የዩኒቨርሲቲዎች የታሪክ እይታ ከድጥ ወደ ማጡ
የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በአራት የዩኒቨርሲቲ መምህራን “የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ፤The History of Ethiopia and the Horn” በሚል እርስ ለመጀመሪያ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማስተማሪያ የሚሆን ጥራዝ አዘጋጅቷል። ዝግጅቱ ለመስከረም አልደርስ ብሎ ይሁን ሌላ ምክንያት ኖሮት ባይታወቅም ለሁለተኛው መንፈቀ ዓመት ሊሰጥ መታሰቡ ተሰምቷል። ስርጭት ላይ ሊውል የተቃረበ የሚመስለው ጥራዝ በሙያው ብቃት ባላቸው ምሁራን መዘጋጀቱም ተገልጧል፡፡ የታሪክ ትምህርት እንዳይሰጥ ተከልክሎ የቆየው የገዥው መደብ መጠቀሚያ ሆኖ ስለኖረ እንደ ገና በአዲስ መልክ መጻፍ አለበት ተብሎ መሆኑን ልብ ማለት ይገባል።
