የቤተ ክርስቲያን በዓላት አከባባር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ አሸጋግሮ በሰላም ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! ዕንቁጣጣሽ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው!ልጆች! በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በዓላት እንዴት እንደሚከበሩ እኛም ደግሞ በምን ዓይነት መልኩ በበዓላት ላይ መሳተፍ አንዳለብን ልንነግራችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!

ወርኃ ጳጉሜን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ጾመ ፍልሰታ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ በመማርና በማስቀደስ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው፤ ልጆች! አሁን ደግሞ የዚህን ዓመት የመጨረሻ የሆነውን ጽሑፍ ስለ ‘ወርኃ ጳጉሜን’ ጥቂት ልናካፍላችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!

ጾመ ፍልሰታ ለማርያም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ናችሁ? የክረምቱን ወቅት ምን ቁም ነገር እየሠራችሁበት ነው? ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መንፈሳዊ ትምህርት እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን፤ ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ ፍልሰታ ጾም ነው፤

ቅዱስ ኤፍሬም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ወርኃ ክረምትን እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ዘመናዊ ትምህርት ተጠናቆ አሁን ዕረፍት ላይ እንደመሆናችሁ መጠን ጊዜያችሁን በተገቢው መንገድ እየተጠቀማችሁበት እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! በጥሩ ውጤት ከክፍል ክፍል እንደተዘዋወራችሁም ተስፋ አለን፡:ልጆች! ዛሬ የምንነግራችሁ የቅዱስ ኤፍሬምን ታሪክ ነው፡፡

ወርኃ ክረምት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ ትምህርት ጊዜ ተጠናቆ ፈተና ተፈትናችሁ ጨረሳችሁ አይደል? ውጤት እንዴት ነው? በጥሩ ውጤት ከክፍል ወደ ክፍል እንደተዘዋወራችሁ ተስፋ እናደርጋለን፤ አሁን ደግሞ የክረምት ጊዜ ስለመጣ ለዛሬ ልናስተምራችሁ የወደድነው ስለ ወርኃ ክረምት ነው፡፡

ቅዱስ ወንጌል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን አላችሁ? ጾመ ሐዋርያትን እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? ልጆች! ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፤ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፡፡…ልጆች! ዛሬ ስለ ቅዱስ ወንጌል እንማራለን፤ መልካም ንባብ!!!

ቅዱስ አማኑኤል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁልን?  ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን! አሜን! (መዝ.፳፪፥፲) ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ስለጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘አማኑኤል’ ስለሚለው ስሙ ትርጉም ይሆናል!

ደብረ ምጥማቅ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የበዓለ ሃምሣ ሳምንታት እንዴት ናቸው? ቤተ ክርስቲያን እየሄዳችሁ ታስቀድሳላችሁ? በሰንበታትስ ከወላጆቻችሁ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ትሄዳላችሁ? ከሆነ በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደብረ ምጥማቅ በሚባል ገዳም ያደረገችውን ተአምር ነው፤

ልደታ ለማርያም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን? በርቱ! ዛሬ የምንነጋራችሁ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ይሆናል!መልካም ንባብ!

ነገረ ትንሣኤ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? እንኳን አደረሳችሁ! የትንሣኤ በዓል እንዴት እያከበራችሁ ነው? መልካም! ልጆች! ዛሬ ስለ ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ እንማራለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን ከትንሣኤ በዓል ጀምሮ እስከ በዓለ ሃምሣ ድረስ ስንገናኝ የምንለዋወጠውን ሰላምታ እናስቀድም!