Entries by Mahibere Kidusan

‹‹እባክህ አሁን አድነን!››

ግሩም አምላክ በትሕትና ከተገለጠባቸው ዕለታት አንዱ የሆነው ድንቅ ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ‹‹ሆሣዕና›› በመባል ይታወቃል፡፡ ሆሣዕና መተርጉማነ አበው በአንድምታቸው ‹‹ ሆሣዕና በአርያም በሰማይ ያለ መድኃኒት›› ብለው ተርጉመውልናል፤

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ተወዳጆች እንደምን ሰነበታችሁ? በዚህ ርእስ ባለፉት ተከታታይ አራት ክፍሎች ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ክብረ ክህነት ጽሑፎችን አቅርበንላችኋል፡፡ በዚህም “ክብረ ክህነት ትናንት እንዴት ነበር? ዛሬስ ምን ሁኔታ ላይ ነው?” የሚሉ ጉዳዮችን በጥቂቱ ለማየት ሞክረናል፡፡ በዚህ በክፍል አምስት ደግሞ የነገዋን ቤተ ክርስቲያን የተሻለች ለማድረግ “ክብረ ክህነት ነገ ምን መሆን አለበት” የሚለውን ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡

ምሥጢረ ሥላሴ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የዐቢይ ጾምን ከጀመርን እነሆ ሰባተኛው ሳምንት ደረስን! በፍቅር አስጀምሮና አበርትቶ ለዚህ ያደረሰን እግዚአብሔር ይመስገን!… ልጆች!ባለፈው “ሥነ ፍጥረት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ምሥጢረ ሥላሴን ስለምንማር ተከታተሉን!

መምህር ሆይ!

መሆንህን አውቆ እውነተኛ

ገሰገሰ ወዳንተ በሌሊት ሳይተኛ

ቅዱስ ቃልህንም ሲሰማ ፈወሰው

የታወረ ኅሊናውን አብርቶ አቀናው

ጥያቄውን እንዲያቀርብ አበረታታኸው

ስለ ዳግም ውልደትም አስተማርከው

መልካም አገልግሎት

መንፈሳዊ ሕይወት ከሚገለጽበት ዋነኛና ተቀዳሚ ተግባራት ከሆኑት መካከል መልካም አገልግሎት አንዱ ነው፡፡ አገልግሎትን መልካም የሚያደርገውን ተግዳሮቶቹን ለይቶ ማወቅ ደግሞ ከማንኛውም መንፈሳዊ አገልጋይ ይጠበቃል፡፡ ይህም የእምነታችን፣ የሃይማኖታችን፣ የመንፈሳዊ ዕውቀታችንና ክርስቲያናዊ ተግባራችን መለኪያ ነው፡፡

‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው›› ቅዱስ ያሬድ

ከማንም አስቀድሞ አገልግሎት ለአምላካችን እግዚአብሔር ይገባል፤ በጥንተ ተፈጥሮ በመጀመሪያው ቀን የተፈጠሩት መላእክት ፈጣሪያቸውን ዘወትር ያለማቋረጥ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እንደሚያመሰግኑት ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በመጽሐፈ አክሲማሮስ ገልጾልናል፡፡በዕለተ ዓርብ ሰው ሲፈጠር እንደ መላእክቱ የፈጠረውን ጌታውን እንዲያመሰግን፣ እንዲያገለግል እንዲሁም ስሙን እንዲቀድስና ክቡርን እንዲወርስ በመሆኑም የቀደመ ሰው አዳምም አምላኩን እያመሰገነና በገነትም በጸሎት እየተጋ ኖሯል፡፡

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ክህነት በዘመናችን በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ ያለ፣ ልዩ ትኩረትን የሚሻ ዐቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ያልተማሩ ከድንቁርናቸው፣ ሥርዓት አልበኞቹም ከክፉ መንገዳቸው እንዲላቀቁ፣ በቆሬ መንገድ የቆሙ ከመንገዳቸው እንዲመለሱ የሚያደርግም ኃይል ነው፡፡

ሥነ ፍጥረት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ዐቢይ ጾምን እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ባለፈው ትምህርታችን ዕድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ማንኛውም ክርስቲያን ጾምን መጾም እንዳለበት በተማርነው መሠረት እንደ ዓቅማችሁ እየጾማችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው! መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፡፡ ባለፈው “የእግዚአብሔር ባሕርያት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር ስለፈጠራቸው ፍጥረታት እንማራለን!

ደብረ ዘይት፡- ዳግም ምጽአት

በመዋዕለ ስብከቱ ስለ ዳግም ምጽአቱና ምልክቶቹ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በዝርዝር በደቀ መዛምርቱ በኩል አሳውቆናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡…