‹‹ታመመ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ›› (የዘወትር ጸሎት)
ጌታ ሰው በመሆኑ የሰውን ልጅ ከኃጢአት፣ ከሞት እና ከሰይጣን ባርነት ነጻ አወጣው። እነዚህ ድል የተነሡትም ፍጹም እስከ መስቀል ሞት በደረሰ መታዘዝ፣ ቅዱስ በሆነ ሕማሙ፣ አዳኝ በሆነ ሞቱና፣ በትንሣኤው ኃይል ነበር።
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 818 entries already.
ጌታ ሰው በመሆኑ የሰውን ልጅ ከኃጢአት፣ ከሞት እና ከሰይጣን ባርነት ነጻ አወጣው። እነዚህ ድል የተነሡትም ፍጹም እስከ መስቀል ሞት በደረሰ መታዘዝ፣ ቅዱስ በሆነ ሕማሙ፣ አዳኝ በሆነ ሞቱና፣ በትንሣኤው ኃይል ነበር።
ግሩም አምላክ በትሕትና ከተገለጠባቸው ዕለታት አንዱ የሆነው ድንቅ ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ‹‹ሆሣዕና›› በመባል ይታወቃል፡፡ ሆሣዕና መተርጉማነ አበው በአንድምታቸው ‹‹ ሆሣዕና በአርያም በሰማይ ያለ መድኃኒት›› ብለው ተርጉመውልናል፤
ተወዳጆች እንደምን ሰነበታችሁ? በዚህ ርእስ ባለፉት ተከታታይ አራት ክፍሎች ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ክብረ ክህነት ጽሑፎችን አቅርበንላችኋል፡፡ በዚህም “ክብረ ክህነት ትናንት እንዴት ነበር? ዛሬስ ምን ሁኔታ ላይ ነው?” የሚሉ ጉዳዮችን በጥቂቱ ለማየት ሞክረናል፡፡ በዚህ በክፍል አምስት ደግሞ የነገዋን ቤተ ክርስቲያን የተሻለች ለማድረግ “ክብረ ክህነት ነገ ምን መሆን አለበት” የሚለውን ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የዐቢይ ጾምን ከጀመርን እነሆ ሰባተኛው ሳምንት ደረስን! በፍቅር አስጀምሮና አበርትቶ ለዚህ ያደረሰን እግዚአብሔር ይመስገን!… ልጆች!ባለፈው “ሥነ ፍጥረት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ምሥጢረ ሥላሴን ስለምንማር ተከታተሉን!
መሆንህን አውቆ እውነተኛ
ገሰገሰ ወዳንተ በሌሊት ሳይተኛ
ቅዱስ ቃልህንም ሲሰማ ፈወሰው
የታወረ ኅሊናውን አብርቶ አቀናው
ጥያቄውን እንዲያቀርብ አበረታታኸው
ስለ ዳግም ውልደትም አስተማርከው
መንፈሳዊ ሕይወት ከሚገለጽበት ዋነኛና ተቀዳሚ ተግባራት ከሆኑት መካከል መልካም አገልግሎት አንዱ ነው፡፡ አገልግሎትን መልካም የሚያደርገውን ተግዳሮቶቹን ለይቶ ማወቅ ደግሞ ከማንኛውም መንፈሳዊ አገልጋይ ይጠበቃል፡፡ ይህም የእምነታችን፣ የሃይማኖታችን፣ የመንፈሳዊ ዕውቀታችንና ክርስቲያናዊ ተግባራችን መለኪያ ነው፡፡
ከማንም አስቀድሞ አገልግሎት ለአምላካችን እግዚአብሔር ይገባል፤ በጥንተ ተፈጥሮ በመጀመሪያው ቀን የተፈጠሩት መላእክት ፈጣሪያቸውን ዘወትር ያለማቋረጥ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እንደሚያመሰግኑት ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በመጽሐፈ አክሲማሮስ ገልጾልናል፡፡በዕለተ ዓርብ ሰው ሲፈጠር እንደ መላእክቱ የፈጠረውን ጌታውን እንዲያመሰግን፣ እንዲያገለግል እንዲሁም ስሙን እንዲቀድስና ክቡርን እንዲወርስ በመሆኑም የቀደመ ሰው አዳምም አምላኩን እያመሰገነና በገነትም በጸሎት እየተጋ ኖሯል፡፡
ክህነት በዘመናችን በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ ያለ፣ ልዩ ትኩረትን የሚሻ ዐቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ያልተማሩ ከድንቁርናቸው፣ ሥርዓት አልበኞቹም ከክፉ መንገዳቸው እንዲላቀቁ፣ በቆሬ መንገድ የቆሙ ከመንገዳቸው እንዲመለሱ የሚያደርግም ኃይል ነው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ዐቢይ ጾምን እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ባለፈው ትምህርታችን ዕድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ማንኛውም ክርስቲያን ጾምን መጾም እንዳለበት በተማርነው መሠረት እንደ ዓቅማችሁ እየጾማችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው! መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፡፡ ባለፈው “የእግዚአብሔር ባሕርያት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር ስለፈጠራቸው ፍጥረታት እንማራለን!
በመዋዕለ ስብከቱ ስለ ዳግም ምጽአቱና ምልክቶቹ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በዝርዝር በደቀ መዛምርቱ በኩል አሳውቆናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡…