ትንሣኤ

ለሰው ልጆች ዘለዓለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ መድኃኒዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለና ነፍሱን በራሱ ሥልጣን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ዐርብ በ፲፩ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደውና ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሠራው መቃብር በንጹሕ በፍታ ገንዘው ቀበሩት፤ መቃብሩንም ገጥመው ሲሄዱ ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ፡፡ በሦስተኛው ቀን እሑድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ!!!

አንተ ጽኑ አለት ነህ

በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ

እያለ ሲነግረው ጌታችን  ለጴጥሮስ

በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር

በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር

ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር

መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!

ሰሙነ ሕመማት

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ሰነበታችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የዐቢይ ጾም ወቅትንስ እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ይህ ጾም ጠላታችን ዲያቢሎስ ያፈረበት፣ ትዕቢት፣ ስስት፣ፍቅረ ንዋይ ድል የተደረጉበት፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጹሞ እንጾም ዘንድ ባርኮ የሰጠን ታላቅ ጾም ነው፡፡ ታዲያ ይህን ወቅት መልካም ሥራ እየሠራን፣ ለሀገር፣ ለቤተ ክርስቲያን እየጸለያችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋ እናደርጋለን! መልካም!

ውድ የእግአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት በዐቢይ ጾም ስለሚገኙ ሳምንታት ስያሜ ባስተማርናችሁ መሠረት በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? አሁን ደግሞ ስለ ሰሙነ ሕማማት ጥቂት ልናካፍላችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ

ሆሣዕና

‹ሆሼዕናህ› ከሚለው በዕብራይስጥ ቃል የተገኘው ‹ሆሣዕና› ትርጉሙ ‹እባክህ አሁን አድን› ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ ‹‹አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡›› (መዝ.፻፲፯፥፳፭-፳፮) የሆሣዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና ሕፃናት ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም›› በማለት ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡ በዓሉም ሆሣዕና የሚለውን ስያሜ ያገኘው በዕለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡ (ዮሐ.፲፪፥፲፫)

ንዑስ አንቀጽና ቅጽሎች

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሦስት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታን እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ በተማራችሁት መሠረት ላቀረብንላችሁ የመልመጃ ጥያቄዎች ምላሻቸውን እንዲሁም ‹ንዑስ አንቀጽና ቅጽሎች› በሚል ርእስ የዛሬውን ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!     

‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› (መዝ.፯፥፱)

ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› በማለት አስተምሯል፡፡ (መዝ.፯፥፱) ከዚህም ቃል እንደምንረዳው አምላካችን የሚሣነው ነገርም ሆነ ከእርሱ የሚሠወረውም ነገር እንደሌለ ነው፡፡ ሁሉንም ሳንነግረው የሚያውቅ አምላክ እንደሆነ ያሰብነውን ብቻም ሳይሆን ገና ያላሰብነውን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡

ኒቆዲሞስ

በግሪክ ቋንቋ ኒቆዲሞስ የሚለው ቃል ትርጓሜ ድል ማድረግን ወይም አሸናፊነትን የሚያመለክት ነው፡፡ በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሚሰብክበት ጊዜ አንድ ፈሪሳዊ ከአይሁድ አለቆችና መምህራን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ ሰው እንደነበረና የጌታችንን ቃል በሌሊት ወደ እርሱ በመሄድ እንደተማረ በወንጌለ ዮሐንስ ተጠቅሷል። (ዮሐ.፩፥፪)

በዓለ ፅንሰት

በተከበረች መጋቢት ፳፱ ቀን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የከበረ መልአክ ገብርኤል የምሥራች የነገረበት ድኅነትን የተመላች ታላቅ በዓል ናት፡፡ በዚህም የከበረ ወንጌል ምስክር ሆኗል፡፡

ዝርዝር ርባታ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሁለት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ የመጨረሻውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ጥንተ ስቅለት

ለዓለም ሁሉ ድኅነት መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት በባተ በ፳፯ኛው ቀን በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ልጆቹም ይህን እናዘክር ዘንድ ዓይን ልቡናችንን ወደ ቀራንዮ እናንሣ!