Entries by Mahibere Kidusan

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

ጥምቀት

በዘመነ ሥጋዌ በናዝሬት ከተማ፤ ዮርዳኖስ ወንዝ የእስራኤል ሕዝብ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ተራ ይዘው በሚጠብቁበት ጊዜ እርሱ እንዲህ እያለ ይሰብክ ነበር፤ ‹‹እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው መቅሠፍት ታመልጡ ዘንድ ማን ነገራችሁ? እንግዲህ ለንስሓ የሚያበቃችሁን ሥራ ሥሩ፤ አብርሃም አባታችን አለን በማለት የምታመልጡ አይምሰላችሁ፤ እግዚአብሔር ከእነዚህ ድንጋዮች የአብርሃም ልጆችን ማንሣት እንደሚችል እነግራችኋለሁ፡፡ እነሆ፥ ምሳር በዛፎች ላይ […]

ሰሙነ ሕማማት (ከዕለተ ሰኑይ እስከ ቀዳሚት ሰንበት)

በመምህር ቸርነት አበበ መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም መግቢያ ከአባታችን አዳም በደል ወይም ስሕተት በኋላ በሕማማት፣ በደዌያት፣ በመቅሠፍታት፣ ወዘተ በብዙ መከራ የሰው ልጅ ሊኖርባቸው ግድ የኾነባቸው ዘመናት ጥቂቶች አልነበሩም፡፡ የሰው ልጅ ቢያጠፋ፣ ቢበድል፣ ከሕገ እግዚአብሔር ቢወጣ እንኳን የዋህ፣ ታጋሽ፣ ቸር፣ አዛኝ የኾነው አምላክ የጠፋውን ሊፈልግ፣ የተራበውን ሊያጠግብ የታረዘውን ሊያለብስ፣ ፍቅር ላጣው ፍጹም ፍቅር ሊለግስ፣ ሰላም […]

‹‹ሰላም ለኒቆዲሞስ ለወልደ ማርያም ዘአምኖ››

በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው ሚያዚያ 5/2011 ዓ.ም. በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት፣ ከዐቢይ ጾም ሳምንታት መካከል ሰባተኛው ሳምንት በኒቆዲሞስ ተሰይሟል፡፡ ሳምንቱ በስሙ ከመጠራቱም ባሻገር በቤተ ክርስቲያን የሚቀርበው ትምህርትም ኒቆዲሞስ ከጌታ የተማረዉን ምሥጢረ ጥምቀት መሠረት ያደረገ ነው፡፡ ይኸውም የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ ከውኃ እና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድ እንደሚገባው ያትታትል፡፡ ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ ምዕራፍ ፲፮ ቍጥር ፲፮ ላይ […]

ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ፡፡

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡ ጥር  17 ቀን  2011 ዓ.ም እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ፡፡ / 1ኛ ጴጥ 4፤7/ በማንኛውም የሰው ልጅ ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችንና ግድያዎችን ሁሉ እናወግዛለን፡፡  በየቦታው የተከሰቱ ችግሮች እንዲቆሙም በድርጊቱ የሚሳተፉ አካላትን ሁሉ እንማጸናለን፤  እናሳስባለንም፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን የክርስትና ሃይማኖት ማእከላዊ ጉዳዩ ሰው ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፣፤ ሰውም አምላክ ሆነ፣ የሚለው […]

“መከራ ልትቀበሉ እንጂ በስሙ ልታምኑ ብቻ አልተጠራችሁም” (ፊል. ፩፥፳፱)

  ዘመናችን መረጃ በፍጥነት የሚለዋወጥበት፣ ስላሙ ሲደፈርስ ደቂቃ የማይፈጅበት እየሆነ መጥቷል፡፡ ሰዎች ሞትን ለመሸሽ የማያደርጉት ጥረት የለም፡፡ ኃያላን ሰማይ ጠቀስ ፎቆች፣ የኤሌክትሪክ አጥር፣ የድኅንነት ካሜራ እያዘጋጁ ወንጀልንና ወንጀለኞችን ለመቆጣጠር ቢሞክሩም አልተሳካላቸውም፡፡ መንገዳቸው ሥጋዊ ፍላጎትን የተከተለ በመሆኑ መፍትሔ ማሰገኘት አልቻለም፡፡ ችግሩ የሚፈታው ሁልጊዜ ችግርን ወደ ሌላ በመጠቆም አለመሆኑን መረዳት ይገባል፡፡ ምዕራባውያን የአዳጊ ሀገሮችን ቅርስና መዋዕለ ንዋይ […]

“ከእንግዲህ በኋላ አብያተ ክርስቲያናትን ማቃጠልና ክርስቲያኖችን በጭካኔ መግደል በዝምታ አይታይም” ብፁዕ ሥራ አስኪያጅ

  በካሣሁን ለምለሙ በአንዳንድ የሀገራችን ክፍሎች በተለየ መልኩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ያነጣጠረ ቃጠሎ፣ ዝርፊያ፣ እንዲሁም በክርስቲያኖች ላይ የሚካሔደው ጭካኔ የተሞላበት ግድያ ከእንግዲህ በኋላ በዝምታ ሊታይ እንደማይገባ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ገለጡ፡፡ ለሀገር ብዙ ዋጋ በከፈለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በአማኞቿ ላይ ለበርካታ ዓመታት አረመናዊ ድርጊት በተደጋጋሚ ሲፈጸም ቆይቷል፡፡ እምነትን […]

በአሜሪካ የዲሲ ንዑስ ማእከል አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን አስመረቀ

ከአሜሪካ ማእከል በማኅበረ ቅዱሳን በአሜሪካ የዲሲ ንዑስ ማእከል አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ነሐሴ ፲፪ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም ለሰባት ወራት ያስተማራቸውን 64 ተማሪዎችን የተማሪ ወላጆችና የማኅበሩ አመራር አባላት በተገኙበት በሜሪላንድ ግዛት አስመረቀ፡፡ በምረቃው መርሐ ግብር ላይ የትምህርት ቤቱ አስተባባሪ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃይለ ማርያም የማኅበሩን መልእክትና የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤትን የ፳፻፲ ዓ.ም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃይለ […]

አባቶቻችን ለዕርቅ አርአያ በመሆናቸው ዘመኑን ዋጅተዋል

  ማስታረቅና ማስማማት ከሰላም መሪ የሚገኝ አርአያነት ያለው ተግባር ነው ይቅር ማለትም እንደዚሁ፡፡ በዓለም ላይ ተቈጥረው የማያልቁ ጦርነቶች ቢካሔዱም ለጊዜው የተሸነፈ የመሰለው ጊዜ እስከሚያገኝ አድፍጦ እንዲቆይ ማድረግ ቻለ እንጂ አማናዊ ሰላም ማምጣት አልቻለም፡፡ አንዱ ሌላውን ሲወር፣ አንዱ ሌላውን ሲያስገብር ኖሯል፡፡ አባቶቻችን ዘመኑን ሲዋጁ የኖሩት ዕርቅ በማድረግ የተለያዩትን በማስማማት ነው፡፡ የጦርነት ውጤቱ ቂምና በቀል ሲሆን የዕርቅ […]