ቅዱስ አማኑኤል
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁልን? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን! አሜን! (መዝ.፳፪፥፲) ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ስለጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘አማኑኤል’ ስለሚለው ስሙ ትርጉም ይሆናል!