ቅዱስ አማኑኤል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁልን?  ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን! አሜን! (መዝ.፳፪፥፲) ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ስለጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘አማኑኤል’ ስለሚለው ስሙ ትርጉም ይሆናል!

ደብረ ምጥማቅ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የበዓለ ሃምሣ ሳምንታት እንዴት ናቸው? ቤተ ክርስቲያን እየሄዳችሁ ታስቀድሳላችሁ? በሰንበታትስ ከወላጆቻችሁ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ትሄዳላችሁ? ከሆነ በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደብረ ምጥማቅ በሚባል ገዳም ያደረገችውን ተአምር ነው፤

ልደታ ለማርያም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን? በርቱ! ዛሬ የምንነጋራችሁ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ይሆናል!መልካም ንባብ!

ነገረ ትንሣኤ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? እንኳን አደረሳችሁ! የትንሣኤ በዓል እንዴት እያከበራችሁ ነው? መልካም! ልጆች! ዛሬ ስለ ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ እንማራለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን ከትንሣኤ በዓል ጀምሮ እስከ በዓለ ሃምሣ ድረስ ስንገናኝ የምንለዋወጠውን ሰላምታ እናስቀድም!

ይቅርታ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? ትምህርት የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት የሚደግፈንና በምድራዊ ኑሯችን ወደፊት ለመሆን የምንመኘውን ለማግኘት የምንጓጓበት መንገድ ነው! …ልጆች! የወላጆቻችሁ ምኞት ጎበዝ፣ ብልህ፣ አስተዋይና ታማኝ ስትሆኑ ለማየት ነው፡፡ መልካም! ለዛሬ የምንማማረው ባለፈው የጀመርነውን የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ቀጣዩን ክፍል ‹‹ይቅርታ›› በሚል ርእስ ይሆናል፡፡ መልካም ቆይታ!

ታማኝነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ታላቁ ዐቢይ ጾም እንዴት ነው? እንደ አቅማችሁ እየጾማቸችሁ ነው? የወላጆቻችሁ ድካማቸውና ክፍያቸው እናንተ ጎበዝ፣ ብልህ፣ አስተዋይና፣ ታማኝ ስትሆኑ ማየት ነውና በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንማማረው ባለፈው የጀመርነውን ትምህርት የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ቀጣዩን ክፍል “ታማኝነት” በሚል ርእስ ይሆናል፤ መልካም ቆይታ!

ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም ከመጀመሪያው የዓመቱ አጋማሽ ትምህርት ውጤታችሁ በመነሣት የበለጠ ጎበዝ ለመሆን እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! “ብልህ ልጅ ከስሕተቱ ይማራል” እንዲሉ አበው ከትናንት ድክመታችሁ በመማር የበለጠ ውጤታማ ተማሪ ለመሆን መሥራት ይገባል፡፡ ወላጆቻችን እኛን ለማስተማር ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ አስተውሉ! ልጆች የእነርሱ ድካም እኛ መልካምና ጎበዝ እንድንሆን ነውና በርቱ! ለዛሬ የምንማማረው ስለ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ነው፤ መልካም ቆይታ!

ኪዳነ ምሕረት!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዕረፍት ጊዜ እንዴት ነበር? መቼም ቁም ነገር ሠርታችሁበት እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው፡፡ ልጆች! ዛሬ የምንማማረው ስለ እመቤታችን ኪዳነ ምሕረትና ከአምላካችን ስለተሰጣት ቃል ኪዳን ነው፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ወር በገባ በ፲፮ኛው (ዐሥራ ስድስት) ቀን “ኪዳነ ምሕረት” ብለን የምናከብረውና የምንዘክረው ታላቅ በዓል አለ፡፡ ይህ በዓል ለምን የሚከበር ይመስላችኋል?

ከጥምቀት በኋላ ክርስትና

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የጥምቀት በዓል እንዴት አለፈ? እናንተስ የጥምቀትን በዓል እንዴት አከበራችሁት? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ አብነት ለመሆን እንዲሁም ደግሞ የዕዳ ደብዳቤያችንን ሊደመስስልን መጠመቁን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በደስታ በምስጋና በዓሉን እናከብራለን፡፡ መቼም ልጆች! ከወላጆች አልያም ከጓደኞቻችን ጋር በመሆን አክብራችኋል፤ መልካም!

ሌላው ደግሞ ወቅቱ ለእናንተ ለተማሪዎች የዓመቱ አጋማሽ የምዘና ፈተና ነበር! ፈተናስ እንዴት ነበር? እንግዲህ የዓመቱ አጋማሽ የትምህርት ወቅት አልቆ ፈተናም ተፈትናችሁ ውጤት የተሰጣችሁ እንዲሁም ውጤት በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ትኖራላች፡፡ ከባለፈው ውጤታችሁ በመነሣት በቀጣዩ የትምህርት ጊዜ በርትታችሁ ለመማር እንደ ምታቅዱ ተስፋችን እሙን ነው፡፡ ደግሞ በዕረፍት ጊዜያችሁ መልካምን ነገር በማድረግ አሳለፉ፡፡ በርቱ! ለዛሬ የምንነግራችሁ ከጥምቀት በኋላ ክርስትና ምን ይመስላል የሚለውን እንመለከታለን፤ መልካም ቆይታ!

‹‹በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ›› (ማቴ.፫፥፲፫)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ! እንኳን አደረሳችሁ! የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል እንዴት አለፈ? ልጆች! አሁን ያላችሁበት ወቅት የዓመቱ አጋማሽ የፈተና ወቅት ነው! ፈተናውን በደንብ አድርጋችሁ መሥራት አለባችሁ! መቼም በርተታችሁ ስታጠኑና ያልገባችሁን ስትጠይቁ ስለነበር በፈተና የሚቀርቡላችሁን ጥያቄዎች በትክክል እንደምትመልሱ አንጠራጠርም! ምክንያቱም የምትጠየቁት የተማራችሁትን ስለሆነ በአንዳች ነገር እንዳትዘናጉ!

ታዲያ ልጆች! ፈተናውን የምትሠሩት ጥሩ ማርክ ለማምጣት ብቻ ሳይሆን ለእውቀትም መሆን አለበት፡፡ ዕውቀት ማለት በተግባር መተርም መሆኑን እንዳትዘነጉ! መልካም! ልጆች ዛሬ ስለ ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት እንማራለን፡፡