Entries by Mahibere Kidusan

ዘመነ አስተምህሮ

ኅዳር 6/2004 ዓ.ም

በቤተ ክርስተያናችን የዘመን አቆጣጠር /አከፋፈል/ መሠረት ከኀዳር 6 ጀምሮ እስከ ታኀሣሥ 13 ድረስ ያለው ወቅት ዘመነ አስተምህሮ ይባላል፡፡

መሀረ ማለት ይቅር አለ ማለት ሲሆን፤ ዘመነ አስተምህሮ ማለት ይቅርታ የመጠየቅ /የምልጃ/ ዘመን ማለት ነው፡፡ ዘመኑ ቤተ ክርስቲያን ስለ ልጆቿ ይቅርታ የምትጠይቅበት፤ ምዕመናንንም ስለ በደላቸው ይቅርታ የሚጠይቁበት፤ ስለዚህም በስፋት ትምህርት የሚሰጥበት ዘመን ነው፡፡

ከትርፍ ነፃ የሆኑ የምስልና የድምጽ ሲዲዎች እንደሚሠራጩ ተገለጠ፡፡

በዲ/ን ኅሩይ ባየ
ቀን 05/03/2004ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል የተዘጋጁ 3 ሺህ የሚሆኑ የምስልና የድምጽ ሲዲዎች ኅዳር 8 ቀን 2004 ዓ.ም በማኅበሩ ጽ/ቤት እንደሚሠራጭ የምክረ ሐሳቡ አስተባባሪ ኢንጂነር ሙሉጌታ ጌትነት አስታወቁ፡፡

ኢንጅነር ሙሉጌታ እንደገለጡት የምስልና የድምጽ ሲዲዎችን ለማግኘትና ለማሠራጨት ምንም ዐይነት ትርፍ ታሳቢ ሳይደረግ የሲዲውን ዋጋ ብቻ በመሸፈን ማግኘት ይቻላል፡፡ በማያያዝም የሥርጭቱ ዋና ዓላማ ስብከተ ወንጌልን በተፋጠነ መንገድ ለምእመናን ማዳረስ ሲሆን በገበያ ላይ የሚገኙት የምስልና የድምጽ ሲዲዎች የምእመናንን ምጣኔ ሀብት የሚጎዱ በመሆናቸው በቀላሉ ቃለ እግዚአብሔር የሚስፋፋበትን መንገድ ለማመቻቸት፣ የተሐድሶ መናፍቃን ስሑት ትምህርቶች በሕዝበ ክርስቲያኑ ሰርገው ስለገቡ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ያላቸውን የስብከት ሲዲዎች ምእመናን እንዲያገኙና ስለ ሃይማኖታቸው እንዲያውቁ ለመደገፍ፣ በከተማ የሚኖሩ ጥቂት ምእመናን የመካነ ድር አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቢሆኑም አገልግሎቱ ውድና ዝቅተኛ ፍጥነት ስላለው የምስልና የድምጽ ዝግጅቶችን መመልከትና መስማት ስለማይችሉ ችግሩን አስወግዶ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እንዲቻልና የቪሲዲ አገልግሎት ከገጠር እስከ ከተማ እየተስፋፋ በመምጣቱ ንጹህ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን ለሁሉም እንዲዳረስ ለማድረግ እንደሆነ አስተባባሪው አስገንዝበዋል፡፡

እነሆ እኔ በእናንተ ደስ ይለኛል፡፡ ፊል. 2፡17

ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተችበት ጊዜ አንሥቶ የቀና እውነተኛና መልካም ጉዞዋን የሚፈታተኑ በዙሪያዋ ጠፍተው አያውቁም፡፡ ከሰው መፈጠር በፊት በመላእክት ዘንድ የነበረችው የመላእክት ማኅበር በክፉው መልአክ /በዲያብሎስ/ እና እርሱን በመሰሉ ጭፍራዎቹ መካከል Gubae_Qanaያለ ነውርና ነቀፋ በመገኘቷ የተመረጠች ነበረች፡፡

 

በጥንተ አበው ታሪክም የምናየው ይህንኑ ነው፡፡ ከአቤል ጀምሮ እስከ ዮሴፍ ያሉ አበው በክፉዎች ብዙ መከራ የደረሰባቸው፣ በዚህች ምድር ላይ እንግዶችና መጻተኞች ሆነው የኖሩ ናቸው፡፡ጌታችን ወደዚህ ምድር በሥጋ እስከመጣበት ድረስ የነበሩት የእስራኤል ልጆች ታሪክም በክፉና መልካም ነገሮች ከሚጎረብጠው ትውልድ መካከል የነበረ ውጣ ውረድ የበዛበት ነው፡፡

ሰርግ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት

ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

ኅዳር 06/2004 ዓ.ም.

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች በላከው መልእክት ም.፬፥፲፪ ላይ ያለውን ኃይለ ቃል በተረጎመበት ፲፪ኛው ድርሳኑ በዘመኑ የሚፈጸመውን የሰርግ ሥርዐት መሠረት በማድረግ ሰርግን አስመልክቶ ሰፋ ያለ ትምህርትን ሰጥቶአል ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በሰርግ ምክንያት የሚወጡትን ወጪዎችና ግርግርና ሁካታ አጥብቆ የሚቃወም አባት ነው ፡፡ በዚህም ጽሑፍ ይህን ወደማስተዋል ልንመጣም እንችላልን ፡፡ መልካም ንባብ

ስለዚህ እንዲህ ብሎ ያስተምራል ፡- ትዳር ምንድን ነው? ትዕይንት(ትያትር) ነውን ? አይደለም፡፡  ምንም እንኳ እናንተ ለትዳርና ለምሳሌውweddingpic አክብሮት ባይኖራችሁ ትዳር ግሩም ምሥጢርና የታላቅ መንፈሳዊ ምሥጢር ምሳሌ ነው ፡፡ ቅዱስ    ጳውሎስ ስለዚህ ሲያስተምር “ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው”   ይልና ጨምሮ “እኔ ግን ስለ ክርስቶስና    ስለ  ቤተ ክርስቲያን እላለሁ” ይላል   ፡፡(ኤፌ.፭፥፴፪) ጋብቻ የቤተ ክርስቲያንና   የክርስቶስ ምሳሌ ነው ፤  እንዲህ በከበረ    ምሥጢር ላይ ዳንኪረኞችን በመጋበዝ   ዝሙትን ታስተዋውቁበታላችሁን ? ነገር   ግን  ከእናንተ መካከል አንዱ እኔን፡- እንዲህ ስትል ደናግል ወይም ያገቡት አይጨፍሩ እያልክ ነው ፤  እንግዲያ እነርሱ በዚህ ሰርግ ላይ ካልጨፈሩ ማን ሊጨፍር ነው ? ብሎ ሊጠይቅ ይችላል ፡፡ ማንም  አይጨፍር ነው መልሴ ፡፡

የቅዱስ ኤፍሬም ቅኔያዊ መዝሙራት

ጥቅምት 30/2004 ዓ.ም

ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

መግቢያ

የሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም አጭር የሕይወት ታሪክ

ቅዱስ ኤፍሬም 299 ዓ.ም ገደማ ንጽቢን በምትባለው ታላቅ ከተማ ተወለደ፡፡ ንጽቢን በጥንታዊቱ የሮም ግዛት በምሥራቅ የምትገኝ ከተማ ነበረች፡፡ አብዛኞቹ የታሪክ ጸሐፍት እንደሚስማሙበት ቅዱስ ኤፍሬም ከክርስቲያን ቤተሰብ የተገኘ ሲሆን በተወለደባት ከተማ በድቁና ሲያገለግል ረጅም የእድሜ ዘመኑን ያሳለፈ ቅዱስ ነው፡፡ አንዳንድ የታሪክ ጸሐፍት ግን የቅስና ማዕረግ አንዳለውም ይተርካሉ፡፡ ነገር ግን በአብዛኛዎቹ የሶርያ የታሪክ ጸሐፊያን ዘንድ ቅዱስ ኤፍሬም ዲያቆን እንደነበረ ተጽፎ እናገኛለን፡፡ ስለዚህም እስካሁን ድረስ በሶርያውያን ክርስቲያኖች ዘንድ የድቁና ማዕረግ በቅዱስ ኤፍሬም ምክንያት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ማዕረግ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡

«ወአድኀነ ሕዝቦ በመስቀሉ»

ክፍል ሁለት

 

3. ክብረ መስቀል

እኛ ኦርቶዶክሳውያን የመስቀልን መንፈሳዊ ትርጉም ከመረዳትና በልባችን ከመያዝ በተጨማሪ ለመስቀል ያለንን ክብር እና ፍቅር ለመግለፅ የምናደርጋቸው በርካታ ነገሮች አሉ፤ ከእነዚህ መካከል ጥቂቶቹን እንጠቁማለን፡-

«ወአድኀነ ሕዝቦ በመስቀሉ»

መስከረም 2002 ዓ.ም.

ክፍል አንድ

«ሕዝቡን በመስቀሉ አዳነ»
ዲ/ን ዘላለም ቻላቸው

በቤተክርስቲያናችን መስከረም 17 ቀን የመስቀል በዓል ይከበራል፡፡ እኛም በዚህ ትምህርት የመስቀሉን ነገር እና የበዓሉን ታሪክና አከባበር እንመለከታለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን የነገረ መስቀሉ መነሻው ነገረ ድኅነት ነውና ጥቂት ነገሮችን ስለዚያ እንበል፡፡

ታላቅ የቪሲዲ ምርቃት

አዘጋጅ፡- በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሙያ  አገልግሎትና አቅም ማጎልበቻ ዋና ክፍልቦታ፡-ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽሰዓት፡- ቅዳሜ ኅዳር 02/03/2004 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ  

“አባታችን ሆይ” ክፍል አንድ

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

መግቢያ

አንባቢያን ሆይ ይህ ጽሑፍ የትርጉም ሥራ ሲሆን ትምህርቱም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስን ወንጌል ሲተረጉም ከጻፈው ላይ የተወሰደ ነው፡፡ የዚህ ቅዱስ አባት ሥራዎች ብዙ ከመሆናቸው የተነሣ ታላቁ ጸሐፊ /The great author/ ተብሎ ነው በሥነ መለኮት ምሁራን የሚታወቀው፡፡ “አባታችን ሆይ” የሚለውን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያስተማረውን የጸሎት ሥርዐት ይህ ቅዱስ እንዴት አድርጎ ድንቅ በሚባል መልኩ እንደተረጎመው ትመለከቱ ዘንድ እነሆ ብለናል፡፡

ቅዱስ እሰጢፋኖስ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምህሮ

ቀን ጥቅምት 17/2004 ዓ.ም.

በዲ/ን ሽመል መርጊያ

 

(የሐዋ.6፡8-ም.7፡53)

መግቢያ

በሐዋርያት ስብከት ቤተ ክርስቲያን ስትስፋፋ በትምህርታቸውና በተዐምራታቸው ተስበው ወደ ክርስትና እምነት የተመለሱ ከአይሁድና ከአሕዛብ ወገን የሆኑ ክርስቲያኖች መሬታቸውንና ጥሪታቸውን በመሸጥ  ያላቸውን ሀብት አንድነት በማድረግ በኢየሩሳሌም የአንድነት ኑሮን ይኖሩ ነበር፡፡ በሕብረትም የሐዋርያት ትምህርትን በመስማትና  በጸሎት ይተጉ እንዲሁም ማዕድን በመባረክ በጋራ ይመገቡ ነበር፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም “አንድ ልብና አንዲትነፈስ አላቸው በማለት (የሐዋ.4፡32) ስለአንድነታቸው ፍጹምነት ይነግረናል፡፡