‹‹በላይ ያለውን ሹ›› (ቈላ. ፫፥፩)
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቈላስይስ ሰዎች በላከው መልእክቱ እንደተናገረው ‹‹ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ በአለበት በላይ ያለውን ሹ፡፡ የላይኛውን አስቡ፤ በምድር ያለውን አይደለም፡፡ እናንተ ፈጽማችሁ ሞታችኋልና፤ ሕይወታችሁም ከክርስቶስ ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ የተሠወረች ናትና፡፡ ሕይወታችሁ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ፥ ያን ጊዜም ከእርሱ ጋር በፍጹም ክብር ትገለጣላችሁ፡፡›› (ቈላ. ፫፥፩-፬)