Entries by Mahibere Kidusan

‹‹ዕለት ዕለት የሚያሳስበኝ የቤተ ክርስቲያን ነገር ነው›› (፪ኛ ቆሮ.፲፩፥፳፰)

ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ቃል የተናገረው ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው መልእክቱ ነው፡፡ ዕለት ዕለት ጽኑ የሆኑ መከራዎች ያጋጠሙት ቢሆንም ያ ሁሉ ሳያሳስበው፣ ሳይከብደውና ሳያስጨንቀው በመዓልትም በሌሊትም ዕረፍት የሚነሣው የቤተ ክርስቲያን ነገር ነበር፡፡ የተጠራው ለቤተ ክርስቲያን እንዲያስብና እንዲያገለግል በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ የደረሱበትን ችግሮች ሁሉ ገለጸላቸው፡፡

ቅድስት፡ የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት

የቅድስና ባለቤት የሆነው እርሱ እግዚአብሔር አምላክ ነው። እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እባረክ አይል ቡሩክ ነው። በእርሱ የባሕርይ ቅድስና እኛን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ቡሩክ ሆኖ ባረከን፣ ቅዱስ ሆኖ ቀደሰን፣ሕያው ሆኖ ሕያዋን አደረገን። የጸጋ ቅድስናንም ከእርሱ አገኘን።

የምን አለበት መዘዝ!

“በምን አለበት” ሰበብ ከእግዚአብሔር ሕግና ትእዛዝ ልንወጣ አይገባም፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እንደ ርግብ የዋህ፣ እንደ እባብ ልባሞች (ብልጦች) ሁኑ” ያለው ያልተገባ የዋህነት ስለሚጎዳ ነው፤ ብዙ የዋሃን በየዋህነት ሃይማኖታቸውን የለቀቁ አሉ፡፡ እኛን ግን እግዚአብሔር አምላካችን በሃይማኖትና በምግባር ያጽናን፡፡

የምን አለበት መዘዝ!

በዚህ ቃል ብዙዎች ሕይወታቸው ተጎድቷል፤ ሃይማኖታቸውም እንዲሁ፤ ለምሳሌ “ባንጾም ምን አለበት? እግዚአብሔር ምን ሠራችሁ እንጂ ምን በላችሁ አይለንም” የሚሉ አሉ፤ “መስቀል ባንሳለም ምን አለበት? ወደ ቤተ ክርስቲያን ባንሄድ ምን አለበት? እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ አለ” የሚሉ ሰዎችም አሉ፤ ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ከሕዝባችን ባህል ውጪ “በምን አለበት” የሚጓዙ ሰዎች ጥቂቶች አይደሉም።፡

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ!››

ውድ አንባብያን! የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስለ ቤተ ክርስቲያን ምንነት፣ ታሪክ ወዘተ መተንተን አይደለም፡፡ የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ምን መምሰል አለባት? እንዴትስ ለትውልዱ እስከ ክብሯና ግርማ ሞገሷ ትሻገር? የሚለውን አሳሳቢ ጉዳዮችን መዳሰስ ነው እንጂ፡፡

የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት

በዚህ ሳምንት የቃል ርደት፣ የወልድ ልደት፣ የአዳም ድኅነት ቢነገርም እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ፣ በክብር ያረገ በኩረ ትንሣኤ መሆኑ አይዘነጋም፡። ለዚህም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ነገር ግን ምስክርነታችንንም አትቀበሉትም። በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁኝ፥ በሰማይ ያለውን ብነግራችሁ እንዴት ታምኑኛላችሁ? ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው።

ሀልዎተ እግዚአብሔር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? የግማሽ ዓመት ትምህርት ተጀምሯልና በደንብ ትኩረት ሰጠታችሁ መማር ይገባል! ልጆች! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! በባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን “ሃይማኖት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ “ሀልዎተ እግዚአብሔር” ማለትም ዓለምን ሁሉ የፈጠረ የአምላካችን የእግዚአብሔር መኖር በምን እንደሚታወቅ እንማራለን፤ ተከታተሉን!

አድዋን ያለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማሰብ ትርጉም አልባ ነው!

የቤተ ክርስቲያናችን አስተዋጽኦ የሚገለጠው “እንዴት አሸነፍን?” የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ስንመረምር ነው፡፡ ይህ ዓለምን በብርቱ ጠፍንጎ የያዘና አንዱን ባሪያ ሌላውን ጌታ የሚያደርግ፣ ሰውን ያህል ፍጡር እንደ ከብት ነድቶ፣ እንደ ዕቃ ጎልቶ፣ ለገበያ አቅርቦ የሚሸጥ እኩይ አስተሳሰብ ከመሠረቱ የናደ፣ ነጻነት ማለት ምን ማለት እንደ ሆነ ለሌሎች ያሳየ፣ የአስተሳሰቡ ሰለባ የነበሩ ነጮችንም ያስደነገጠ ድል ኢትዮጵያውያን እንዴት ሊቀዳጁ ቻሉ? ዓቅሙና ብርታቱስ ከየት ተገኘ? ምዕራባውያን ያላቸው የሠለጠነ ወታደር፣ የጦር መሣሪያ ልዩነት እና ዓለምን የተቆጣጠረው “የነጮች” የበላይነት አስተሳሰብ እያለ የመግጠምስ ሞራሉና እምነቱ ከወዴት መጣ? ኢትዮጵያውያንን ከዚህ የአስተሳሰብና የሞራል ከፍታ ያደረሳቸው ገፊ ምክንያትስ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ስንጠይቅ መልሱ ቤተ ክርስቲያናችን ዘንድ ያደርሰናል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ህልውና በላይ የሚያስቀድመው አንዳች ነገር የሌለ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የገጠማትን ፈተና ለማለፍ የሚጠበቅበትን መንፈሳዊ ግዴታ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን የካቲት ፲፱/፳፻፲፮ ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ማኅበሩ በመግለጫው የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን መንፈሳዊ አንድነት የጠየቀ ሲሆን “ቤተ ክርስቲያንን በማይጠቅማት ጉዳይ የግል ፍላጎትንና ምድራዊ ዓላማን መሠረት አድርገው ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ውጭ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊን ለመተካት፣ ፓትርያርክ ለመሾምና የመሳሰሉትን ለመፈጸም” የሚንቀሳቀሱ ያላቸውን “አንዳንድ አባቶች” ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በማሳሰብ ጉዳዩንም በመከታተል መረጃውን ለምእመናን አደርሳለሁ ብሏል።፡፡