ቅዱስ እሰጢፋኖስ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምህሮ
ስለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ክፍል አንድን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
አይሁድን ቀርቦ ለመረመራቸውም አሕዛብ ከሆኑት ከፋርስ ወገን እንደሆኑ እንዲሁም አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ተአምራትን ሳይሻ ለእግዚአብሔር መከራዎቹን ሁሉ ታግሦና ተቋቁሞ የተመላለሰው እንደሆነ እግዚአብሔር ልጁ እንደሚያደርገው፣ እንዲሁም የሁሉ አባት አብርሃም እንዳደረገው የአባቶችን መቃብርና ያለንን ሁሉ በመተው ልንታዘዝ እንደሚገባንም ጠቁሞናል ፡፡
የአብርሃም አባትና ዘመዶቹ ምንም እንኳ ረጅም ጉዞ ከአብርሃም ጋር ቢጉዋዙም ከንዓንን ይወርሱ ዘንድ የተገባቸው ካልሆኑ ልጆቹስ ላይ እንዴት ይህ እጣ ፈንታ አይደርስባቸው ይሆን? “ነገር ግን ልጅ ሳይኖረው ለእርሱ ከእርሱም በኋላ ለዘሩ ርስት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ ተስፋ ሰጠው፡፡” አለ፡፡ በዚህ የእግዚአብሔርን ድንቅ ስጦታንና የአብርሃምን እምነት ታላቅነት እንመለከታለን፡፡ “ልጅ ሳይኖረው” የሚለው አገላለጽ የእርሱን በእምነት መታዘዝን የሚገልጥ ነው፡፡ “ለእርሱ ከእርሱም በኋላ ለዘሩ ርስት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ”የሚለው በድርጊት ከታየው ጋር ስናነጻጽር የተቃረነ መስሎ ይታየናል፡፡ ምክንያቱም አስቀድሞ “በዚችም የእግር ጫማ ስንኳ የሚያህል ርስት አልሰጠውም” እንዲሁም ልጅም አልነበረውም ይለናልና፡፡ እነዚህ ዐረፍተ ነገሮች አብርሃም በእምነቱ ከተሰጠው ጋር የሚጣጣሙ ላይመስሉን ይችላሉ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊሰጥ ያሰበውን ያንኑ ነው የሚሰጠው፡፡ በዚህ ቦታ ግን ቃሉና ድርጊቱ የተቃረኑ ይመስሉናል፡፡ ነገር ግን እንደ እኛ አስተምህሮ ፈጽሞ የሚጣረሱ አይደሉም፡፡ እንደውም ፈጽመው የሚጣጣሙ እንጂ፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በዚህ እንደምንደክም ነገር ግን እረፍታችን በላይ በሰማይ እንደሆነ አስተምሮናል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ እስጢፋኖስ እንዲህ አለ፡፡