ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለ ፫ ተከታታይ ቀናት በመላው ዓለም የታወጀው የነነዌ ፆም እና ምሕላ መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1082 entries already.
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለ ፫ ተከታታይ ቀናት በመላው ዓለም የታወጀው የነነዌ ፆም እና ምሕላ መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ፡፡
ከዚህ ኃይለ ቃል ሦስት ነገሮችን እንማራለን፤ አንደኛ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር አምላክ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት መሆኑን፣ ሁለተኛ ጳጰስ አድርጎ የሚሾም መንፈስ ቅዱስ መሆኑን፣ ለመንጋውና ለራሳችን መጠንቀቅ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን መሰነባባቻ ባደረገው ንግግር ይህን ኃይለ ቃል ተናግሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሦስት ሺህ ዘመናት ውስጥ የቆየው ቀኖና፣ሥርዓተ ሢመት፣ ትውፊት ቅብብሎሽ በአሁኑ ዘመን ለመሻር መንጋውን እየበተነ አባቶችን እየሸረሸረ ያለውን ክስተት ሁሉ በየደረጃው ያለው የድርሻውን ለመወጣት ከማንኛውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት የምንነሣበት ጊዜ መሆኑን ነው፡፡
ይህን ቃል የምናገኘው በትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ ውስጥ ነው፤ የተናገሩት ደግሞ እግዚአብሔርን የማያመልኩ ይልቁንም ጣዖት አምላኪ ሰዎች ናቸው። በነነዌ ሀገር ንጉሡ ስልምናሶር በነገሠበት ዘመን የነነዌ ሕዝቦች እግዚአብሔርን በደሉ፣ ከሥርዓቱ ፈቀቅ አሉ፤ ጣዖት አምላኪዎች ሆኑ፤ ጩኸትም አበዙ።
እግዚአብሔርም ተቆጣቸውና ሊገሥጻቸው ዮናስን “ተነሥና ወደ ነነዌ ሀገር ግባ፤ በድለውኛልና ነነዌ በሦስት ቀን ትጠፋለች ብለህ ስበክ” አለው። ዮናስ ግን “የአንተ ምሕረት እጅግ የበዛ ሲሆን ትጠፋለች ብዬ ተናግሬ እሳት ከሰማይ ሳይወርድ ቢቀር ሐሰተኛ ነቢይ ልባል አይደለምን?” አለና ከእግዚአብሔር ሊደበቅ መንገድ ጀመረ። (ዮና.፩፥፩-፫)….
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የጥምቀት በዓል እንዴት አለፈ? እናንተስ የጥምቀትን በዓል እንዴት አከበራችሁት? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ አብነት ለመሆን እንዲሁም ደግሞ የዕዳ ደብዳቤያችንን ሊደመስስልን መጠመቁን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በደስታ በምስጋና በዓሉን እናከብራለን፡፡ መቼም ልጆች! ከወላጆች አልያም ከጓደኞቻችን ጋር በመሆን አክብራችኋል፤ መልካም!
ሌላው ደግሞ ወቅቱ ለእናንተ ለተማሪዎች የዓመቱ አጋማሽ የምዘና ፈተና ነበር! ፈተናስ እንዴት ነበር? እንግዲህ የዓመቱ አጋማሽ የትምህርት ወቅት አልቆ ፈተናም ተፈትናችሁ ውጤት የተሰጣችሁ እንዲሁም ውጤት በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ትኖራላች፡፡ ከባለፈው ውጤታችሁ በመነሣት በቀጣዩ የትምህርት ጊዜ በርትታችሁ ለመማር እንደ ምታቅዱ ተስፋችን እሙን ነው፡፡ ደግሞ በዕረፍት ጊዜያችሁ መልካምን ነገር በማድረግ አሳለፉ፡፡ በርቱ! ለዛሬ የምንነግራችሁ ከጥምቀት በኋላ ክርስትና ምን ይመስላል የሚለውን እንመለከታለን፤ መልካም ቆይታ!
በጻድቁ ኢዮብ መጽሐፍ የተጻፈ ኃይለ ቃል ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በዕለተ ሐሙስ “ውኃ ሕያው ነፍስ ያላቸውን ተንቀሳቃሾች ታስገኝ” በማለት ቃል በተናገረ ጊዜ በልባቸው የሚሳቡ፣ በእግራቸው የሚሽከረከሩ፣ በክንፋቸው የሚበሩ ፍጥረታት ከባሕር ተገኙ፡፡ (ዘፍ.፩፥፳)
በባሕር ከተፈጠሩ ከነዚህ ፍጥረታት የሚበሉና የሚገዙ፣ የማይበሉ የማይገዙም አሉ፡፡ ከባሕር ጸንተው የሚኖሩ አሉ፤ አንድ ጊዜ በየብስ አንድ ጊዜ በባሕር የሚኖሩ አሉ፤ በክንፋቸው በረው ከባሕር ወጥተው የቀሩም አሉ፡፡ (መጽሐፈ ሥነፍጥረት ምስለ አምስቱ አእማደ ምሥጢር፤ ገጽ ፷፤ ሥነ ፍጥረት ክፍል ሦስት ለከፍተኛ የመንፈሳዊ ትምህርት ተማሪዎች የተዘጋጀ ገጽ ፵)
ቅዱስነታቸው በጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
እንኳን ለእናታችን ለቅድስተ ድንግል ማርያም በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!
የቅድስት ድንግል ማርያም ሞት ግን ይደንቃል! የሞትን ኃይል ያጠፋ፣ ሞትን በሞቱ የገደለ፣ ክርስቶስን ወልዳ ሳለ መሞቷ ይደንቃል። እናም “ለምን ሞተች?” ብሎ መጠየቅ የተገባ ነው፤ ይኸውም በተአምረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው በሲኦል ያሉ ነፍሳትን አሳይቷት ስለነበር በልጇ ሞት ነፍሳት እንደዳኑ በእርሷ ሞትም ነፍሳትን እንደሚያድንላት ስለነገራት ስለ ኃጢአተኞች ነፍሷን በልጇ ትእዛዝ ሰጠች።
