማኖት በሚል ርእስ ለዛሬ ወደ አዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ!

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! አንድ ነገር ለማወቅ በጣም ጓጓን! ምን መሰላችሁ? ስለ ዘመናዊ ትምህርት ውጤታችሁ! በዚህ ጎበዞች እንደ ሆናችሁ ብናምንባችሁም እንደው የግማሽ ዓመት የፈተና ውጤታችሁ ምን እንደሚሆን እንገምታለን፤ ጥሩ ውጤት እንዳመጣችሁ አንጠራጠርም!

ልጆች! ‹‹ልጅነቴ›› በሚል ርእስ የልጅነት ጸጋን እንዴት እንደምናገኝ ተምረን ነበር፤ አሁን ደግሞ የልጅነት ክብርን ካገኘን በኋላ በሃይማኖት እንዴት መጽናት እንዳለብን እንማራለን፡፡

‹‹ልጅነቴ!››

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀቱን በዓል እንዴት አሳለፋችሁ? ደስ በሚል ሁኔታ አሳልፋችሁታል ብለን እናስባለን፡፡ ልጆች! ዛሬ ልንነግራችሁ የፈለግነው ስለ ‹‹ልጅነት›› ነው፡፡ ልጅነቴ! ብለን ስንናገር ወይም ደግሞ ስናስብ ብዙ ሊታወሱን የሚችሉ ነገሮች አሉ፤

‹‹ወደ ቤተ ልሔም እንሂድ!›› (ሉቃ.፪፥፲፭)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! ትምህርት እንዴት ነው? አሁንማ ፈተና ደርሷል አይደል ልጆች? ስለዚህ ጨዋታ ሳያታልላችሁ በትኩረት በማጥናት፣ ያልተረዳችሁትን በመጠየቅ፣ የግማሽ ዓመት ፈተናውን በጥሩ ውጠየት ለማለፍ ማቀድ አለባችሁ!

ታዲያ በቀደሙት ትምህርታችን ስለ ጾመ ነቢያትና ስለ ነቢያት አባቶቻችን ስንማማር ነበር፤ አሁን ደግሞ የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እናከብራለን፤

በዓለ ቅዱስ ገብርኤል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ሳምንቱ እንዴት አለፈ? በሰንበት ቤተ ክርስቲያን ሄዳችሁ መንፈሳዊ ትምህርት እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው፤መልካም! ለዛሬ ልንነግራችሁ የተዘጋጀነው ቅዱስ ገብርኤል ከእሳት ስላዳናቸው ሦስቱ ሕፃናትና እና ይህን በዓል አስመልክቶ ክብረ በዓል ከሚከበርባቸው ቅዱሳን መካናት መካከል አንዱ ስለ ሆነው ስለ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ነው!

ነቢዩ ኤልያስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች ! እንዴት አላችሁ? ባለፈው ትምህርታችን ስለ ቅዱሳን ነቢያት፣ እነርሱ ስለ ጾሙትና የነቢያት ጾም ተብሎ ስለሚጠራው ጾም በጥቂቱ ተመልክተናል፤ለዛሬ የምንነግራችሁ ደግሞ ስለ ከቅዱሳን ነቢያት አንዱ ስለሆነው ስለ ነቢዩ ኤልያስ ነው፡፡

አበው ነቢያት!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  እንዴት አላችሁ! መንፈሳዊ ሕይወት እንዴት ነው? በትምህርት ቤት፣ በሠፈር ውስጥ እንዲሁም በተለያየ ቦታ ስትገኙ በሥርዓት እና በአግባብ እንደምትኖሩ ተስፋችን እሙን ነው፤መልካም!!! ለዛሬ የምንነግራችሁ ስለ ቅዱሳን ነቢያት ነው፡፡