Entries by Mahibere Kidusan

በፊትህ ናት

በኀምሳኛው ዕለት መንፈስ ቅዱስ ሲያድርባቸው

በ፸፪ የተለያየ ዓይነት ቋንቋቸው

ሲናገሩ ተገረሙ አሕዝቡ ሰምተው

በእግዚአብሔር ሥራ እጅግ ተደንቀው

የወንጌሉን ቃል ሲረዱ ተነክቶ ልባቸው

ሦስት ሺህ ነፍሳትም ተጠመቁ አምነው…

አባ ገሪማ ዘመደራ

…አባ ገሪማ መጽሐፍ እየጻፉ ከቆዩ በኋላ መምሸት በመጀመሩ ፀሐይ ሊጠልቅ ተቃረበ፤ ያን ጊዜም በጸሎታቸው ጽሕፈታቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ፀሐይን በቦታው እንዲቆም አደረጉ፤ በኋላም ከእጃቸው የወደቀው ብዕር ወዲያው በቅሎ፣ አቈጥቍጦ አደገ፡፡ ምራቃቸውን ትፍ ያሉበት ሥፍራም እስከ ዛሬ ድረስ ሕሙማንን ይፈውሳል፡፡

‹‹በሥጋችሁ ፈቃድ ለነጻነታችሁ ምክንያት አታድርጉላት›› (ገላ. ፭፥፲፫)

ነጻነት አለኝ ብሎ እንደ ልብ መናገር፣ ያሰቡትን ሁሉ መፈጸም አእምሮውን ያጣ ሰው መገለጫ እንጂ ጤነኝነት አይደለም፡፡ ፍጡራን እንደመሆናችን መጠን ነጻነታችን ገደብ አለው፡፡ ለነጻነቱ ገደብ የሌለው ቸርነቱ ካልከለከለው በቀር ሁሉን ማድረግ የሚችል እርሱ ልዑል አምላክ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ቀዳማዊው ሰው አዳም አምላካችን እግዚአብሔር ሲፈጥረው ነጻ አድርጎ የፈጠረው መሆኑ ባያጠያይቅም ፍጡር እንደመሆኑ መጠን ደግሞ ‹‹በገነት ካለው ዛፍ ብላ፤ ነገር ግን መልካሙንና ክፉን ከሚያሳየውና ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና›› ብሎ ገደብ አስቀምጦለታል፡፡ (ዘፍ. ፪፥፲፮-፲፯)

የሐዋርያት ጾም

ሐዋርያት ወንጌለ መንግሥት እንዲስፋፋና በሕዝብም ሆነ በአሕዛብ ዘንድ አገልግሎታቸው የሠመረ እንዲሆን መንፈስ ቅዱስን በተቀበሉ በበዓለ ሃምሳ ማግሥት  ጾም ጀመሩ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያቱ በሰጣቸው ሥልጣን ድውያንን መፈወስና አጋንንትን ማውጣት እንዲሁም የተለያዩ ገቢረ ተአምራትን ይፈጽሙ ዘንድ ጸሎትና ጾም ያስፈልጋቸው ነበርና፡፡ በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው ጌታችን ጋኔን ያለበትን ልጅ ካዳነው በኋላ ሐዋርያቱ ስለምን እነርሱ ጋኔን ከሰው ማውጣት እንዳልቻሉ በጠየቁት ጊዜ እንዲህ ሲል መልሶላቸዋል፤ ‹‹…ይህ ዓይነቱ ግን ያለጾምና ጸሎት አይወጣም፡፡›› (ማቴ.፲፯፥፳፩)

ርደተ መንፈስ ቅዱስ

ርደተ መንፈስ ቅዱስ ወይንም የመንፈስ ቅዱስ መውረድ በብሉይ ኪዳን በትንቢት የተነገርና  በሐዲስ ኪዳን የተፈጸመ ነው፡፡ ነቢዩ ኢዮኤል ስለ መንፈስ ቅዱስ ወደዚህ ዓለም መውረድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ሀብትነት ዓለም እንደሚታነጽና ሃይማኖት እንደሚጸና እንዲህ ሲል ተናግሯል፤ ‹‹ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ካይ አፈሳለሁ፡፡›› (ኢዩ. ፪፥፳፰)

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል

አንድ አምላክ በኾነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ዐሥራ ሁለት፤ በዚች ዕለት የከበረ የመላእክት አለቃ የመልአኩ የሚካኤል የመታሰቢያውን በዓል ያከብራሉ፡፡ የሚያከብሩበትም ምክንያት እንዲህ ነው፤…

‹‹ጌታችን በመለከት ድምጽ ዐረገ›› (መዝ. ፵፮፥፭)

ነቢዩ ዳዊት ለመዘምራን አለቃ የቆሬ ልጆች አስቀድሞ በመንፈሰ ትንቢት ‹‹አምላካችን በዕልልታ፥ ጌታችንም በመለከት ድምጽ ዐረገ፥ ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ››  በማለት እንደተናገረ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን ፈጽሞ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በዐርባኛው ቀን ዐርጓል፤ እኛም ይህንን ቃል በማሰብና በማክበር የጌታችንን የዕርገት በዓል ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን አመላካች በመሆኑ በዝማሬ እና በዕልልታ እናከብር ዘንድ ይገባል፡፡ (መዝ.፵፮፥፭)

‹‹ከፊት ይልቅ ትጉ›› (፪ ጴጥ. ፩፥፲)

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ ከቀደመ ተግባራችን ይልቅ እንድንተጋ ያስተማረበት ኃይለ ቃል እንዲህ የሚል ነው፤ ‹‹እናንተ ግን በሥራው ሁሉ እየተጋችሁ፥ በእምነት በጎነትን፥ በበጎነትም ዕውቀትን ጨምሩ፤ በዕውቀትም ንጽሕናን፥ በንጽሕናም ትዕግሥትን፥ በትዕግሥትም እግዚአብሔርን ማምለክን፥ እግዚአብሔርም በማምለክ ወንድማማችነትን በወንድማማችነትንም ፍቅርን ጨምሩ፤ እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጓችኋልና፡፡ እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብ ያለውን ብቻ ያያል፤ የቀደመውንም የኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል፡፡ ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ፥ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህንም ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉም፡፡ እንዲሁ ወደ ዘለዓለም ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በምልአት ይሰጣችኋል፡፡›› (፪ ጴጥ. ፩፥፭-፲፩)

‹‹ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል፤ ዋጋዋ ከቀይ ዕንቊ እጅግ ይበልጣል!›› (ምሳ. ፴፩፥፱)

ዓለማችን የልዩነት መድረክ ናት፡፡ ልዩነቶቹ እንዲህ፣ እንዲያ፤ አንድ እና ሁለት ተብለው የማይወሰኑ ናቸው፡፡ ሴትነትና ወንድነትም የጾታ ልዩነት አንድ መደብ ናቸው፤ የሴት መሆንም የወንድ መሆንም መገናኛው ሰው መሆን ነው፡፡ ጥያቄው ታዲያ ምን ዓይነት ሴት ወይም ምን ዓይነት ወንድ እንሁን፤ ከዚያም ምን ዓይነት የሰው ልጅ ይኑር የሚለው ነው፡፡ ወንድ የሚለው ስም ብቻውን ወደ ሰውነት አያደርስም፤ ሴት ተብሎ መጠራትም ሴት የመሆንን ትክክለኛ መዳረሻ ጥግ አያመጣውም፡፡ ሁሉ በተገቢው ሚዛን ሊመዝነው የሚችለውን ሚዛን መምረጥ አለበት፡፡