Entries by Mahibere Kidusan

ደብረ ዘይት(ለሕጻናት)

መጋቢት 06/2004ዓ.ም

በቴዎድሮስ እሸቱ

 

5debrezeit

ልጆች እንኳን ለጾመ እኩሌታው /ለደብረ ዘይት/ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ይህ አምስተኛው ሳምንት ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ የጾሙ እኩሌታ በመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ በዓል ነው፡፡ ልጆች በዚህ ቀን ጌታ በደብረ ዘይት ስለዳግም ምጽአቱ ያስተማረው ትምህርት ይነገራል፡፡ ጌታ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ለሁሉም እንደየሥራው ለመክፈል፣ በግርማ መንግሥቱ ይመጣል፡፡

የአሰቦት ገዳም ደን ዳግም ቃጠሎ

መጋቢት 3/2004 ዓ.ም በእንዳለ ደምስስ የአሰቦት ገዳም ደን ዳግም በመቃጠል ላይ ይገኛል፡፡ ከመጋቢት 2/2004 ዓ.ም.ከቀኑ አሥር ሠዐት ጀምሮ መነሻው ባልታወቀ ምክንያት ቃጠሎው በአዲስ መልክ እንደተቀሰቀሰ የገዳሙ ማኅበረ መነኮሳት ገልጸዋል፡፡ ከገዳሙ መነኮሳት በደረሰን የድረሱልን ጥሪ መሰረት እሳቱን ለማጥፋት ከአቅማቸው በላይ እንደሆነ በመግለጽ የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሔ እንዲፈልግላቸው በመማጸን ላይ ይገኛሉ፡፡ ከቀኑ አሥር ሠዐት የጀመረው ቃጠሎ በአባ […]

መውደቅ አዳማዊ ነው፤ ወድቆ አለመነሣት ግን ዲያብሎሳዊ ነው”

መጋቢት 3/2004 ዓ.ም.

በዲ/ን ኅሩይ ባየ
“ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው መተርጉማን፣ ሰባኪያንና የእምነት አርበኞች መካከል አንዱ ነው፡፡ ከአሕዛብነት ወደ ክርስትና የተመለሱ ሰዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ክርስቲያን ተብለው በተጠሩበት የሦርያ ዋና ከተማ በሆነችው በአንጾኪያ ተወልዶ ያደገው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በሕይወቱ በአርአያነቱ የሚጠቀስ መንፈሳዊ አባት ነው፡፡

የአሰቦት ገዳም ደን ቃጠሎ ሪፖርታዥ

መጋቢት 1/2004 ዓ.ም.


በእንዳለ ደምስስ

አይቴ ሀሎከ አምላከ አበዊነ? /የአባቶቻችን አምላክ ወዴት አለህ?/

የአሰቦት ቅድስት ሥላሴና የአባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም ደን በእሳት የተቃጠለ ሲሆን  ለማጥፋት በማኅበረ መነኮሳቱና ምዕመናን እንዲሁም በፌደራል ፖሊስና በኦሮሚያ ፖሊስ ከፍተኛ ጥረት ከአምስት ቀናት በኋላ ሊጠፋ ችሏል፡፡

 

የአሰቦት ገዳም በ13ኛው መቶ ክ/ዘመን በአባ ሳሙኤል ዘወገግ የተመሠረተ ሲሆን በ15ኛው መቶ ክ/ዘመን አህመድ ግራኝ አጠፋው፡፡ የገዳሙ መነኮሳትም ከሞት የተረፉት ተበታተኑ፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ለረጅም ዘመናት አገልግሎት መስጠት ያልቻለ ቢሆንም አንዳንድ መናንያን ወደቦታው በመሔድ በጸሎት ተወስነው ይኖሩ እንደነበር ይነገራል፡፡ በ1911 ዓ.ም. ንግስት ዘውዲቱ እንደገና ገዳሙ እንዲመሰረት አደረጉ፡፡

 

በ1928 ዓ.ም. የጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን በመውረሩ ገዳሙን ለማጥፋት ጥረት አድርጎ ነበር፡፡ አፄ ኃ/ሥላሴ በ1936 ዓ.ም. በተጠናከረ ሁኔታ ገድመው፣ መተዳደሪያ፣ ርስት ጉልት ሰጥተውና ለመነኮሳት መኖሪያ አሰርተው በሥርዓት እንዲጠበቅ አደረጉ፡፡ ሣራ ማርያም አካባቢ / ከአሰቦት ገዳም በስተምዕራብ/ እስከ 300 ወታደሮች ተመድበው ገዳሙንና ደኑን ሲጠብቁ እንደነበር አበመኔቱ የታሪክ ማኅደርን ጠቅሰው ይገልጻሉ፡፡ በ1969 ዓ.ም. የሶማሊያ ጦር ኢትዮጵያን ለመውረር ያደረገውን ጥረት ተከትሎ ወታደሮቹ በመወሰዳቸው ገዳሙ አደጋ ስላንዣበበበት ከገዳሙ የተውጣጡ አራት መነኮሳት ብቻ በየቀኑ መጠበቅ ጀመሩ፡፡ አሁንም በዚህ ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡

 

ለመሆኑ የእሳት ቃጠሎው መነሻው ምንድነው? እንዴትስ አለፈ?

መፃጒዕ /ለሕፃናት/

መጋቢት1/2004 ዓ.ም.

በቴዎድሮስ አሸቱ

እንደምን ሰነበታችሁ? ልጆች ደህና ናችሁ? መልካም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አሁን የአብይ ጾም አራተኛው ሳምንት ላይ ደርሰናል፡፡ ለቤተ ክርስቲያናችን ይህ ሳምንት መፃጒዕ ይባላል፡፡ በዚህ ሳንምንት በቤተ ክርስቲያን የሚቀርቡ ምስጋናዎች ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረጋችውን ድንቅ ድንቅ ተአምራት /ህሙም መፈወሱን፤ ሙት ማስነሣቱን/ የሚያዘክሩ ናቸው፡፡

የዐቢይ ጾም ስብከት (ክፍል 4)

የካቲት 29/2004 ዓ.ም.

በአያሌው ዘኢየሱስ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም ሲመጣ ሰው ሁሉ በሥጋም ሆነ በነፍስ ታሞ ነበር፡፡ እርሱ ወደዚህ ዓለም የመጣው የሰው ልጆች ሁሉ አባትና መድኀኒት ስለሆነና ከዚህ በሽታቸው ሊያድናቸው ነው፡፡ ይህ ስለሆነ ወደ እኛ ከመጣ በኋላ ስለ መጣበት ዓላማ እንዲህ በማለት ተናገረን፡-   «. . . ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩት መፈታትን፣ ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፤ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ፤ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል. . .» ሉቃ 4፥17-19፡፡ ይህ በመሆኑም መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድረ እስራኤል ተዘዋውሮ በልዩ ልዩ ደዌ የተያዙ በሽተኞችን ሁሉ አድኗቸዋል፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ይህን ሁኔታ የገለጸው እንዲህ በማለት ነው፡- «. . . የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ በገሊላ ሁሉ ይዞር ነበር፡፡ ዝናውም ወደ ሶርያ ሁሉ ወጣ፤ በልዩ ልዩ ደዌና ሥቃይም ተይዘው የታመሙትን ሁሉ፤ አጋንንት ያደሩባቸውን፤ በጨረቃም የሚነሣባቸውን ሽባዎችንም ወደ እርሱ አመጡ፤ ፈወሳቸውም፡፡» ማቴ 4፥23-24፡፡

አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ ማቴ.4፥2

የካቲት 29/2004 ዓ.ም.

በመ/ር ምሥጢረሥላሴ ማናየ

ይህ ከላይ ያነሣነው ርዕስ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት መጾሙን ያስተምረናል፡፡
በዚህ ኀይለ ቃል ሁለት ታላላቅ ቁም ነገሮችን ቃላትን እንመለከታለን

 

  1. አርባ መአልትና አርባ ሌሊት
  2. ጾም የሚሉት ናቸው፡፡

በቅድሚያ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት የሚለውን ከእነ ምስጢሩ እንመለከተዋለን፡፡ ቀጥለን ደግሞ ጌታችንስ ለምን አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ? የሚለውን እንመለከታለን እግዚአብሔር አይነልቡናችንን ይክፈትልን፡፡