Entries by Mahibere Kidusan

“ባለፉት 34 ዓመታት በአገልግሎት የራቁትን ማቅረብ፣ የቀረቡትን ደግሞ ለንስሐ ሕይወት ለእግዚአብሔር መንግስት ማብቃት ትልቅ ነገር ነው።” ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ጅግጅጋና የምሥራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል

ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ጅግጅጋና የምሥራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል    የብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስካየ ኃዙናን መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም የበላይ ኀላፊ ሊቀ ጳጳስ ተወካይ በጉባኤው ተገኝተው መመሪያ አስተላልፈዋል። […]

ማኅበረ ቅዱሳን 34ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ

ማኅበረ ቅዱሳን 34ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በአበው ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በማኅበሩ ሕንጻ 3ኛ ወለል ንቡረ ዕድ ድሜጥሮስ አዳራሽ ከቀኑ 8 ሰዓት አክብሯል። በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል  የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ […]

 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

      “ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም፤ በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ) በመምህር ብንያም “አነ ጽጌ ገዳም ጽጌ ደንጎላት ዘውስተ ቄላት ወከመ ጽጌ ደንጎላት በማእከለ አስዋክ-እኔ የምድረ በዳ አበባ ነኝ በቆላ ውስጥ ያለ በሾህ መካከል የበቀለ የሱፍ አበባ ነኝ።” (መኃ.፪፥፩) ብሎ ነቢዩ ሰሎሞን እንደተናገረ ግንቦት አንድ ቀን በምድረ በዳ በአድባረ ሊባኖስ የበቀለችውን አማናዊት ንጽሕት የሱፍ ፣ የጽጌረዳ […]

፻፴፬ ኛው የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልአተ ጉባኤ ላይ በቅዱስነታቸው የተላለፈ አባታዊ መልእክት

፻፴፬ ኛው የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልአተ ጉባኤ ላይ በቅዱስነታቸው የተላለፈ አባታዊ መልእክት ሚያዝያ ፳፳/፳፻፲፰ ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የግንቦት ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የመክፈቻ አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ ኣምላክ ኣሜን! ብፁዕ […]

በአሜሪካ ቦስተን ከተማ የበገና እና የመሰንቆ ተማሪዎች ተመረቁ

ሚያዝያ ፳፰/፳፻፲፰ ዓ.ም   በማኅበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማእከል ቦስተን ንዑስ ማእከል በገና እና መሰንቆ በተለያየ ዙር ሲማሩ የነበሩትን በቦስተን አካባቢ የሚገኙ ሕጻናት እና አዋቂዎቸን ቅዳሜ ሚያዝያ ፳፬ ቀን ፳፻፲፰  ዓ.ም አስመርቋል።   በመርሐ ግብሩ አርባ አንድ የበገና እና ሦሰት የመሰንቆ ተማሪዎች የተመረቁ ሲሆን በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የበገና እና የመሰንቆ ዝማሬ አቅርበዋል።   በመጨረሻም ለተመራቂዎች […]

አዲስ አበባ ማእከል 26 ለሚሆኑ የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና መጠናቀቁን አስታወቀ

አዲስ አበባ ማእከል 26 ለሚሆኑ የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና መጠናቀቁን አስታወቀ ሚያዝያ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ስብከተ ወንጌልና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት ዋና ክፍል ከተለያዩ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ለተውጣጡ 26 የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ማእከል አስታውቋል። በሥልጠናው […]

ለአንድ ወር ያክል ሲሰለጥኑ የቆዩ 28 ተተኪ አመራሮች መመረቃቸው ተገለጸ

ለአንድ ወር ያክል ሲሰለጥኑ የቆዩ 28 ተተኪ አመራሮች መመረቃቸው ተገለጸ ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል አባላትና ማስተባበሪያ አገልግሎት ዋና ክፍል ከየካቲት 14 እስከ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለአንድ ወር ያክል ሲያሠለጥናቸው የቆዩ ተተኪ አመራር ሠልጣኞችን  ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም አስመርቋል። በመርሐግብሩ  የማእከሉ መዘምራን ያሬዳዊ መዝሙር ያቀረቡ ሲሆን  ትምህርተ ወንጌል […]

አሜሪካ አቀፍ የአቡነ ጎርጎርዎስ ተማሪዎች ዓመታዊ ውድድር መካሄዱ ተገለጸ

ፖርትላንድ የአጠቃላይ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ ሚያዝያ ፳/፳፻፲፰ ዓ.ም በአሜርካ በሀገር አቀፍ ደረጃ  ሁለተኛው የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (April 25, 2026)  በችካጎ ከተማ  መደረጉን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች አስተዳደር ቦርድ ገልጿል:: ውድድሩ በመጀመሪያ በእያንዳንዱ ትምህርት ቤትና ቀጥሎም በማስተባበሪያ ማእከል ደረጃ በአራት የዕድሜ ክልል ተከፍሎ የተደረገ ሲሆን በአንድ የዕድሜ […]

‹‹ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፤ የጻድቅ መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል›› (መዝሙረ ዳዊት ፻፲፩፥፮)

የምድራዊ ሕይወት ውጣ ውረድን አልፎ፣ የእሾህና አሜኬላዋን ሥቃይ ተቋቁሞ፣ ቀናውን የጽድቅ ጎዳና ተጉዞ፣ ሩጫውን በገድል ጨርሶ፣ በመልካም ፍሬ ዘለዓለማዊ ዕረፍትን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፡፡ ቅዱሱ መጽሐፍ ‹‹ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፤ የጻድቅ መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል›› ይለናል፡፡ (መዝሙረ ዳዊት ፻፲፩፥፮)   

ጾመ ነነዌ

ምሕረቱ የበዛው አምላካችን የነነዌ ሰዎችን ይቅር እንዳላቸው ሁሉ እኛንም ጸሎታችንን ሰምቶ፣ ልመናችንን ተቀብሎና ጾማችንን አስቦ ምሕረትን ያደርግልን ዘንድ ከክፋት ርቀን፣ ከቂም በቀል ከጥላቻ ነጽተን፣ በበጎነትና በመልካም ምግባር ጾሙን እንጹም!