ዓሣ

ወርቅ ሠሪው ጴጥሮስ(ለሕፃናት)

በእመቤት ፈለገ

ልጆች እንደምን ሰነበታችሁ? ዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው የአንድ ጌጣጌጥ የሚሠራ ሰው ታሪክ ነው ተከታተሉ፡፡

ከብዙ ዓመታት በፊት ስሙ ጴጥሮስ የተባለ በጣም ጥሩ ክርስቲያን ነበር፡፡ የተለያዩ ጌጣጌጦች ማለትም ቀለበት፣ የአንገት ሃብል ይሠራ ነበር፡፡

ብዙ ጊዜም ቤተ ክርስቲያን መሄድ ያስደስተው ነበር፡፡ እርሱ በሚኖርበትም አካባቢ የሚገኝ በእግዚአብሔር የማያምን አንድ መጥፎ ሰው ነበር፡፡ ጴጥሮስንም እጅግ በጣም ይጠላው ነበር፡፡ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሊጎዳው ይፈልግ ነበር፡፡ ምክንያቱም ጴጥሮስ እግዚአብሔርን ስለሚወደው ነበር፡፡ ይህ ክፉ ሰው የአንድ የመንግሥት ባለሥልጣን ጸሐፊ ነበር፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን የመንግሥት ባለሥልጣን የነበረው ሰው ቀለበት ማሠራት ፈለገ እንዲያሠራለትም ለዚያ ክፉ ሰው ሰጠው፡፡ ያ መጥፎ ሰውም ጴጥሮስን ለመጉዳት ጥሩ አጋጣሚ እንዳገኘ አሰበና ደስ አለው፡፡ ወደ ጴጥሮስም ሄደና ቀለበቱን ሰጠው፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣኑ ቀለበት እንደሆነ ቆንጆ አርጎ በፍጥነት እንዲሠራ ነገረው፡፡ ጴጥሮስም ቀለበቱን ተቀብሎ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠውና ሌላ እንግዳ ማስተናገድ ጀመረ፡፡ ክፉውም ሰው ቀለበቱን ሰርቆ ሄደ ወንዝ ውስጥ ጣለው፡፡ ጴጥሮስ ቀለበቱን ሲፈልግ አጣው በጣም አዘነ የመንግሥት ባለሥልጣኑም ይህን ሲሰማ ምን ሊያደርገው እንደሚችል አሰበ እጅግ ጨነቀው ሱቁንም ዘግቶ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡

ቤቱ እንደገባም የሆነውን ሁሉ ለባለቤቱ ነገራት እርሷም እግዚአብሔር ከነርሱ ጋር እንደ ሆነ ምንም መፍራት እንደሌለበት ነገረችው፡፡ በሚቀጥለውም ቀን ወደ ሥራ ሄደ ነገር ግን በጣም ስለተጨነቀ ምንም ሥራ መሥራት አልቻለም፡፡ ዓሣ የሚሸጥ ሰው በየቀኑ ለጴጥሮስ ዓሣ ይዞለት እየመጣ ይሸጥለት ነበር፡፡ ያን ቀን ግን ጴጥሮስ ዓሣ ሻጩን ሲያየው “ዛሬ ምንም አልፈልግም አለው፡፡ ዓሣ ሻጩም ጥሩ ዓሣ እንደያዘ ነገረው ጴጥሮስ ግን “በፍጹም አልገዛም” አለው፡፡ ዓሣ ሻጩም ወደ ጴጥሮስ ቤት ሄደ ዓሣውን ለሚስቱ ሸጠላት፡፡

ዓሣየጴጥሮስ ሚስትም ዓሣውን ገዝታ መሥራት ስትጀምር በጣም የሚያብረቀርቅ ነገር አየች ቀለበት ነበር! ልክ ባለቤቷ ወደ ቤት ሲመጣ የተፈጠረውን ነገር ማመን አቃተው፡፡ እግዚአብሔር ሕይወቱን ጠበቀለት፡፡

ጴጥሮስን ከክፉ ነገር ሁሉ የጠበቀው አምላክ እኛንም ከክፉ ነገር ይጠብቀናል፡፡ ስለዚህ ልጆች ሁል ጊዜም ስለሚደረግልን ነገር ሁሉ እግዚአበሔርን ማመስገን አለብን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔ

በደህና ሰንብቱ ልጆች!

 

“በእንተ ጦማረ ሐሰት”

ግንቦት 13፣ 2003 ዓ.ም

በሐሰት የተሠራጨውን ሰነድ በተመለከተ ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠ መግለጫ

እምነትና ሥርዓቷ ጸንቶ የቆየውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕልውናዋን ለማሳጣት እና ሐዋርያዊ ተልእኮዋን ለማደናቀፍ ቀን ከሌሊት የሚተጉ አካላት የጥፋት ሤራቸውን ከመጎንጎን እና የተቻላቸውን ሁሉ ከመፈጸም ወደ ኋላ ብለው አያውቁም፡፡ ቅድስት ቤተክርቲያን ሕግና ደንብ አውጥታ በመዋቅሯ አቅፋ እንዲያገለግል አደራና ሓላፊነት የሰጠችው ማኅበረ ቅዱሳንም የጥቃታቸው አንዱ አላማ ነው፡፡ የማኅበሩን ቀና አገልግሎት ለማስቆም ብዙ ጥረዋል፡፡
 
በእግዚአብሔር ፈቃድና ቸርነት የተመሠረተ እንደመሆኑ የቅድስት ቤተክርቲያንን መመሪያ ጠብቆ በአባቶች ምክርና ጸሎት እየታገዘ አገልገሎቱን ከመፈጸም ወደኋላ አይልም፡፡ እነዚህ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚፈታተኑ አካላት የማኅበረ ቅዱሳንን ስም በማጥፋት እንደደከሙት ሁሉ፤ ሰሞኑን የማኅበሩን ማኅተም በተጭበረበረ ሁኔታ / ፎርጅድ/ በመጠቀም፣ "የማኅበሩ የሃያ አምስት ዓመት እቅድ" ነው በማለት የሐሰት ሰነድ አዘጋጅተው በኢንተርኔት ለማሠራጨት እና ለተወሰኑ ብፁዓን አባቶች እንዲደርስ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎቱ ሁሉ ግልጽ ነው፡፡ ባሳለፋቸው አሥራ ዘጠኝ የአገልግሎት ዓመታት እቅድና አፈጻጸሙ በየደረጃው ለሚገኙ የቤተክርስቲያን አካላት እና አባቶች እንዲሁም ለማኅበሩ ማእከላትና አባላት በየወቅቱ በሪፖርት የሚገለጽ ውይይት የሚደረግበት ሲሆን በዚሁ ሁኔታ ተግባራዊ የሚሆን ነው፡፡ ይህ የማኅበሩ አሠራር በተገቢው ሁኔታ ወደፊትም ይቀጥላል፡፡ ሰሞኑን የተሠራጨውን የሐሰት ጽሑፍ በተመለከተ የማኅበሩን መግለጫ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ ሰሞኑን “ድንግል ማርያም” በተባለ የፌስ ቡክ አድራሻ(face book Account) “የማኅበረ ቅዱሳን የረዥም ጊዜ እቅድ” በሚል የተበተነ የሐሰት ጽሑፍ እንዲወጣ (Post) መደረጉ ታውቋል፡፡ ይህ ጽሑፍ በመጨረሻው ላይ የማኅበረ ቅዱሳን የሃያ አምስት ዓመት እቅድ እንደሆነ ይገልፃል፡፡ ለመሆኑ ይህ “ጦማረ ሐሰት” ምንጩ ከየት ነው? ጽሑፉ እንዳመለከተው በውኑ የማኅበረ ቅዱሳን እቅድ ነውን? ይዘቱና ዓላማውስ ምንድን ነው? ማኅበረ ቅዱሳንስ በዚህ ጽሑፍ ላይ ያለው አቋም ምንድን ነው?

ምንጩ ከየት ነው?
ጽሑፉ በራሱ ሥልጣን እየተጣጣረም ቢሆን ለመናገር የሚሞክረው "የማኅበረ ቅዱሳን ነኝ" እያለ ነው፡፡ ነገር ግን በመናገር እና በመሆን መካከል ያለውን ርቀት እንዳይፈራገጥ ባስገነዘው ጣእረ ሞት እንደያዘው የሚይዘውን የሚጨብጠውን ያጣ ወረቀት ነው፡፡ ለዚህም ጽሑፉ ሳያውቀው ምንጩን ሲናገር እናገኘዋለን፡፡ ይሁን እንጂ በመጀመሪያ ምንጩ ማኅበረ ቅዱሳን ሊሆን ይችላልን?

የሚለውን መመልከቱ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እቅድ እያቀደ የእግዚአብሔርን አጋዥነት እየለመነ አገልግሎትን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ እቅድ ማቀድ በማኅበሩ ዘንድ እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ በጥቂቱ የሃያ ዓመት ልምድም ያለው ማኅበር ነው፡፡ አባላቱም ከመንፈሳዊው አገልግሎት ባሻገር በየተሠማሩበት የሙያ ዘርፍ እቅድ እያቀዱ ራሳቸውን በዘመናዊው አሠራር ያበለጸጉ ከመሆናቸው አንጻር መሠረታዊ የእቅድ አዘገጃጀት እውቀት ያላቸው መሆኑን ልንጠራጠር አንችልም፡፡ የተበተነው ጽሑፍ ያውም ሁለት ከወገብ በታች /ግማሽ ገጽ/ የሆኑ ወረቀቶች ላይ ማኅበሩ የሃያ አምስት ዓመት እቅድ ተብሎ ተዘርዝሯል፡፡ እንዲህ አይነቱ የሃያ አምስት ዓመት እቅድ ማቀድ   በአዘጋጆቹ ዘንድ የተለመደ ይሆናል እንጂ በማኅበረ ቅዱሳን ዘንድ የለም፡፡ የማኅበሩ የአራት ዓመት ስልታዊ እቅድ እንኳን የተዘጋጀው በሃምሳ አምስት ገፆች ነው፡፡

ስልታዊ እቅድ እንደመሆኑ መጠን በዘመናዊው አሠራር የራሱ ቅርጽ (format) አለው፡፡ ቢያንስ ቢያንስ መግቢያ፣ የማኅበሩን ማንነት፣ የማኅበሩ ዓላማ፣ ርእይ፣ ተልእኮ፣ እሴት፣ የባለድርሻ አካላት ትንተና፣ ውጫዊ አካባቢ ትንታኔ፣ እንዲሁም አስፈላጊነቱ ሌሎች ትንታኔዎች ምቹ እና ፈታኝ ሁኔታዎች፣ የምቹ እና ፈታኝ ሁኔታዎች ምዘና፣ ወሳኝ ጉዳዮች፣ ስልታዊ እቅድ ዓላማ፣ ግብና ስልት፣ ዝርዝር የአፈጻጸም መርሐ ግብር እንዲሁም የክትትልና የግምገማ ሥርአት ያለው ሊሆን ይገባል፡፡

በዚህ ቅርጽ መሠረት የማኅበረ ቅዱሳን ስልታዊ /ስትራቴጂክ/ እቅዱን አዘጋጅቶ  ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት በማቅረብ በእቅዱ መሠረት አገልግሎቱን በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ አሠራሩ ያልተመቻቸው አካላት የጐንዮሽ እቅድ በማቀድ የራሳቸውን የፈጠራ ሥራ አቅርበዋል፡፡ማኅበረ ቅዱሳንን ለመወንጀል ታስቦ የሐሰት ሰነድ (forged document) ተዘጋጅቶ የተበተነበትም ምክንያት ያንን እቅድ አባቶች እንደማያውቁት በማስመሰል ነው፡፡

የፖለቲካ አጠቃቀም
ማኅበሩ በመዋቅሩ ሥር ያሉትን አካላት በራሱ መጥራት የተሳነው አስመስለው ቀርጸውታል፡፡ ለማሳያ የሚሆነውም በዝርዝር እቅዱ ውስጥ በአንድ ላይ "በየንዑሳን ቅርንጫፍ በኩል" የሚል ሐረግ ይገኛል፡፡ ሲጀምር ማኅበሩ ቅርንጫፍ የሚባል ምንም ዓይነት መዋቅር የለውም፡፡  
 
ከዋናው ማእከል ቀጥሎ ያሉት ማእከላት ይባላሉ እንጂ ንዑሳን አይባሉም፡፡ ይህም አጠቃቀሙ ሌላ አካል መሆኑን ያሳያል፡፡ በአስገራሚ ሁኔታ የተበተነው ወረቀት አንድ ተማሪ ክፍል ውስጥ ገብቶ ሲማር ከሚይዘው ማስታወሻ እንኳ ያነሰ፤ እቅድ መባል ካለበት እንኳ የጨነገፈ እቅድ ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ሊያወጣው አይችልም፡፡ በዚህ መስፈርት እንኳን ቢታይ እቅዱ በምንም መለኪያ የማኅበረ ቅዱሳን አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ራሱን ሲጠራ ”ማህበረ ቅዱሳን” ብሎ አያውቅም። "እቅድ" የሚለውን ቃል አቅድ የሚለውን ተክቶ ለጥቅም እንዲውል አድርጐም አያውቅም፡፡ እነዚህን የተጠቀመው ጽሑፍ ራሱን እርቃኑን አቁሞ የማኅበረ ቅዱሳን አለመ ሆኑን የገለጠበት ዘርፍ ነው፡፡ ወረቀቱ ስለ እቅድ የሚናገር ከሆነ የተግባራዊነት ዘመኑ ከመቼ እስከ መቼ እንደሆነ እንኳ አለመገለጹ ድንገቴ እንደ ወራጅ ውኃ የፈሰሰ የጥቂቶች አሳብ እንጂ እቅድ አለመሆኑን ያሳብቅበታል፡፡ የስሕተት ሙሻዙር የጠመዘዛቸው አዘጋጆች እንደመሰላቸው እነርሱ ያስቀመጧቸውን በወንጀል ደረጃ የሚፈረጁ አደገኛ አሳቦች በማኅተም አትሞ በቲተር እና በፊርማ አስደግፎ ራሱን ለአደጋ አጋልጦ የሚያስቀምጥ ተቋም በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ይገኛል ብሎ ማሰብ ቂልነት ነው፡፡

በተሠራጨው እቅድ ላይ የተቀመጡት አሳቦች አሉታዊ እና አፍራሽ አስተሳሰቦች እንደመሆናቸው መጠን ማኅበሩ የቱንም ያክል ክፉ ነው ተብሎ ቢታሰብ እንኳ እንዲህ ያለ እቅድ በዚህ መልክ አዘጋጅቶ እና አንድ ቦታ አጠራቅሞ ይገኛል ተብሎ አይታሰብም፡፡ ያንን ያክል ክፋት ማርገዝ የቻለ እኩይ ሕሊና ቢኖር እንኳ አካሔዱን እና አቀማመጡን አይጠበብበትም ነበር የሚለው ለአንባቢ የሚተው ውሳኔ ይሆናል፡፡ እነዚህን አካሔዶች ጠቅልለን ስንመለከታቸው ምንጩ ለጊዜው የማኅበረ ቅዱሳንን በመጨረሻም የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጥፋት ሌት ተቀን ከሚለማመኑ አካላት የተቀዳ ለመሆኑ ከቶውኑ ማን ይመራመራል? መጽሐፍ “በክፋታቸው እየባሱ ይሔዳሉ” እንዳለው የማኅበረ ቅዱሳን መኖር የእግር እሳት ስለሆነባቸው በምን መንገገድ ስሙን ቢያጠፉ ተቀባይነት ሊያገኙ እንደሚችሉ ሁልጊዜ ወጥመድ ያጠምዳሉ፡፡ እስካሁን ድረስ የእግዚአብሔር ቸርነት ከልክሏቸው አልተሳካላቸውም እንጂ የወገባቸው የሐሰት ዝናር ሲያልቅባቸው በማኅበሩ ወንበር ተቀምጠው የሚናገሩ በማስመሰል ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ተልእኮ እንዳለው አድርገው ሊያቅዱለት ፈለጉ፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ካባ ለብሰው ያቀዱለት እቅድ ግን ከተለመደው ክሳቸው የወጣ አለመሆኑ ነው፡፡

እስካሁን ድረስ ማኅበሩን ለምን ትቃወማላችሁ ሲባሉ ይሰጡት የነበረውን መልስ እቅድ ነው ብለው አቀረቡት እንጂ ምንም አዲስ ነገር አላመጡም፡፡ ስለሆነም በዚህ በጻፉት እቅዳቸው ምክንያት ማንም ሊደነግጥላቸው አይችልም፡፡ በተቻላቸው መጠን የመጨረሻዋን ጥይት ለመተኮስ ሲጥሩ መልሶ ራሳቸውን ወጋቸው፡፡ በተጉበትም መጠን በመጐዳታቸው አሟሟታቸውን ለማሳመር የሐሰት እና የጥፋት እቅድ ለማኅበሩ አወጡለት፡፡ የሚጠባበቁት ውጤት በእነዚያ ወንጀሎች ምክንያት ያቀዱለት አካል እለቱኑ ታንቆ እለቱኑ ሲሞት ለማየት በጉጉት ኮርቻ ላይ ተቀመጡ፤ የፈለጉት ማኅበሩ እነርሱ ጐን ቆሞ ቤተክርስቲያንን አንዲያጠፋላቸው ነበር፡፡

ግን ምን ያደርጋል? እነርሱም ታወቁ ሕልማቸውም መከነ፡፡ ራሱን በራሱ ሲቃረን አንድ  ተቋም ራሱን ሲገልጽ ‘እኛ” በሚል ባለቤት ሊናገር እንደ ሚችል የተረዳ ነገር ነው፡፡ በጽሑፉ ላይ ግን አባቶችን አባላት በማድረግና ”ስብሰባቸው ላይ” የሚል አባባል ተጠቅመዋል፡፡ ስለራሱ እቅድ የሚናገር ሰው ”በስብሰባችን ላይ” ይላል እንጂ ”ስብሰባቸው ላይ” እንዴት ሊል ይችላል? በተጨማሪም ”በራሱ ጠቅላላ ጉባኤ መምራት” በማለት ማኅበሩ ራሱን ”እርሱ” እያለ እንዲጠራ አድርገው ጽፈዋል፡፡ እንዲሁም ”ካህናቱን ለድርጅቱ ሠራተኞች አድርጐ መቅጠር” በሚለው እቅዳቸው ላይ ”እርሱ” ብሎ ራሱን እንዲጠራ አድርገውታል፡፡

ከእነዚህ አገላለጾች የምንረዳው የሆነ አካል ራሱን አስገድዶ የማኅበሩ አካል አድርጐ በመቁጠር ስለማኅበሩ ሆኖ እንዲጽፍ እንደተጨነቀ ያሳያል፡፡ ታዲያ ምን ያደርጋል አልተቻለውም፡፡ ራሱን ጠፍሮ በማሠር ስለማኅበሩ እንዲናገር አሰቃየው እንጂ ስለሌላ ማኅበር እንደሚናገር ተገልጦበታል፡፡ ጸሐፊው ያለ እርሻው የበቀለ ከሌላ ዘር የመጣ ነውና የራሴ ነው ያለውን ማኅበር ”እነርሱ” ”እርሱ” እና ”እኛ” እያለ ጠራው፡፡ ያልሠለጠነ ውሸታም በመሆኑ እንዲጽፍላቸው የቀጠሩትን ሰዎች አጋለጣቸው፡፡ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወዴት መሸሸግ ይቻላል? የጨለማው መጋረጃ ተቀደደባቸው፣ ከእነ ተንኮላቸው እጅ ከፈንጅ ተያዙ፡፡ ወዲህና ወዲያ እንዳይሉ በራሳቸው ገመድ ተጠፍንገው ታሠሩ፡፡ እግዚአብሔር ይፍታችሁ ከማለት ውጭ ምን እንላለን?

ማኅበሩ ማኅበሩን ሲቃወም በዕቅዳቸው ውስጥ ማኅበረ ቅዱሳን የሚያሳትማቸውን ኅትመቶች ያለ ኤዲቶሪያል ቦርድ ኅትመት አከናውኖ ማሠራጨት የሚል የተጠላለፈ አሳብ አስቀምጧል፡፡ በመሠረቱ ማኅበረ ቅዱሳን በመዋቅሩ እንዳመለከተው ማንኛውንም ኅትመት ኤዲቶሪያል ቦርዱ ዓይቶት ሲፈቅደው ይታተማል፡፡ ታዲያ እንዴት አንድ ማኅበር የራሱን መዋቅር የጣሰ ለመሥራት ያቅዳል፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው ቦርዱን ማፍረስ ሲችል እንዴት ስለመጣስ ያስባል። እንዲህ ያለ ዕቅድ ታይቶም ተሰምቶም አያውቅምና ዕቅድ አውጪዎቹ በጣም የተራቀቁ መሆን አለባቸው፡፡ ዕቅዳቸውን ለራሳቸው ጥብቅና ሲያቆሙት ቅድስቲቱን እምነት ለመበረዝ የተነሡ የተሐድሶ ኦርቶዶክስ ዓላማ አራማጆች ስውር ተልኮአቸው በአሁኑ ወቅት ስለተነቃባቸው ከገቡበት አዙሪት ለመውጣት ሲፍጨረጨሩ ይታያሉ፡፡

ከዚህም መንገድ አንዱ ተሐድሶ የሚባል የለም የሚል መፈክራቸውን ማስተጋባት ነው፡፡ ዕቅድ ተብየውም ይህንኑ የተከተለ ሳያውቀው በስውር ዓላማቸው የተቃኘ የተነረተ የበሽታ ሆድ ሆኖባቸዋል፡፡ ስለሆነም ከዕቅዱ መካከል በአንዱ ላይ ታላላቅ የቤተክርስቲያን መሪዎችና ተሐድሶዎች /ፖለቲከኞች/ ናቸው በማለት ከምዕመኑ ሰላማዊ ቅብብል እንዳይኖራቸው የሚል ይገኛል /ቃላቱ እነርሱ እንዳስቀመጧቸው የተቀመጡ ናቸው/። በዚህ ዕቅድ ላይ ሁለት ዋና ዋና ነጥቦችን ማስተዋል እንችላለን፡፡አንደኛው ተሐድሶን ፖለቲከኛነት ጋር ለመቀላቀል መታሰቡ ሲሆን ሁለተኛው ግን ታላላቅ የቤተክርስቲያን መሪዎች ያሏቸውን የሚመለከት ነው፡፡ ተሐድሶ ማለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲየንን ሙሉ በሙሉ ወደ ፕሮቴስታንት ጐራ ለመክተት አቅዶ የሚሠራ ሲሆን ፖለቲካኛ ደግሞ ሌላ ለዕቅድ አዘጋጆች ግን ተሐድሶና ፖለቲካ ተቀላቅሎባቸዋል፡፡ እውን  ተቀላቅሎባቸው ይሆንን? መልሱ ለአንባቢው የሚተው ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ታላላቅ የቤተክርስቲያኗ መሪዎችን ማኅበረ ቅዱሳን ስማቸውን እንደሚያጠፋ ያመላክታል፡፡ ታላላቆችማ ታላላቆች ናቸው፡፡እነርሱን የሚቃወም ማንነቱ ግልጽ ነው፡፡ ስም ማጥፋትም ወንጀል ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ግን ተሐድሶ የሆኑትን ተሐድሶ ናችሁ ከማለት አስያፈገፍግም፡፡ ይህንን ሲያደርግ በማስረጃ እንጂ በተራ አሉቧልታ አይደለም፡፡ ነገር ግን ታላላቆችን አባቶች የሚነኩትን ማኅበሩም ዝም  አይላቸውም ተልኳቸው ይታወቃልና፡፡ ይሁን እንጂ ሊያስተላልፉ የፈለጉት ተሐድሶ የለም የሚለውን የዘወትር የጨለማ መጋረጃቸውን ለመሆኑ ማን ሁለት ጊዜ ያስባል? ድንጋይ ይቧጥጣሉ እንጂ መጋለጣቸው አይቀርም፡፡ ይህ ሁሉ የሐሰት ደበሎ ይገለጣል፡

የጽንሰ ሐሳብ ችግር

ከዝርዝር ዕቅዳቸው አንዱ ባልተጠኑ ትምህርቶች የቤተርክስቲያኗን ምዕመናን ደጋፊ ማድረግ ይላል። አንድ ጤናማና የሚያስብ አእምሮ ያለው ሰው ይህንን አባባል እንዴት ይረዳዋል? ብሎ መገመት እጅግ ቀላል ይሆናል፡፡ ዕቅድ እያቀደ ያለ አንድ አካል እንዴት ባልተጠና ትምህርት ሌላውን ሊያሳምን ይችላል? ዕቅዱን ያቀዱት ሰዎች የሰለቻቸው ይመስላል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት /የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ተማሪዎችን/ የሚያስተምረው በተጠና ሥርዐተ ትምህርት መሆኑን ያወቁ እንዴት ይህን ሊሉ ቻሉ? በርግጥም ደክሟቸው መሆን አለበት፡፡

የጽሑፉ ዓላማ

 ማኅበረ ቅዱሳን ከተለያዩ የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ማኅበራትና ልጆች ጋር በመቀናጀት በአሁኑ ሰዓት ፀረ ተሐድሶ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህም ምክንያት ማዕበሉ እያንጓለለ የለያቸው ያሉ የተደራጁ  የሃይማኖት ጠላቶች ማምለጫ እስኪያጡ ድረስ አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል፡፡ የተዋሕዶ ምዕመናንን እየሰለቿቸው መጥተዋል፡፡ በመሸማቀቅ በቁማቸው አልቀዋል፡፡ ከመጠን በላይ በመደንገጣቸው ምክንያት ሳያስቡት የመጣባቸውን እውነት ለመጋፈጥ የሚያስችል መንፈሳዊ ተክለ ሰውነት አጥተዋል፡፡  ስለሆነም አቋራጭ የመሰላቸው የጨነገፈ ስልት ነድፈዋል፡፡ በዋነኛነትም የሞት ሽረት ትግል ለማድረግ አስበዋል፡፡

በዚህም መንገዳቸው አንዱ የማኅበሩን ስም በድብቅ ሆኖ ማጥፋት ነው፡፡ እውነተኞች ሰዎች ከሆኑ ማንነታቸውን ገልጠው ፊት ለፊት በያዙት መረጃ በታገሉ ነበር፡፡ ለዚህ ያልታደሉ የመልካም ዘር ፀሮች በመሆናቸው መደበቁን መርጠዋል፡፡ ተደብቆ ውጭ ማኅበረ ቅዱሳን ሊያስበው ከቶውኑ የማይፈልገውን ያስቡለታል፡ ፡ “አዛኝ ቅቤ አንጓች” እንደሚባለው ሆኖባቸው በዚህ ስልት ማኅበሩን ለማጥቃት ሞክረዋል ራሳቸው ጽፈው ሊሰሙን ይችላሉ ብለው ለሚያስቧቸው አካላት ጽሑፉን ለመበተን ሞክረዋል፤ ይህንን ማድረጋቸውም አንድም አባቶችን ንቀዋቸዋል አለበለዚያም ተዳፍረዋል፡፡

ይህንን ከደረጃ ወጥቶ ጊዜ ወስዶ የተንኮታኮተ ጽሑፍ ዕቅድ ብለው ይዘው መዞራቸው በትክክል ማንነታቸውን ይገልጥባቸዋል፡፡ በየትኛውም መመዘኛ ማኅበረ ቅዱሳንን የማይመስል ወዘና የሌለው ወረቀት ብቅ ማድረግ ማንነታቸውን ገልጠዋል፡፡ በዝምታ ሊታለፉ አይገባቸውም፡፡

ማጠቃለያ
ይህንን ጽሑፍ ያሰራጩት አካለት እነማን ሊሆኑ እንደሚችሉ ማንም ሰው መገመት ይችላል፡፡ ከመገመትም አልፎ አገኘሁ ብሎ ማኅበሩን ለማጥላላት የሚጠቀምበት ሁሉ እንዳለ ይታወቃል፡፡ ተቀባዮችም የሰጪዎችን ማንነት ያውቃሉ፡፡ እንዲያውም ከማብራሪያ ጋር እንደተቀበሉ ይታመናል ፡፡

ስለሆነም፡-

1. ይህ የሐሰት ጽሑፍ የደረሳቸው አካላት ሰዎችን በማጋለጥ ሊተባበሩ ይገባል፤
2. ማኅበሩ እነዚህን አካላት በሕግ መጠየቅ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ የእነዚህን ሰዎች ማንነት አጣርቶ ፍትሐዊ ውሳኔ እንዲሰጥን እንፈልጋለን፤

3. ይህ ጽሑፍ የደረሳቸሁ ምዕመናን በሐሰት ሥራ እንዳትታለሉ እናሳስባለን። አስፈላጊ ሆኖ ካገኙትም ወደ ማኅበሩ ጽ/ቤት በመምጣት ተገቢውን ውይይት ማድረግ እንደሚችሉ እንጠቁማለን።

ሕገ ቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱስ ሲኖዶስና ስለ ቅዱስ ፓትርያርክ ምን ይላል?

ግንቦት 11፣2003ዓ.ም

ቅዱስ ሲኖዶስ በ1991 ዓ.ም ባወጣው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለ ቅዱስ ሲኖዶስና ስለ ቅዱስ ፓትርያርክ የሚናገሩ ምዕራፎች እና አንቀጾችን አቅርበናል፡፡

ምዕራፍ ሁለት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ

አንቀጽ 5
የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና /የበላይነት/

1.    በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ ስለሆነ በቤተ ክርስቲያኒቱ የመጨረሻው ከፍተኛ ሥልጣን ባለቤት ነው፡፡

2.    ከማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን መዋቅር ሁሉ የበላይ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ስለሆነ ሕጐችን፣ ልዩ ልዩ ደንቦችንና መመሪያዎችን የማውጣትና የዳኝነት ሥልጣን አለው፡፡

አንቀጽ 5

የቅዱስ ሲኖዶስ ዓላማ

1.    ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ አገልግሎቱም የተሟላ እንዲሆን ለማድረግ፣

2.    የሃይማኖትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዳይፋለስ ለመጠበቅና ለማስጠበቅ፣

3.    ጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ለመጠበቅና ለማስፋፋት፣

4.    ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋትና ለማጠናከር፣

5.    ወጣቶች ከአበው የተቀበሉትን ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀው በትምህርትና በሥነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉ ሰንበት ትምህርት ቤትን ለማጠናከርና ለማስፋፋት፣

6.    የሰው ዘር ሁሉ ከርሃብ፣ ከእርዛት፣ ከበሽታና ከድንቁርና ተላቆ በሰላምና በአንድነት በመተሳሰብና በመረዳዳት በመንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖር ማስተማርና መጸለይ፣

አንቀጽ 7

የቅዱስ ሲኖዶስ ሥልጣንና ተግባር

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚከተለው ሥልጣንና ተግባር ይኖረዋል፡፡

1.    ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያንን በበላይነት ይመራል፣ ይጠብቃል፡፡

2.    ሕገ ቤተ ክርስቲያን በሚፈቅደው መሠረት ሕጎችን፣ ደንቦችንና ልዩ ልዩ መመሪያዎችን ያወጣል፣ ያሻሽላል፡፡

3.    የቤተ ክርስቲያኒቱን አጠቃላይ የምጣኔ ሀብታና የሙዓለ ንዋይ መመሪያዎችን /ፖሊሲዎችን/ ይወስናል፡፡

4.    ዓመታዊውን በጀት ያጸድቃል ተግባራዊነቱንም ይቆጣጠራል፡፡

5.    የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊ መዋቅር እንዲሁም የጽሕፈት ቤቶችን ደረጃና ተጠሪነት ይወስናል፡፡

6.    የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደርና አገልግሎት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት እንዲመራ ያደርጋል፡፡

7.    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት በአገር ውስጥና በዉጭ አገር እንዲስፋፋ ያደርጋል፡፡ ትምህርት ቤቶችንም ያቋቁማል፡፡

8.    የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ያስተምራል ያስፋፋል፡፡

9.    በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር አዲስ የሀገረ ስብከት ጽ/ቤትና መንበረ ጵጵስና እንደ አስፈላጊነቱ ያቋቁማል፡፡

10.    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከውጭ አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያላትን ግንኙነት ያስፋፋል ያጠናክራል፡፡

11.    በውጭ አገር በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከትና አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት የሚመደቡና እንደዚሁም በአገር ውስጥ የሚሰጠውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ትምህርት ተምረው የውጭውን ትምህርት መማር የሚችሉ ካህናትን እየመረጠ እንዲላኩ ያደርጋል፡፡

12.    ማንኛውም ሰው ቤተ ክርስቲያኒቱን ወክሎ ለሥራም ሆነ ለጉብኝት ወደ ውጭ አገር በሚላክበት ጊዜ ቅዱስ ሲኖዶስ እየፈቀደ ነው፡፡

13.    ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዓተ ጉባኤ እየወሰነ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት እንዲመረጡና እንዲሾሙ ያደረጋል፡፡ እንዲሁም ሊቃነ ጳጳሳትንና ኤጲስ ቆጶሳትን በየሀገረ ስብከቱና በተለያዩ የሥራ ክፍሎች ይመድባል በበቂ ምክንያት ያዘዋውራል፡፡

14.    በቋሚ ሲኖዶደስ የሚያገለግሉ ጳጳሳትን በየሦስት ወሩ እየመደበ እንዲሠሩ ያደርጋል፡፡

15.    በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ሥልጣን ላይ የሚመደቡትን

ሀ. የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለ. የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ

ሐ. የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቱ ም/ሥራ አስኪያጅ

መ. የልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር

ሠ.የውጭ ጉዳይ መምሪያ ሓላፊ

ረ. የልዩ ልዩ ሥራ ዘርፎች ቦርድ አባላት እየመረጡ እንዲሾሙ ያደርጋል፡፡

16.    ቅዱስ ሲኖዶስ በየጊዜው በሚያደርጋቸው ስብሰባዎች የሚቀርቡትን አጀንዳዎች ያጸድቃል እንደአስፈላጊነቱም ያሻሽላል፡፡

17.    ቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፡፡ ለጥፋተኞችና ለበደለኞችም ምሕረትና ይቅርታ የመስጠት ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡

18.    በዚህ ሕግ ባልተካተቱ በማናቸውም በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉደዮች ላይ ሁሉ ቅዱስ ሲኖዶስ የመወሰን ሥልጣን አለው፡፡

አንቀጽ 8

የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት

1.    በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ፓትርያርክ፣ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት ሆነው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከትና በልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች የተሾሙ ሁሉ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ናቸው፡፡

2.    ከፓትርያርኩ ጀምሮ እያንዳንዱ ሊቀ ጳጳስ፣ ጳጳስና ኤጲስ ቆጶስ ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡

3.    የቅዱስ ሲኖዶስ አባልነት ዕድሜ ልክ ይሆናል፡፡

4.    አንድ የቅድስ ሲኖዶስ አባል ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የሚያፋልስ ሆኖ ከተገኘ ከአባልነቱ ይሠረዛል፡፡

5.    ይህም የሚሆነው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ ነው፡፡

6.    በሃይማኖትም ሆነ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተከሰሰ የሲኖዶስ አባል በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ቀርቦ ራሱን የመከላከል መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

7.    አንድ የሲኖዶስ አባል ስለራሱ ጉዳይ በሚታይበት ስብሰባ ላይ በአባልነት መገኘት አይችልም፡፡

አንቀጽ 9

የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ

1.    የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በፓትርያርኩ ሰብሳቢነት ይመራል፡፡ ፓትርያርኩ በልዩ ልዩ ምክንያት ጉባኤውን መምራት ባይችል ከአባላቱ መካከል እሱ የሹመት ቅድምና ያለውን አባት በመወከል ስብሰባው ሊመራ ይችላል፡፡

2.    ከዚህ በታች ከተመዘገቡት በሦስት ምክንያቶች ካልሆነ በቀር ፓትርያርኩ ርዕሰ መንበር ያልሆነበት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ሊካሔድ አይችልም፡፡

ሀ. ፓትርያርኩ በዕርጅናና በጤና ጉድለት ምክንያት ጉባኤውን የሚመራ አባት መወከል ካልቻለ፣

ለ. የቤተ ክርስቲያንን እምነትና ቀኖና በተመለከተ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ እንዲደረግ የሲኖዶሱ አባላት ሲጠይቁት ፈቃደኛ ሳይሆን ከቀረ፣

ሐ. ስብሰባው ፓትርያርኩን የሚመለከት ጉዳይ ከሆነ በፍትሕ መንፈሳዊ መሠረት ይፈጽማል፡፡

3.    ከዚህ በላይ በተዘረዘሩት ምክንያቶች ፓትርያርኩ ጉባኤውን መምራት ካልቻለ በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በተመረጡ የሹመት ቅድምና ባለው አንድ አባት ስብሰባው ሊካሔድ ይችላል፡፡

አንቀጽ 10

የቅዱስ ሲኖዶስ የስብሰባ ሥርዓት

1.    ፍትሕ መንፈሳዊ በአምስተኛው አንቀጽ ቁጥር 164 በሚያዝዘው መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያካሒዳል፡፡ የስብሰባውም ጊዜ፣

ሀ. የመጀመሪያው ጉባኤ በየዓመቱ ጥቅምት 12 ቀን

ለ. የሁለተኛው ጉባኤ ትንሣኤ በዋለ በሃያ አምስተኛው ቀን /በርክበ ካህናት/ የሚካሔደው ነው፡፡

2.    አስቸኳይና ድንገተኛ ጉዳይ ሲያጋጥም፣

ሀ. ቅዱስ ፓትርያርኩ ወይም ቋሚ ሲኖዶስ በሚያደርጉት ጥሪ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ሊካሔድ ይችላል፡፡

ለ. ከጠቅላላው አባላት ከሦስት ሁለት እጁ የሚሆኑ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ምልዓተ ጉባኤ እንዲደረግ በጠየቁ ጊዜም ጥሪ ሊደረግና ስብሰባው ሊካሄድ ይችላል፡፡

3.    የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሚባለው ከዓቅም በላይ የሆነ ዕክል ካላጋጠመ በቀር መላው አባላት የተገኙበት ጉባኤ ሲሆን ነው፡፡

4.    በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በሕመምና በልዩ ልዩ ከዓቅም በላይ በሆነ ምክንያት አንዳንድ አባላት ባይገኙ፣

ሀ. ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በሚመለከት ጉዳይ ከጠቅላላው አባላት ከአራት ሦስት እጅ የተገኙ ከሆነ፣

ለ. አስተዳደርን በሚመለከት ጉዳይ ከጠቅላላው አባላት ከሦስት ሁለት እጅ የተገኙ ከሆነ ነው፡፡

5.    ቅዱስ ሲኖዶስ በማናቸውም ስብሰባ ላይ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ፣

ሀ. አስተዳደርን የሚመለከት ጉዳይ ከሆነ ከተገኙት አባላት መካከል ከግማሽ በላይ በሆነ ድምጽ የተደገፈው ሐሳብ ያልፋል፡፡

ለ. አንድን ጉዳይ ለመወሰን የአባላቱ ድምፅ እኩል በኩል ከሆነ ቅዱስ ፓትርያርኩ ያለበት ያልፋል፡፡

ሐ. ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የሚመለከት ከሆነ በሙሉ ድመፅ ያልፋል፡፡

ምዕራፍ አራት

የኢትዮጵያ ፓትርያርክ

አንቀጽ 13

ስለ ቅዱስ ፓትርያርክ ምርጫ

1.    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ ቀኖና በሚፈቅደው መሠረት ተመርጦ ይሾማል፡፡

2.    ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ፓትርያርክ ምርጫ በሚወስነው ቁጥር መሠረት አስመራጭ ኮሚቴ ይቋቋማል፣

3.    ለፓትርያርክነት የሚመረጡት ዕጩዎች ከሊቃነ ጳጳሳት ከጳጳሳትና ከኤጲስ ቆጶሳት መካከል ሲሆን ብዛታቸው ከሦስት ያላነሡ ከአምስት ያልበለጡ ይሆናል፡፡

4.    አስመራጭ ኮሚቴው እጩዎችን ጠቁሞ ለቅዱስ ሲኖዶስ ያቀርባል፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግና ሥርዓት መሠረት ምርጫው እንዲካሔድ ይደረጋል፡፡

5.    መራጮች የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ፣ የየመምሪያና ድርጅት ሓላፊዎች፣ የጥንታውያን ገዳማት አበምኔቶች የአድባራት አስትዳዳሪዎች ከየሀገረ ስብከቱ ሰበካ ጉባኤያት በዕድሜ ከሠላሳ ዓመት ያላነሱ የካህናትና የምእመናን ተወካዮች እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ22 አስከ 30 ዓመት የሆኑ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ሲሆኑ በጠቅላላው በሰበካ ጉባኤው የሚወከሉት ከአንድ ሀገረ ስብከት አሥራ ሁለት ሆነው በሥጋወደሙ የተወሰኑ በሕገ ቤተ ክርስቲያን የጸኑ መሆን አለባቸው፡፡

6.    የምርጫው አፈጻጸም ቅዱስ ሲኖዶስ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት ይሆናል፡፡

7.    የተመረጠው ፓትርያርክ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትንና ቀኖናዋን ሊጠብቅና አድልዎ በሌለው መልኩ ቤተ ክርስቲያኒቱን ሊያስተዳድር ቃለ መሐላ ይፈጽማል፡፡

8.    ከዚህ በላይ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ስለ ፓትርያርክ ምርጫ ቅዱስ ሲኖዶስ ደንብ ያወጣል፡፡

አንቀጽ 14

የፓትርያርኩ የማዕረግ ስምና መንበር

1.    ፓትርያርኩ ከተሾመበት ቀን ጀምሮ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ እገሌ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ይባላል፣ ስሙም በመላዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጸሎት ይጠራል፡፡

2.    ፓትርያርኩ በአገር ውስጥም ሆነ በውጨ አገር ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን መንፈሳዊ አባት ነው፡፡

3.    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ መንበር በአዲስ አበባ ከተማ በቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ነው፡፡

አንቀጽ 15

የፓትርያርኩ ሥልጣንና ተግባር

1.    ፓትርያርኩ በተሰጠው ኃላፊነት መሠረት ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቃል፣ ያስጠብቃል፡፡

2.    በዚህ ሕግ አንቀጽ 9 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት ፓትርያርኩ የቅዱስ ሲኖዶስን ጉባኤ በሊቀ መንበርነት ይመራል፡፡

3.    ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 እና በዚሁ ሕግ አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ 13 መሠረት ፓትርያርኩ ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋር ሆኖ ኤጲስ ቆጶሳትን ይሾማል፣ እንዲሁም ቅዱስ ሲኖዶስ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት ሲስማማበት ለብፁዓን ጳጳሳት የሊቀ ጵጵስና ማዕረግ ይሰጣል፡፡

4.    በዚህ ሕግ አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ 15 መሠረት የተመረጡትን የሥራ ሓላፊዎች ይሾማል፤ በቀደምትነትና በታሪክ የታወቁትን የታላላቅ ገዳማት አበምኔቶችና የከፍተኛ አድባራት አስተዳዳሪዎች በየሀገረ ስብከቱ ሊቃነ ጳጳሳት እየተመረጡ ሲቀርቡለት የማዕረግ ስም እየሰጠ ይሾማል፡፡

5.    ስለ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የመንግሥትን ፈቃድ ማግኘት በሚያስፈልግበት ጊዜ በቅዱስ ሲኖዶስ እያስወሰነ በተግባር ላይ ያውላል፡፡

6.    ቅዱስ ፓትርያርኩ በዓበይት ጉዳዮች ላይ ሁሉ በቅዱስ ሲኖዶስ አያስወሰነ ይሠራል፡፡

7.    በቅዱስ ሲኖዶስ የወጡ ሕጐች፣ የተላለፉ መመሪያዎችና ውሳኔዎች ሁሉ በተግባር ላይ መዋላቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፡፡

8.    በቅዱስ ሲኖዶስ የሚወጡትን ሕጐችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን በፊርማው ያስተላልፋል፡፡

9.    ከመንግሥታውያንም ሆነ መንግሥታውያን ካለሆኑ መ/ቤቶች ድርጅቶችና ግለሰቦች የሚቀርቡ ደብደቤዎች ወይም አቤቱታዎችን ደረጃቸውን ጠብቀው በሕግ መሠረት ይፈጸሙ ዘንድ ለጠቅላይ ጽ/ቤት ያስተላልፋል፡፡

10.    በውጭ አገር በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከት ለማገልገል ወይም የነፃ ትምህርት ለመማር የሚላኩ ካህናት በዚሁ ሕግ አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ 11 መሠረት ተመርጠው ሲቀርቡ እንዲላኩ ያደርጋል፡፡

11.    ከውጭ የሚመጡትን እንግዶች በውጭ ጉዳይ ኃላፊ አቅራቢነት እየተቀበለ ያነጋግራል፡፡

12.    ፓትርያርኩ በውጭ አገር በሚደረግ በማናቸውም ስብሰባ ላይ ለመገኘትና ጉብኝት ለማካሔድ በሚያስፈልግ ጊዜ ስለተልዕኮው ጉዳይ አስቀድሞ በቅዱስ ሲኖዶስና በቋሚ ሲኖዶስ ያስወስናል፡፡

አንቀጽ 16

የፓትርያርኩ ከማዕረግ መውረድ

1.    ፓትርያርኩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ከተሾመ በኋላ የተቀበለውን ሓላፊነት በመዘንጋት፡-

ሀ. የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትን የሚያፋልስ፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የማይጠብቅ ቤተ ክርስቲያንን የሚያሰነቅፍ ተግባር ፈጽሞ ከተገኘ፣

ለ. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ከቁጥር 172 እስከ 208 በተደነገገው መሠረት በደለኛ መሆኑ ከታመነበት፣

ሐ. በቃሉ የማይገኝና በዚህ ሕግ አንቀጽ 13 ንዑስ አንቀጽ 7 ድንጋጌ መሠረት በተሾመበት ቀን የፈጸመውን ቃለ መሐላ ያልጠበቀ በአጠቃላይ ታማኝነቱና መንፈሳዊ አባትነቱ በካህናትና በምእመናን ዘንድ ተቀባይነትን ያጣ ሆኖ ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚያስነቅፍ መሆኑ በትክክል ከተረጋገጠ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ከሥልጣኑ ይወርዳል፤ በምትኩም ሌላ ፓትርያርክ ተመርጦ ይሾማል፡፡

2.    ከዚህ በላይ በተደነገገው መሠረት ከሥልጣኑ የተገለለ ፓትርያርክ በቀኖና ተወስኖ በገዳም ይቀመጣል፡፡

3.    ከሥልጣን የተገለለው ፓትርያርክ በገዳም አልቀመጥም በቀኖናም አልወሰንም በማለት እምቢተኛ ከሆነ ተወግዞ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ይለያል፡፡

4.    ፓትርያርኩ መንፈሳዊ ሥራውን በማካሔድ ላይ እያለ እሥራትና ግዞት ቢደርስበት ቤተ ክርስቲያኒቱ በቅዱስ ሲኖዶስ ትመራለች እንጂ ሌላ ፓትርያርክ አይሾምም፡፡

5.    ከዚህ በላይ የተዘረዘረው ሁሉ ፍትሕ መንፈሳዊ በሚያዝዘው መሠረት ይፈጸማል፡፡

አንቀጽ 17

ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ

1.    ፓትርያርኩ በሞት ሲለይ ወይም በዚህ ሕግ አንቀጽ 16 መሠረት ከሥልጣኑ ሲወርድ ቅዱስ ሲኖዶስ በሹመት ቀደምትነት ካላቸው ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በዕለቱ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ መርጦ ይሾማል፡፡ የተተኪው ፓትርያርክ ምርጫም ይካሔዳል፡፡

2.    የተተኪው ፓትርያርክ ምርጫ አፈጻጸም እንደጊዜውና እንደሥራው ሁኔታ እየታየ ከ40 እስከ 80 ቀን ባለው ጊዜ ይሆናል፡፡

3.    የዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ተግባር

ሀ. ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ጊዜያዊ ጉደዮችን ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር እየመከረ ያከናውናል፡፡

ለ. በፓትርያርኩ ምርጫ ጊዜም የቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀ መንበር ሆኖ ምርጫውን ያስፈጽማል፤ እርሱ ግን ከምርጫው አይገባም፡፡

/ምንጭ፦ ሕገ ቤተ ክርስቲያን 1991 ዓ.ም/

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ተጀመረ፡፡

ግንቦት 10፣ 2003ዓ.ም


በርክበ ካህናት የሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ተጀመረ። ጉባኤውን ተከትሎ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው፡፡

 
ወደ 1000 የሚጠጉ የሐዋሳ ከተማ ምዕመናን አዲስ የተመደቡትን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ጌታቸው ዶኒን ሹመት በመቃወም በሀገረ ስብከታቸው የተፈጠሩ ችግሮች የመጨረሻ እልባት እንዲሰጥበት የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅድሳን ማረያም ገዳም በመገኘት አቤቱታቸውን አቅርበዋል፡፡  ከቅዱስ ሲኖዶስ መክፈቻ ጸሎት በኋላ ለቅዱስነታቸው እና ለብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥያቄያቸውን ያቀረቡት ምዕመናኑ «በምልዐተ ጉባኤው አጀንዳ ተደርጎ ሊያዝ እንደሚችል ቃል ተገብቶልናል» ሲሉ በቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰበው ምእመን በተወካያቸው አማካይነት ገልጸዋል፡፡

ከሓዋሳ የመጡ ምእመናን አስፈላጊውን የሕግ አግባብነት ተከትለው ቢመጡም ባልታወቀ ምክንያት ዱከም ላይ ታግተው የቀሩ ምእመናን እንዳሉ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡

በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳንም የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በአጀንዳ ሊያያቸው ይገባል ያላቸውን ጉዳዮች በቀን 9/9/03 ዓ.ም በቁጥር ማ.ቅ.ሥ.እ.መ/17/02/ለ/03 በጻፈው ደብዳቤ አቅርቧል፡፡ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት እና በግለባጭ ለሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት በላከው ደብዳቤ በማኅበሩ ላለፉት 19 ዓመታት የተሠሩ ሥራዎች እንዳሉ ሆነው በአሁኑ ወቅት ግን ለቤተ ክርሰቲያን እድገትና መልካም አሠራር እንቅፋት የሆኑ ችግሮች  መኖራቸውን በአጽንኦት ይገልጻል፡፡

ወቅታዊውን የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ከዚህ በፊት ያሣለፋቸውን ውሳኔዎች ተፈጻሚነትን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትውልድን የማፍራት ጉዳይ ይኸውም የሕፃናትና የወጣቶች ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትና የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎችን ችላ ባይነት፣ የማኅበሩን ስም ለማጥፋት እየተንቀሳቀሱ ስላሉ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ለቅዱስ ሲኖዶስ አባልነትና የሚቀርቡና የሚሾሙ ኤጲስ ቆጶሳትን ጉዳይ ይኸውም ወቅቱ የተሐድሶ መናፍቃን በቤተ ክርስቲያኗ መዋቅርና የሓላፊነት ቦታ ለመግባት ከፍተኛ ርብርብ የሚያደርጉበት ስለሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ለዚህ ጉዳይ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የሚያመለክቱ አጀንዳዎች በአጀንዳነት ተይዘው ውሳኔ ሊሰጥባቸው ይገባል በማለት እንደልጅነታችን ሀሳባችንን እናቀርባለን ሲል ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተጻፈው ደብዳቤ ያሳስባል።


 


በተያያዘም እነዚህንና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር የቀረቡ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ በወቅታዊው የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ሠፋ ያሉ ዘገባዎች ቀርበዋል።

ቅዱስ ሲኖዶስንና መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ልዕልናውን፣ የወቅታዊውን የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ፣ እንዲሁም አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፣ በማኅበረ ቅዱሳን የውሸት /forged/ ማኅተም «የማኅበረ ቅዱሳን የረጅም ጊዜ ዕቅድ» በሚል ያዘጋጁትን እና በክስ መልክ ለፓትርያኩ ያቀረቡትን የሐሰት ጦማርና ሌሎችንም ወቅታዊ ጉዳዮች በተመለከተ ሰፋ ያለ ዘገባ በመያዝ ወጥታለች፤ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም።

ቤተ ክርስቲያን የማትነጥፍ መንፈሳዊት ጥገት ሆና ከምታፈሰው መንፈሳዊ ሐሊብ /ወተት/ ምእመኖቿ እንዲጠቀሙ የቅዱስ ሲኖዶስ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ልዕልና መከበር ወሳኝ ነው።

ቤተ ክርስቲያንም የቅድስና ዘውዷንና የክብር አክሊሏን ከራሷ ሳታወርድ ልዕልናዋ እንዳለ ሁሉ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች መከበር አለባቸው ስትል ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በልዩ እትሟ አስነብባለች።


የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም

ቅዱስ ሲኖዶስ ጠንካራ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል

ግንቦት 10/2003 ዓ.ም.

በቤተክርስቲያኒቱ አጠቃላይ ሁኔታ ላይ የሚመክረው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቀጣይ በቤተክርስቲያኒቱ አገልግሎት መጠናከርና በገጠሟት ችግሮች ላይ መፍትሔን የሚሰጥ ጠንካራ ውሳኔ ያሳልፋል ብሎ እንደሚያምን ማኅበረ ቅዱሳን አስታወቀ፡፡ የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እንዳስታወቁት፤ ዘንድሮ ከግንቦት 10 ቀን ጀምሮ የሚካሔደው ዓመታዊ መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በእግዚአብሔር አጋዥነት እና በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ በመሆኑ ጠቃሚ ሀሳቦች የሚነሡበት፤ ለቅድስትቤተክርስቲያን የሚበጁ ጠንካራ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሚሆን ማኅበረ ቅዱሳን በፅኑ ያምናል፡፡
 
«በቅድስት ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ያለው ቦታና ልዕልና ከፍተኛ ነው፤ ስለዚህም የቤተክርስቲያኒቱን ዶግማና ቀኖና ከማስጠበቅ፣ በየጊዜው የሚያጋጥሟትን ችግሮችና ፈተናዎች ላይየማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም ውሳኔዎችን ከማሳለፍ አንፃር የጉባኤው ውጤት በጉጉት ይጠበቃል» ያሉት ሰብሳቢው፤ ይህ ይሆን ዘንድ ማኅበሩ ምኞቱን ይገልጣል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የቤተክርስቲያኒቱን ሥርዓት፣ዶግማ እና ቀኖናዋን እንዲሁም ማንነቷን የሚሸረሽር ትልቅ የተሐድሶ እንቅስቃሴ መኖሩን የጠቆሙት ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ፤ በዚህ ላይ የሲኖዶሱ ውሳኔ ወቅታዊነት ያለው ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
በፀረ ቤተክርስቲያን ኃይሎች መንፈሳዊ ተቋማትና ገዳማትን የመበረዝ፣ ውስጧንም የመቀየርና ማንነቷን የማጥፋት ሰፊ ሥራ እየሠሩ መሆኑን ጠቅሰው በእነዚህና በመሳሰሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ እንቅፋቶች ላይ ጉባኤው መክሮ የሚያሳልፈው ውሳኔ ጠቃሚ እና ተስፋ ሰጪ  እንደሚሆንም እምነታቸውን ገልጠዋል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎ ለማስፈፀሚያነት የሚወጡ መመሪያዎችንና ደንቦችን በአግባቡ የመከታተልና የመቆጣር ሓላፊነትም የቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን ጠቅሰው፤ አፈጻጸሙ ላይ ማኅበሩ የቤተክርስቲያኒቱ አካል እንደመሆኑ መጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል፡፡

እንደ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም ገለጻ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ውሳኔዎችን እንደ ቅድስት ቤተክርስቲያን አካልነቱ ከመፈጸም እና ከማስፈጸም በተጨማሪ ማኅበሩ ባለው የኅትመት ውጤቶች ማለትም በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ፣ በሐመር መጽሔት እና በሌሎች የኤሌክትሮኒክ ሚዲያ ለምእመናን የማድረስ ሓላፊነቱን ይወጣል፡፡ ማኅበሩ በቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያና ደንብ መሠረት የተዋቀረ በመሆኑ ለቤተክርስቲያኒቱ ያለውን አጋዥነት አሁንም በተግባር ማረጋገጡን እንደሚቀጥል የጠቀሱት ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ በአባቶች ምክር፣ ምርቃትና ቡራኬ የሚመራ መሆኑ አገልግሎቱን እንዳገዘው ተናግረዋል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎችን የማኅበሩ አባላትም ሆኑ ምእመናን አክብረው ተግባራዊ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

«እርሳቸው የያዙት መንገድ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከም ነው፡፡ » ማኅበረ ቅዱሳን

 ግንቦት 9/2003ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ተመሥርቶ በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር አገልግሎት ከጀመረ አንስቶ ወደ 10 የሚጠጉ የመምሪያ ኃላፊዎች ተፈራርቅዋል፡፡ እስከ አሁን ምንም ያልተባለለት የማኅበሩና ማደራጃ መምሪያው ግንኙነት፣ የአሁኑ የመምሪያው ኃላፊ አባ ሠረቀብርሃን ከመጡ ከ6 ዓመት በፊት ጀምሮ፣ ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ ይነገራል፡፡ ማኅበሩም አሁን ያሉት የመምሪያው ኃላፊ አላሠራኝ አሉ በማለት ይወቅሳል፡፡ ይህንን በተመለከተ ከማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡
 
    ቅዱስ ሲኖዶስ ባጸደቀውና በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የማኅበረ ቅዱሳን ግንኙነት ምን መምሰል አለበት?

የማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ በ1994 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በጸደቀው መሠረት ማኅበሩና ማደራጃ መምሪያው የሚያከናውኗቸው ተግባራት በግልጽ ተቀምጠዋል፡፡ የማኅበሩ ተግባርና ኃላፊነት፥ ማኅበሩ ለማደራጃ መምሪያው ማድረግ የሚገባው ነገር፥ ምን መሥራት እንዳለበት በግልጽ ተቀምጠዋል። በተለይ ማኅበሩ የበላይ ተጠሪው ማደራጃ መምሪያው እንደመሆኑ የሚሠራቸውን ዕቅዶች የማሳወቅ፣ ዕቅዶችንም ካሳወቀና በጠቅላላ ጉባኤው ላይ እንዲገኘ አድርጎ አስተያየት እንዲሰጥ ካደረገ በኋላ አስተካክሎ ያንን ማቅረብና ወደ ሥራ መግባት፥ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በየ6 ወሩ የአፈጻጸም ሪፓርት ማቅረብ የሚሉ ነገሮች ናቸው የተካተቱት፥ ይህ እንግዲህ የመጀመሪያውና ትልቁ ነገር ነው፡፡

ከዚያ ሪፖርት ተነሥቶ ማደራጃ መምሪያው በሚሰጠው ግብረ መልስ /Feed back/ እና መመሪያ መሠረት እየተነጋገረ ወደ ማስተካከያ ተግባሩ ይሄዳል ማለት ነው፡፡
 
የአንድ ተቋም ተጠሪነት ሲባልም ከዚያ ያለፈ አይደለም፡፡ ሙሉ በሙሉ እቅድ ላይ የሚሳተፍ፥ የተሠራውን ሥራም የማቅረብ ነው፡፡

ከዚያም ውጭ በአብዛኛው የማደራጃ መምሪያው በማኅበሩ አገልግሎት ላይ ድጋፍ የማድረግ ነገር ነው ያሉት፥ ለምሳሌ ማኅበሩ ከጠቅላይ ቤተ ክህነትና ከሌሎች ሦስተኛ አካላት ጋር የሚያደርገው ግንኙነት ችግር ቢገጥመው በማደራጃ መምሪያው ከዚያም አልፎ በጠቅ/ቤ/ክ አማካኝነት እነዚያ ግንኙነቶች እንዲስተካከሉና እንዲሰምሩ ይደረጋል፡፡

ማኅበሩ የባንክ አካውንት ሲከፍት በራሱ ስም ነው። የማኅበሩ ሕጋዊ ሰውነት ደግሞ በቤተ ክርስቲያኑ ነው፡፡ ይሄን አካውንት ደግሞ ቀጥታ ወደ ባንክ ቤት በመሄድ ራሱ አይከፍትም ። ማደራጃ መምሪያው ቢጽፍለትም እንኳን አይከፍትም፡፡ ስለዚህ ማኅበሩ ለማደራጃ መምሪያው ደብዳቤ ይጽፋል፡፡ እነዚህ… እነዚህ አካውንቶች ይከፈቱልኝ በማለትም ይጠይቃል፡፡ ከዚያም ማደራጃ መምሪያው ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ይጽፋል፡፡ በዚያ መሠረት ይከናወናል፡፡ እንደገናም ማኅበሩ ከመንግሥት አካላት ሆነ መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማትም ግንኙነት ፈልጎ ችግር ቢገጥመው ወይም ሕጋዊ ሰውነቱ ላይ ጥያቄ ቢኖራቸው፣ ይሄ የሚፈታው በቤተ ክርስቲያን በኩል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ይሄን ለማሳለጥ የመደበችው ማደራጃ መምሪያው ነው፡፡

ስለዚህ በሚሠሩት ሥራዎች በሙሉ እየተገኘ መመሪያዎችን የመስጠት፣ የማሳለጥ /facilitation/ ሥራዎችን የመሥራት፣ ሀገረ ስብከቶችና ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስፈላጊው ትብብር እንዲያደርግ ኃላፊነት የተሰጠው ለማደራጃ መምሪያው ነው፡፡

በዚህ ዓይነት ግንኙነት ማደራጃ መምሪያው ለማኅበሩ የሚሠራው አለ፡፡ ማኅበሩ ለማደራጃ መምሪያው የአገልግሎት ማኅበር ስለሆነ ሪፖርት ነው የሚያቀርብለት፡፡ ሌላ ምንም ሊያደርግለት አይችልም፡፡

ስለሆነም ግንኙነታቸው እንዲህ በግልጽ የተቀመጠ ነው። በማንኛውም ተቋም የበላይና የበታች እንዴት እንደሚሠራ እንደተቀመጠው የተቀመጠ ነው፡፡

•    በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 9 ቁጥር 1 መሠረት ማደራጃ መምሪያው ማኅበረ ቅዱሳን የሚያበረክተውን አገልግሎት በቅርብ ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ ተገቢውን መመሪያ ይሰጣል ይላል። ይህን እንዴት ነው ማኅበሩ የሚተረጉመው?

ማኅበሩ በዕቅድ የሚመራ ማኅበር ነው፡፡ ዕቅድ አለው በዚያ መሠረት ሥራውን ይሠራል፡፡ ማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ሲያደርግ የማደራጃ መምሪያው ኃላፊ በተገኙበት እያንዳንዱ አንቀጽ፥ እያንዳንዱ በጀት እያንዳንዱ ዕቅድ እያንዳንዱ አካሄድ ይታያል፤ ይገመገማል፡፡ የመጨረሻውን ዕቅዱን ዶክመንት ለማጽደቅ እንኳን ሦስት ቀን ይፈጃል፡፡ በዚያን ጊዜ ተገኝተው በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ መመሪያ ይሰጣሉ ማለት ነው፡፡ በነገራችን ላይ ከአባ ሠረቀ በፊት የነበሩ መምሪያ ኃላፊዎች በሙሉ በጠቅላላ ጉባኤ እየተገኙ መመሪያ ይሰጡ ነበር፤ ይከታተሉ ነበር፤ ምን እንደተወሰነ ያውቃሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ በተወሰነው መሠረት የ6 ወር ሪፖርት ሲቀርብላቸው ይሄ ለምን ተሠራ? ይሄ ለምን አልተሠራም? ይሄ ለምን ቀረ? ብለው ያያሉ በማኅበሩ ጽህፈት ቤት እየተገኙ የማኅበሩን የጽህፈት ቤት አሠራር ይጎበኛሉ፤ ይመለከታሉ። እርሳቸው ግን በ6 ዓመት ውስጥ ጽህፈት ቤቱን እንኳን አይተውት አያውቁም፡፡ እንዲመጡ ቢጋበዙም እኔ አውቃለሁ በማለት ነው እዛው ቁጭ የሚሉት፡፡ ይሄንን የመምሪያው ምክትል ኃላፊም የማኅበሩን ጽህፈት ቤት ጎብኝቶ ምንድን ነው የሚሠራው? እንዴት ነው የሚሠራው? ምን አገልግሎት ነው ያለው? ምን ድካም ነው ያለው? የሚሉትን ነገሮች አይቶ አያውቅም፡፡ እነዚህን ሰዎች በግድ ጎትቶ ማምጣት አይቻልም፡፡ ይሄ የእነርሱ ኃላፊነት ነው። በቅርብ ለመገኘት ይከታተላል ይቆጣጠራል ማለት በዕቅዱ በሪፓርቱ ብቻም አይደለም፡፡ በአካልም የመስክ ጉብኝቶችን በማድረግ እየተገኘ ማስተማር መመሪያ መስጠት የእነርሱ ኃላፊነት ነው። ይሄንን ከዚያ በፊት የመምሪያ ኃላፊ የነበሩት እነ ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባ ብቻ አይደለም፤ ከማዕከላት ጋር ይወያዩ ነበር፡፡ በግቢ ጉባኤያት ተገኝተው ያስተምሩ፣ ይመክሩ፣ በርቱ ይሉ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ግን የት ቦታ ማኅበረ ቅዱሳን እንዳለ፥ ምን እንደሚሠራ አያውቁም፡፡ 

አሁንም ለቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ የምናቀርበው ጥያቄ ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ ሰዎች ስለሆኑ ውሳኔ ይሰጥልን ይሆናል፡፡ ይሄንን ጥያቄ አሁንም ከ 6 ዓመት በኋላ በድጋሜ እናቀርባለን፡፡ የማደናቀፍ ሥራ ብቻ ነው እየሠሩ ያሉት እንጂ አልተቆጣጠሩም፣ አልመሩም አልተከታተሉምና ሊመራ የሚችል አካል ለእኛ ብቻ አይደለም፥ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ለመላው ሰንበት ትምህርት ቤት ያስፈልጋል፤ የሚል ጥያቄ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ ነው፡፡

•    ማኅበረ ቅዱሳን አሁን ያሉት የመምሪያው ኃላፊ አላሠራኝ አሉ በማለት ይወቅሳል።  እንዴት ነው አላሠራ ያሉት? ከዚያ በፊት ከነበሩት የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎች ጋር የነበረው ግንኙነት ምን ይመሥል ነበር?

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ካሉት መምሪያዎች አንዱ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ነው። በ1956ዎቹና 1960ዎቹ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ሲቋቁምና ሲዋቀር፥ በተለይ በ1960ዎቹ ወደ ተግባር ሲመጣ፥ የተሰጠው ኃላፊነት ሕፃናትንና ወጣቶችን እንዲያስተምር ነው፡፡ በዚህ የማስተባበርና የማደራጀት ሥራ እንዲሠራም ነው፡፡ በእያንዳንዱ አጥቢያ ላይ ሰንበት ትምህርት ቤትና የወጣቶች ክፍል እንዲኖር የማስቻል ሥራ ነው የሚሠራው፡፡ በዚህ መሠረት ሲሠራ ቆይቶ፣ ከዩኒቨርሲቲ የተመረቁ በዩኒቨርሲቲ የተማሩ ወጣቶችን ይዞ ሲመጣ፥ የት ቦታ ነው መግባት ያለበት የሚለውን በማሰብ፥ ማኅበሩ ራሱ ነው በማደራጃ መምሪያው ስር ብደራጅና ቁጥጥር ቢደረግብኝ ይሻላል በማለት የሄደው፡፡ ስለዚህ በወቅቱ የነበሩትን የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎች ማኅበሩ አነጋገረ፣ እነርሱም ፈቃደኞች ሆኑ። በዚህ ምክንያት ማኅበረ ቅዱሳን በሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ እውቅና ተሰጥቶት ግንቦት 2 ቀን በ1984 ዓ.ም ይፋ ሆነ። ስለዚህ ተጠሪው /አለቃው/ ማደራጃ መምሪያው ሆነ ማለት ነው፡፡ በጊዜው የነበሩት ኃላፊዎች አንድ ዓመትም አልሠሩ ከኃላፊነት ተነሱ፡፡ ቀጥለው ከነበሩት ኃላፊዎች ጋር በመግባባት መንፈስ ሥራዎችን ቀጠለ፡፡ እንዲህ እያለ ማኅበረ ቅዱሳን እስከ 1998 ዓ.ም ወደ 10 የሚሆኑ የመምሪያ ኃላፊዎች ሲፈራረቁ ቆይተዋል፡፡ ከሁሉም የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎች ጋር በመግባባት በትብብር ነው የሠራው። ስህተቶች ሲኖሩ የሚያርሙ መመሪያዎች ሲያስፈልጉ መመሪያ የሚሰጡ፣ የሥራ ትብብሮች ሲኖሩ የሚተባበሩ ለአገልግሎት ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ በመሯሯጥ የሚሠሩና የምናስታውሳቸው የመምሪያ ኃላፊዎች ተሹመዋል፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን በምንኩስናው የነበሩት ብዙዎቹ ወደ ጵጵስና ማዕረግ ደርሰዋል፡፡ ከእነዚህ ሁሉ ማኅበሩ እንደ አባትና ልጅ እንደ አለቃና ታዛዥ በመሆን ነው ሲሠራ የነበረው፡፡

አባ ሠረቀ ብርሃን የዛሬ 6 ዓመት ነው ወደ ማደራጃ መምሪያ በኃላፊነት የመጡት፡፡ ወደ ቦታው ከመጡበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ፤ እኔ የማኅበረ ቅዱሳንን ሰነዶች አይቻለሁ እስከ ዛሬ የሚሠራው ሥራ ልክ አይደለም፡፡ ኃላፊዎችም ልክ አልሠሩም በማለት ነው የጀመሩት፡፡ የመጀመሪያው አስተያየታቸውም እስከ አሁን የነበሩት የመምሪያ ኃላፊዎች ማኅበረ ቅዱሳንን በትክክል አልመሩትም፡፡ ኃላፊነታቸውንም አልተወጡም ከእንግዲህ በኋላ እኔ ነኝ የምወጣው ብለው ነው የጀመሩት፡፡

በዚህም የተነሣ ልክ እንደተቀመጡ የማኅበሩን አባላት ዝርዝር መረጃ ላኩልኝ ነበር ያሉት። ማኅበረ ቅዱሳን ከ120,000 በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎችን አስተምሮ አስመርቋል። ሁሉን አባል አድርጎ ባይዝና ባይመዘግብም፥ ብዙዎች እንኳ ሳይመዘገቡ እኛ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ነን የሚሉ እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ በሙሉ ስም ዝርዝራቸውን በHard copy /በጽሑፍ ተባዝቶ/ እንዲሄድላቸው ነው የአባ የመጀመሪያ ጥያቄ፡፡ እንግዲህ ማኅበሩ ከአገር ውጭ፣ ከውስጥም እስከ ገጠር ያሉትን አባላት ዝርዝር እንዲያመጣ ነው የተፈለገው፡፡

አሁን ጥያቄው፥ ምንድን ነው ጥቅሙ? እንዲህ ዓይነት መመሪያስ አለ ወይ? የሚለው ነው። ይሄ አላስፈላጊ ነው፤ ባይሆን የአመራሩን ዝርዝር እንላክ፤ የሚል ሐሳብ ስናነሣ ይሄ በፍጹም አይሆንም፤ ዝርዝራቸውን ካላገኘን አሉ። በተጨማሪም ሌሎችን በፍጹም ከኃላፊነት ጋር ያልተገናኙ ጥቃቅንና ከቁጥጥር ጋር ያልተገናኙ ጥያቄዎችን ያቀርባሉ፡፡ እኛም እንደዚህ አይደለም በማለት እንመልሳለን፡፡ በተቀመጡ 6 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ወደ 5 ደብዳቤ ነው ለማኅበረ ቅዱሳን አከታትለው የጻፉት። ስለዚህ ግንኙነታችን በጣም የማይሆን የደብዳቤ ልውውጥ ሆኖ ሲገኝ፥ አንድ ዓመት እንኳ ሳይሠሩ ወደ ቅዱስ አባታችን አቤቱታ አቀረብን። በአካልም በመገኘት «በመምሪያ ኃላፊነት የተመደቡት አባት ተባብሮ ከማሠራት ይልቅ ሥራ እያደናቀፉ ነው ያሉት፥ ለእኛ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚገኙትን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለማደራጀት ብቃት የላቸውም፥ ስለዚህ ከኃላፊነት ተነስተው ሌላ ሰው ይመደብልን ቅዱስነትዎ የሚያምኑበትን ሲያሠራና ሊሠራ የሚችል ሰው ይመድቡልን» ብለን ጥያቄአችንን አቀረብን፡፡ ቅዱስነታቸው “እናንተ ብዙ ሰዎችን ማሳመን የምትችሉ፣ አንድ ደካማ መነኩሴ ይነሣ ብላችሁ ጥያቄ ማቅረብ የለባችሁም ይሄ ከእናንተ ደረጃ በታች ነው፡፡ ስለዚህ አሳምኑ” የሚል ሐሳብ ነው የሰጡን። በዚህ ጊዜ «በቅዱስ አባታችን በተቀመጡ በ6 ወራቸው 5 ደብዳቤ ጽፈዋል፡፡ ስለዚህ ደብዳቤ መጻፍ ነው ሥራቸው የምንሰጣቸውንም መልሶች እየሰሙና በአግባቡ እየመሩን አይደለም፡፡” የሚል ጥያቄ አቅርበናል፡፡ አሁን ላይ ሆነን ስናየው የዛሬ 6 ዓመት ይሄን ጥያቄ ማቅረባችን ትክክል ነበር፡፡ በወቅቱ ገና አጀማመራቸው ማኅበረ ቅዱሳንን የመቆጣጠር ሳይሆን የማቆም ዕቅድ ነው ያላቸው ይሄን ደግሞ በይፋ እየሠሩት እንደነበር አይተናል፡፡

እንግዲህ ከዚያ በኋላ ኃላፊው ማንኛውም ጥናትና ማኅበረ ቅዱሳንን የሚመለከት ነገር ወደ ቅዱስነታቸው ሲያቀርቡ፥ ለማኅበረ ቅዱሳን ግልባጭ አያደርጉም፤ በስውር ነው የሚጽፉት፡፡ ከ25 ገጽ ያላነሰ ጥናት የሚባል ነገር ከሌሎች የተሐድሶ ቡድንና የሃይማኖት አበው አባላት ጋር በመሆን ጥናት የሚመስል ነገር አቅርበዋል፡፡ ባቀረቡት ጥናት ላይም ማኅበረ ቅዱሳን የሚለው ክፍል አያስፈልግም፡፡ ወጣቶች በሙሉ በአንድ ተጠቃለው መመራት አለባቸው፡፡ ሐመርና ስምዐ ጽድቅንም እኛ እናዘጋጃለን፤ እኛ እንረከበው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪና የሰንበት ተማሪ ብሎ መከፋፈል አያስፈልግም። በአንድነት ወጣቶችን ሰብስበን ልናስተምር እንችላለን፡፡ ለዚህ የሚያሰፈልጉ ወደ 300 የሚጠጉ የነገረ መለኮት /theology/ ምሩቃንን ከነበጀቱ ይመደቡልን፡፡ ጠቅላላ እኛ እናስተምራለን፡፡ የሚል ጥያቄ የዛሬ 4 ዓመት ነው ያቀረቡት፡፡ ያ ጥናት በወቅቱ ባለመመለሱ ተከታታይ ደብዳቤ ለቅዱስነታቸው ጽፈዋል፡፡ እነዚያ ደብዳቤዎችም፥ ተስፋ ቆርጫለሁኝ ስለዚህ ወደ ትምህርት መመለስ አለብኝ፡፡ እሠራለሁ ብዬ ነበር የመጣሁት፥ ስለዚህ ተግባራዊ እየሆነልኝ አይደለም ያለው የሚል አቤቱታ ያዘለ ደብዳቤ ሲያቀርቡ ቆይተው በአሁኑ ወቅት ያለን ግንኙነት ከተሐድሶ ማንሠራራት ጋር ተያይዞ የቤተክርስቲያኒቷን አደረጃጀት በውስጥም በውጭም እየያዙ ሲመጡ አሁን በትብብር የሚሠራበትና አንድ ላይ ሆነው የሚያጠቁበት ደረጃ ላይ ነው የደረሱት። በዚህ ምክንያት ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ተደጋጋሚ የሆኑ ደብዳቤዎችን የመጻፍ፣ የማይሆኑ ትዕዛዞችን የማዘዝ፣ ተፈጻሚ ሊሆኑ የማይችሉ መመሪያዎችን የማስተላለፍ፣ ሥራ የማገዝና ተፈጻሚ እንዲሆኑ የማቀላጠፍ ሳይሆን የማደናቀፍ የማቆም፣ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል እንዳይካሄዱ እንቅፋት የመፍጠር፣ ወጣቶች እንዲማሩ ሳይሆን እንዲበተኑ የማድረግ ሥራዎች ነው እየተሠሩ ያሉት በዚህ በጣም እናዝናለን፡፡

የእኛን ሥራ የመደገፍ ይቅርና የተመደቡበትን ሰንበት ትምህርት ቤቶችን እንኳ ዘወር ብሎ ለማየትና አንዱም ቦታ ላይ የማስተማሪያ መጻሕፍትም ይሁን መምህራን ተመድበው የሌለበት ቦታ ነው። አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ ትውልዱን የሚመራው ክፍል እንደዚህ ሆኖ ይገኛል፡፡ እንግዲህ ያለን ግንኙነት ይሄንን ይመስላል፡፡
•    የማደራጃ መምሪያው ኃላፊ ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየተፈጠረ እንደሆነ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ እውነት ሥጋት ነው? እርሳቸው እንዲህ የገለጹት በምን ምክንያት ይመስልዎታል፡፡

ለአባ ሠረቀ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ አደጋ አለው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቷን እየተካት ነው። የማኅበረ ቅዱሳን አወቃቀርና አደረጃጀት አጠቃላይ ቤተ ክርስቲያኒቷን መዋቅር የተመለከተ ነው፡፡ ይኸውም ማለት እንግዲህ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን መዋቅር ነው እንዲህ እያሉ ያሉት። ቅድም እንደገለጽኩት 25 ገጽ ጥናት ለቅዱስ ፓትርያርኩ ሲያቀርቡ፣ በጥናቱ ውስጥ ለማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠው መተዳደሪያ ደንብ በቂ አይደለም፥ ቅዱስ ሲኖዶስ ተሳስቷል ነው የሚለው፡፡ እንዲህ ዓይነት መተዳደሪያ ደንብ ለማኅበረ ቅዱሳን መሰጠት አልነበረበትም፤ ስለዚህ ስህተት ተፈጽሟል፤ ይሄ ስህተት መታረም አለበት፡፡ ለመታረም ደግሞ ደንቡ ይሻሻል ሳይሆን ጭራሽ መቆም አለበት የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ሲኖዶስን ነው የሚወቅሰው። እንዲያውም መተዳደሪያ ደንቡ ማደራጃ መምሪያውን ለማኅበረ ቅዱሳን ሎሌ አድርጎታል፥ ጭራሽ ጉዳይ አስፈጻሚ አድርጎታል እንጂ አለቃነቱን የሚያሳይ አይደለም በሚል ነው የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ እየተቃወሙ ያሉት፡፡

ይሄን እንዳለ ትተነው ለቤተ ክርስቲያኒቱ አደጋ ነው በማለት የሚያስቀምጡት የራሳቸውን ሥጋትና አስተሳሰብ ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አጋዥ ነው፡፡ ክፍተቷን የሚሞላ የሚደግፍ ነው፡፡ ምዕመናን እንዳይበተኑ በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች እንዳይበተኑ እያደረገ ነው፡፡ ይሄንን አባ ሠረቀ ብርሃን አዛብቶ በማቅረብ ቤተ ክርስቲያኒቷን እየተካ ነው፡፡ የሚል የራሳቸውን የሥጋት ስሜት ሌሎቹም ላይ ለመጫን ነው፡፡

እንደማነጻጸሪያ የሚያቀርቡት የማኅበረ ቅዱሳንን አወቃቀርና የቤተ ክርስቲያኒቷን አወቃቀር ነው፡፡ እርሳቸው በራሳቸው የተሳሳተ መንገድ ነው እያቀረቡት ያለው፡፡ ለምሳሌ የማኅበረ ቅዱሳን ጠቅላላ ጉባኤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር እኩል ነው፤ የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ የቋሚ ሲኖዶስ ጉባኤ አቻ ነው፤ የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈጻሚ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንደማለት ነው በማለት ራሳቸው ፈጥረው ነው ያቀረቡት፡፡ እኛ ጋር የሌሉ ክፍሎችን ሁሉ እያነጻጸሩ ነው ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቷ አደጋ ነው፤ እየተካትም ነው፡፡ እያለ የሚል አስተሳሰብ የሚያንጸባርቁት፡፡ ስለዚህ ይሄ አስተሳሰብ ሙሉ በሙሉ የአባ ሠረቀ ነው፡፡

አባ ሠረቀ ይሄንን ስጋት ከየት አመጡት? ከተባለ ከዓላማቸው አኳያ ነው፡፡ በፍጹም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማሳደግና ወጣቶችን የመሰብሰብ የማስተማር ፍላጎት የላቸውም። ቤተ ክርስቲያኒቷ እንድትጠናከር እየሠሩ ነው ማለትም አይቻልም፡፡ ተግባሮቻቸውም የሚያሳዩት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወጣቶች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዳይማሩ የሚሰጠውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ማስቆም ነው፡፡ ይሄ በምንም ዓይነት ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ማስፈጸም ነው ተብሎ አይታመንም፡፡ ማኅበረ ቅዱሳንም በዚህ አያምንም፡፡ እርሳቸው የያዙት መንገድ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከም ነው፡፡ ትውልድ የማሳጣት ሥራዎችን የመሥራት ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የሌሎች ተልዕኮ ነው። ስለሆነም ሌላ የተጫኑት ተልዕኮ አለ ብለን ነው የምናምነው፡፡ ከሌሎች የተጫኑት ቤተ ክህነቱን የማዳከም ተልዕኮ አላቸው። የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ ቤተ ክርስቲያኒቷን የሚያጠናክር ከሆነ፥ ማኅበረ ቅዱሳንን ማቆም ቤተ ክርስቲያኒቷ እንዳትጠናከር አንድ እርምጃ ብለው ስለሚያስቡ በተቻላቸው መጠን ስም በማጥፋት ለቤተ ክርስቲያኒቷ ስጋት ነው በማለት ማቅረብና የሁሉንም ትኩረት እንዳያገኝ የማድረግ ሥራ ነው የሚሠሩት። በዚህ ተግባር ላይ ተሠማርተው ነው ያሉት በአሁኑ ወቅት፡፡
•    ሌላው የሚነሳው ጉዳይ፣ መስከረም 12 ቀን 2002 ዓ.ም ከመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከሊቃነ ጳጳሳትና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር በተደረገው ስብሰባ ላይ ማኅበረ ቅዱሳንን በመክሰስ ሂደት ላይ እርሳቸው አንድ ተሳታፊ እንደነበሩ ይነገራል፡፡ በወቅቱ ሁኔታው እንዴት ነበር? የእሳቸው ሚናስ ምንድን ነበር?

በእርግጥ በአጋጣሚ አልተገኘሁም፡፡ የመስከረም 12 ጉባኤ ከመደረጉ በፊት መኖሩን አናውቅም ነበር፡፡ ነገ ጠዋት እንድትገኙ ነው የተባለው፡፡ እኔ በሰማሁትና በነበሩት ሪፓርቶች ሁኔታ፥ በጉባኤው ላይ አባ ሠረቀ ብርሃን ዋነኛው የጉባኤው ከሳሽ ሆነው ነው የቀረቡት፡፡ ሁሉም እንደሚያስታውሰው በወቅቱ ማኅበረ ቅዱሳን የተከሰሰው በሁለት ጉዳዮች ነው፡፡ በፓለቲካ ውስጥ ገብቷልና የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ውስጥ ጣልቃ ገብቷል የሚል ነው፡፡ ሁለቱም ምንም ዓይነት መሠረት የሌላቸው ናቸው። ማኅበረ ቅዱሳን ፖለቲካ ውስጥ ገብቷል ያሉት በተለያዩ ጊዜ የተጻፉ ዘገባዎችን በማንሣት ጥፋተኛ እንደሆነ ለማሳየት ነው የተሞከረው፡፡ ይሄ የጽሑፍ ሥራ ነው፡፡ እነዚህ ጽሑፎች ሙሉ በሙሉ ሲተረጎሙ ምንም ዓይነት አንድምታ /impact/ አይኖራቸውም ብሎ ማለት ላይቻል ይችላል፡፡     ነገር ግን ሆን ተብሎ የፖለቲካ አቅጣጫ ውስጥ ለመግባት የተሠራ ሥራ አይደለም። ትምህርት የማስተማር፣ ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የመጠበቅ፣ ሠላም እንዲኖር የማድረግ ኃላፊነቶችን እንደ ዓላማ አድርጎ ነው የሚሠራው። ዳሩ ግን እነዚህን በመያዝና ጉዳዩን መንግሥት በልዩ ትኩረት እንዲያየው ለማድረግ በማሰብ ከስም ማጥፋት ተግባሮች እንደ አንዱ ሆኖ የቀረበው ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ሲጀመር ጀምሮ የስም ማጥፋቶች ሲሠሩ ነበር፤ በተለይ በቤተ ክርስቲያን ጠላቶች፡፡ ካለፉት 5 እና 6 ዓመታት ወዲህ የአባ ሠረቀ ወደዚህ ኃላፊነት መምጣት ይሄንን የስም ማጥፋት ዘመቻ የበለጠ ለማጧጧፍ ጉዳዩን መንግሥትም እንደ አደጋ እንዲያየው ለማድረግ የተጠቀሙበት ዘዴ ነው፡፡ ዓላማቸውንም ለማሳካት ሌላ ኃይልን በሙሉ የማሰባሰብ ነው፡፡ ልክ ጌታን ሮማውያን እርምጃ እንዲወሰዱበት በአይሁድ በፖለቲካ እንደተከሰሰው። ያልሠራውን ሠራ ግብር እንዳይከፍል ከልክሏል ሲባል እንደነበረው። አሁንም ተመሳሳይ የስም ማጥፋት ዘመቻና ቤተ ክርስቲያንን የማሳደድ ዘመቻ ነው ያለው፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ማኅበረ ቅዱሳን የተከሰሰው እንጂ፥ በእንደዚህ ዓይነት አቋም ማኅበረ ቅዱሳን በምንም ዓይነት መልኩ በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት የለውም፥ አይኖረውም። ይሄ በመተዳደሪያ ደንቡ የተገለጠ ነው።

የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ላይም ቢሆን ቅዱስ ሲኖዶስ እስከሚያጸድቀው ድረስ ማኅበረ ቅዱሳን ጣልቃ አይገባም የሚል አንቀጽ ነበረው፡፡ የአባቶች ኮሚቴ ሲነጋገር፥ ቅዱስ ሲኖዶስ ሲያጸድቅም፥ ‹‹ግቡም አትግቡም›› የሚል እዚህ ቦታ ላይ አያስፈልግም። አስፈላጊ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያንን በአስተዳደር መርዳት ይኖርበታል። መደገፍ ይኖርበታል። ‹‹ደንቤ አይፈቅድልኝም›› እያለ ዳር ቆሞ ማየት የለበትም በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዐተ ጉባኤ ሲያጸድቅ ይሄን አንቀጽ አስተካክሎ ነው ያጸደቀው። ይሁን እንጂ ማኅበረ ቅዱሳን ካለው ልምድ በመነሣት በቤተ ክርስቲያን አስተደደር ላይ ‹‹እከሌ ይሾም፣ እከሌ ይውረድ እገሌ እንዲህ ነው›› የሚል ነገር አንስቶም አያውቅም። እስከ ዛሬው ሰዓት ድረስ ‹‹ደንቤ ይከለክለኛል፤ አይፈቅድልኝም›› በሚል መንገድም ሄዶ አያውቅም።
 
በ2002 ዓ.ም የተደረገው ስብሰባ ምን ማለት እንደሆነ ራሱ ግልጽ አይደለም። ምን አልባት በቅዱስ ሲኖዶስ ሲነሱ የነበሩ ውዝግቦችን መሠረት አድርጎ ይሆናል፡፡ በዚያን ጊዜም ቢሆን ማኅበር ቅዱሳን አቋሙ ግልጽና ግልጽ ነው። ቅዱስ ሲኖዶሱ በሚወስነው ውሳኔ ይሄዳል የሚል ነው። ያን ሁሉ ውዝግብ የፈጠረው ማኅበረ ቅዱሳን ነው የሚል ስሜት በአባቶቻችንና በሌሎች ሰዎች ለማሳደር የተወጠነ ነው። እንኳን በቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳይ ይቅርና በአንድ አጥቢያ ጉዳይ ማኅበረ ቅዱሳን ጣልቃ ገብቶ አያውቅም፡፡ የመግባትም ፍላጎት የለውም። ትልቁ የስብከተ ወንጌል ጉዳይ እንጂ የገንዘብና የአስተዳደር ነገር ዋነኛ ጉዳይ ነው ብሎ አስቦበት አያውቅም።

ሌላው በአባ ሠረቀና በሌሎችም የቀረበው ክስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከአክራሪዎች እንዲጠበቁና ራሳቸውን እንዲከላከሉ በንቃት ዙያቸውን እንዲያዩ፣ የተጎዳውን በመርዳት በኩል እንዲተባበሩ፣ ቤታቸው የተቃጠለባቸውን እንዲሠሩ፣ የተጎዳ ተጎድቶ እንዳይቀር ሁሉም እንዲነሳሳ የሚያደርጉ መልእክቶችን በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣና በሐመር መጽሔት ላይ በ1999 ዓ.ም አክራሪዎች ባደረሱት ጥቃት ምክንያት የጻፍነውን በማንሳት፥ ‹‹ይሄ ቀስቅሷል›› የሚል ከሌላ አካል አይደለም ከራሳችን የቤተ ክርስቲያን አካላት ከአባ ሠረቀና ከሌሎች አካላት በዚያው ዕለት ቀርቦ ነበር፡፡ 

ለተነሱት ጉዳዮች በሙሉ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም ሁሉም በቂ መልስ ሰጥተዋል። ካጠፋም ማኅበረ ቅዱሳንን እኛ ነው የምንመክረው፤ በቅዱስ ሲኖዶስ ነው የምንመክረው። ከእኛ አቅም በላይ አይደለም የሚል ሐሳብ ተንጸባርቆ ነው የዛን ቀን ስብሰባዎቹ የተደመደሙት። ስለዚህ ያን እንደሌላ ድልና ውጤት በመቁጠር ማኅበረ ቅዱሳንን ለመወንጀልም ስሙን ለማጥፋት የሚሄድበትና የዚያን ጊዜም እድል ተሰጥቶት አልታረመም በሚል ነው እየከሰሱት ያሉ።

•    የተሃድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ለመግታት ዘመቻ የተያዘበት ወቅት ነው፡፡ ዳሩ ግን ኃላፊው የግለሰቦችን ስም መዋቅር ሳይጠብቅ ተሃድሶ መናፍቅ ወዘተ እያለ ያመጣል የተለያዩ ጉዳዮችን ያነሣል? በሚል ክስ ያቀርባሉ ስለዚህ ክስ ማኅበሩ ያለው አቋም ምንድን ነው?

ከዚህ በፊት በግልጽ ፕሮቴስታንት መሆናቸው የታወቁ፥ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብተው የነበሩና የተባረሩ አሉ። አንዱ ‹‹ዲ/ን›› ሙሉጌታ ወ/ገብርኤል የሚባል ነው። ይህ ግለሰብ እዛው ኮሌጅ ውስጥ በመባረር በሂደት ላይ እያለ፣ ከወጣ በኋላም «ማኅበረ ቅዱሳን ወይስ ማኅበረ ሠይጣን›› የሚል መጽሐፍ ጻፈ። ለመጽሐፉ ሰነድ የወሰደው ከማደራጃ መምሪያው ነው። እርሱንም የሰጡት አባ ሠረቀ ብርሃን ናቸው። የእርሱ ማሳተም ብቻ አይደለም ቁም ነገሩ፤ ከዚያ በኋላ የመጽሐፉ ስርጭት ላይም ተሳታፊ ነበሩ። እኛ አስቁሙ ብለን ደብዳቤ ስንጽፍላቸው ማቆም አልቻሉም። በዚህም የተነሣ ከተሐድሶ መናፍቃን ጋር ያላቸው ጥምረት እጅግ በጣም የጠበቀ ሆኖ እናገኘዋልን። ሌሎችንም ተጨማሪ ማስረጃዎች ማቅረብ ይቻላል፡፡ 

አሁን የተሃድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ እየጠነከረ በሄደበት ወቅት ላይ ለማደራጃ መምሪያና ሌሎች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ገለጻ አድርገናል። አባ ሠረቀ ግን በእኛ መርሐ ግብር ላይ አይገኙም። ቢጋበዙም አይመጡም። ማኅበሩ በሚያዘጋጃቸው መርሐ ግብሮች ላይ ጥናቶች ላይ አይገኙም። ስለዚህ እኛ ለሊቃነ ጳጳሳት ሳናሳውቅ ለቅዱስ ሲኖዶስ ሳናሳውቅ ሥራዎችን አልሠራንም። እንቅስቃሴውንም በሚመለከት ከ10 በላይ ለሚሆኑ /ተጨማሪ?/ ሊቃነ ጳጳሳት አሳውቀናል። በጽሑፍም ከ25 በላይ ለሚሆኑ ሊቃነ ጳጳሳት አሳውቀናል። እንግዲህ በቀጣይነት ወደ ቅዱስ አባታችን ገብተን ለማሳወቅ ፕሮግራም ይዘን ባለንበት ወቅት ነው የተሃድሶ መናፍቃኑ ቡድኑ ማዋቅሩን ዙርያውን በመያዝ ወደ ኋላ በመጎተት የስም ማጥፋት ዘመቻዎችን በማኅበሩ ላይ በማካሄድ ከቅዱስነታቸው ጋር ለማጣላትና ለማራራቅ ሙከራዎችን የሚያደርጉት። እኛ አሁን በቅዱስነታቸው መመሪያ ሰጭነት በዚህ በተሕድሶ ጉዳይ ላይ ቤተ ክርስቲያን መፍትሔ ታገኛለች የሚል እምነት አለን፡፡ 

ማደራጃ መምሪያውም ‹‹እኔ ነኝ ማወቅ ያለብኝ። ማንም ሰው መስማት የለበትም።›› የሚለው ይሄ ስሕተት ነው። የአፈጻጸም ሪፓርት አይደለም የምናቀርበው፥ ጥናት ነው ያቀረብነው፡፡ ዓውደ ጥናት ላይ የመንግሥትም መንግሥታዊ ያልሆኑ ባለስልጣናትም ሌሎችም ሰዎች በተገኙበት ጥናት ይቀርባል። ይሄ እንደ አንድ ግኝት፣ ጥናትና እንቅስቃሴ የሚቀርብ እንጂ እኔ ሳላምንበት የሚለው ያልታየ አዲስ አካሄድ ነው። የማደራጃ መምሪያውም በተለይ አባ ሠረቀ ብርሃንም ይሄን ጥናት ደግፈው ይጓዛሉ የሚል እምነትም የለንም። የዓላማ ጉዳይ ስለሆነ ከዚህ በተጻራሪ ቆመው ነው ያሉት። ስለሆነም ጥያቄያቸው እኔ ሰምቼ ለምን አላስቆምኩትም ነው እንጂ፥ ጥናትን ለማቅረብ የግድ የማደራጃ መምሪያው ፈቃድ የሚያስፈልገው ሆኖ አይደለም፡፡ አሁንም በጥናትና ምርምር ማዕከላችንም ሆነ በሌሎች ብዙ ጥናቶችን እናቀርባለን። እነዚህ ጥናቶች በዓመት ዕቅድ ተይዞላቸው የሚቀርቡ ናቸው። የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ግን ቤተ ክርስቲያኒቷን ከፍተኛ የሆነ አደጋ ላይ እየጣለ ያለ ጉዳይ ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ ብፁዓን አባቶች አይተው፣ ሰምተውት ሕዝቡም ማወቅ አለበት የሚለውን ሐሳብ ሰጥተውበትና እነርሱም በጽሑፍ ደርሷቸው ተረድተውት የቀጠልነው ነው። ቅዱስ አባታችን ጋርም አሁንም እስከ ሲኖዶስ ስብሰባ ባለው ጊዜ ውስጥ በተቻለ መጠን ጉዳዩን ተረድተውት አውቀውት የእነዚህን ሰዎች ተንኮልና አካሄድ እንዲያስቆሙ ለማድረግ አሁንም ጥረታችንን እየቀጠልን ነው፡፡
•    ምንም እንኳን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ በ2002 የሥራ ክንውን ሪፖርታቸው ቢገልጹትም አሁንም በኃላፊው መግለጫ ላይ ማኅበረ ቅዱሳን ሂሳቡን ኦዲት አያስደርግም? የባንክ ሂሳቡንም ለማደራጃ መምሪያው ለማሳወቅ ፍቃደኛ አይደለም የሚል ይገኝበታል ስለዚህ ምን ይላሉ? 

በእውነቱ ቅድም እንደጠቀስኩት ማኅበረ ቅዱሳን የሚከፍተው የሂሣብ አካውንት በሙሉ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ታውቀው የሚከፈቱ ናቸው፡፡ ሂሣቡን አያሳውቅም የሚለው ሩቅ ላለ ሰው አስደንጋጭ የሆነ የውሸት ክስ ነው፡፡ ሙሉ በሙሉም ሐሰት ነው፡፡ በጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ፊርማ ከዚህ በፊት በነበሩት መምሪያ ኃላፊዎች ጥያቄ ለጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እየቀረበ የሚከፈተውን የባንክ አካውንት ማኅበረ ቅዱሳን ምስጢር አድርጎ እንደያዘው ሁሉ የባንክ አካውንቱን አያሳውቅም ማለት ምዕመናንን ለማስደንገጥ የታሰበ ነው፡፡ ምዕመናንም ለገዳማትም ለሌሎች አገልግሎቶችም የምትሰጡትን ገንዘብ ለእኛ እያሳወቀ አይደለም በማለት ስም ለማጥፋትና አስደንግጦ ወደ ኋላ ዘወር ለማድረግ የታሰበ ነው እንጂ የማኅበረ ቅዱሳን አካውንት ይታወቃል። ከዚያም በፊትና ከብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ጀምሮ የነበሩት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጆች ናቸው ደብዳቤ ጽፈው ፈቅደው የባንክ አካውንት የሚከፈተው እኔ አላውቀውም የሚሉ ከሆነ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መዝገብ ቤትን ማየት በቂ ነው።

ሁለተኛው ኦዲት አያስደርግም ለሚለው በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ የተቀመጠው፣ የማኅበሩ ኦዲትና ኢንስፔክሽን በየዓመቱና በየጊዜው የማኅበሩን ኦደት ይሠራል ኢንስፔክት ያደርጋል፤ የሚል ደንብ በቅዱስ ሲኖዶስ ተሰጥቶታል። አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የማኅበሩ ሥራ አመራር ጉባኤ በውጭ ኦዲተር የማኅበረ ቅዱሳንን ሂሣብ ኦዲት እንዲደረግ ያደርጋል። ማኅበሩ ዓለም አቀፍ እውቅና ባላቸው የውጭ ኦዲተሮች፣ በመንግሠት የምሥክር ወረቀት የተሰጣቸው /licensed የሆኑ/፣ ግብር የሚከፈሉ፣ በሥራቸውም ጥፋት ቢያጠፉ ሊጠየቁ በሚችሉ ኦዲተሮች አስመርምሯል። ለወደፊትም ያስመረምራል። ይሄንንም ሪፖርት ለጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ለማደራጃ መምሪያውና ለሚመለከታቸው አካላት አስገብቷል። የማኅበረ ቅዱሳንን የኦዲት ሪፖርት አሠራር ውድቅ ሊያደርግ የሚችል አላየሁበትም በማለት አሳውቋል። ስለዚህ ይህ በሆነበት የማኅበረ ቅዱሳን ሂሣብ አይታወቅም አይደረግም ማለት በጣም ከፍተኛ የሆነ ስም የማጥፋት ሥራ ነው። ወይም ስለ ኦዲት ያለመረዳት ችግሮች አይኖርም ብለን አናስብም፡፡
•    ይሄ አለመግባባት ችግር እስከመቼ ይቀጥላል? ማኅበሩስ አቋሙ ምንድን ነው? 

በእነዚህ ስም የማጥፋት ዘመቻዎችና ሁኔታዎች ማኅበረ ቅዱሳን አይደናገጥም። ማኅበሩ የተመሠረተው የቤተ ክርስቲያኒቷን ክፍተት ለመሙላት፣ ድጋፍ ለማድረግ ነው። ሁላችን የሰበካ ጉባኤ አባላት ነን፣ የሰንበት ትምህርት ቤትም አባላት ነን፣ አጥቢያ አለን፣ ቤተ ክርስቲያን አለችን አናስቀድሳለን፣ እንቀድሳለን፣ እናስተምራለን አገልግሎትም እናገኛለን ከአንድ ምእመን የሚጠበቀውን አገልግሎት እንሰጣለን። ማኅበረ ቅዱሳን የመጣው ተጨማሪ ሥራዎችን ለመሥራት፣ ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት፣ ተጨማሪ ጉልበት ለመሥጠት፣ ተጨማሪ ገንዘብ ለማውጣት ነው እንጂ ሌላ ምንም ጥቅም ኖሮት አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ተጨማሪ ሥራ ለምን ያስፈልጋታል ከተባለ የዛሬ 20 ዓመትም፥ 25 ዓመትም የነበሩት ችግሮች ዛሬም አልተፈቱም። ገዳማት እየተዘጉ ነው ያሉት፣ ስብከተ ወንጌል በአግባቡ እየተሥፋፋ አይደለም፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የላቸውም። ሰንበት ትምህርት ቤት የተቋቋመባቸውና ያልተቋቋመባቸው ቢታዩ 25% አይሆኑም፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ለማስተማር አካል ያስፈልጋል እነዚህ ናቸው ማኅበረ ቅዱሳንን እንዲመጣ ያደረጉት። 

ይሄ በራሷ በቤተ ክርስቲያኒቷ መዋቅር ለምን አልተሠራም? ካልን ወደ ዘመናዊው ጊዜ ስንመጣ ያልተለወጡ የተወሰኑ ነገሮች አሉ። ስልት /Strategy/ የለም፣ ዕቅድ የለም፤ በእነዚህ ሥራዎች ላይ መሥራት አልተጀመረም። ከዚያም ይልቅ ሥራን ማደናቀፍ በጣም ትልቅ ሥራ ሆኖ ነው የምንመለከተው። አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኒቷን አስተዳደር አካሄድ አሠራር በተቀናጀና ዕቅድ ባለበት ሁኔታ ለመምራት በጣም ብዙ ሥራዎች ይቀራሉ። ከሚሠሩ ይልቅ የሚያደናቅፉ በጣም ብዙ እንዳሉ እናውቃለን። ቤተ ክርስቲያኒቷንም የማዳከም ሥራ የሚሠሩ ብዙ እንዳሉ እናውቃለን። ይሄን ሠርታችኋል በርቱ ከመባል ይልቅ አቁሙ አቁሙ እንደምንባል ጥንትም እናውቃለን ስንጀምርም እንዲያ ነበር ዛሬም ያው ነው። 

ፈተና ሳይኖር ደግሞ መንፈሳዊ አገልግሎት ሊቀጥል አይችልም ይህ ከሰው ብቻ የሚመነጭ ሳይሆን ከራሱ ከጥሩ ነገር ጠላት ከዲያብሎስም የሚመነጭ ነው። ፈተና ምንም አያስፈልግም ካልን የምንሠራው መንፈሳዊ አገልግሎት /ሥራ/ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ የምንሠራው ሥራ መንፈሳዊ ሥራ ነው። መንፈሳዊ ሥራ ደግሞ የሠይጣን ፈተና አለበት። ሥራችንን እንድናቆም ይፈልጋል እስከ ዛሬ ሲታገለን ቆይቋል ዛሬም ደግሞ አጠንክሮ ይታገላል። የበለጠ በጠነከርን ቁጥር የበለጠ ፈተና ይመጣል። ይሄንን ከቅዱሳት መጻሕፍት እናውቃለን ከታሪክ እናውቀዋለን። ከራሳችንም ሕይወት እናውቃለን። በመሆኑም ይሄ ፈተና እስከመቼ ይቀጥላል ካልን፥ አገልግሎታችን አስከቀጠለ ድረስ ይቀጥላል። ፈታኞቹ ወደ ልቦናቸው ተመልሰው ወደ ሥራ ሲገቡ ሠይጣን ሌላ ፈታኝ ያዘጋጃል። አባ ሠረቀ እንኳን ቢያቆሙና ወደ ትክክለኛው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ቢመለሱ ሰይጣን ሌላ ፈታኝ ያመጣል ይሄ እስከ ክርስቶስ ምጽአት ድረስ የማይቀር ጉዞ ነው። ስለዚህ ይሄ መቼ ይቆማል ብለን የሚቆምበትን ቀን ተስፋ አናደርግም፤ የሚቆመውም መንፈሳዊ አገልግሎታችንን ስናቆም ነው። ስለዚህ ይሄንን ይዘን እንሄዳለን።

ነገር ግን ይሄ ፈተና የሚቀጥል ነው ብለን ችላ ማለት የለብንም። በእኛ በኩል ማድረግ የሚገባንን በሙሉ እናደርጋለን “ከእንግዲህ ከማኅበሩ ጋር አልሠራም” የሚል ደብዳቤ ጽፈዋል። “ማኅበሩ የሚሰጠውን ደብዳቤ በሙሉ አልመልስለትም” በማለት ለጠቅላይ ቤተ ክህነት አቤቱታ አቅርበዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ማኅበሩ ጥያቄ ያቀርብላቸዋል። እንደማይመልሱም እየታወቀ ትክክለኛ መንገድ ተከትለን እንሄዳለን። ስንመልስላቸው አልተመለሰልንም ብለው ያቀርባሉ እኛም መልሰን እንመልስላቸዋለን። ሁል ጊዜም ግን ለፋይል እንዲመቻቸው ‹‹አልተመለሰልኝም፣ አልታዘዘኝም፣ አልታዘዘኝም›› ነው የሚሉት። እኛ ግን እየታዘዝን፣ እየታዘዝን እንቀጥላለን። እየተቀበልን መፈጸም የሚገባንን እንቀጥላለን። 

አሁን በመሠረቱ ማኅበረ ቅዱሳን ከፍተኛ ገንዘብ እንዳለው ያስወራሉ። የምዕመኑ ገንዘብም ወደዚህ እንደመጣ አድርገው ይናገራሉ። ስለዚህ የመቀራመትና የመውሰድ ስሜት ነው ያላቸው። ማኅበረ ቅዱሳን ገንዘብ የለውም፤ አንዳንድ ዕቅዶችንም እየሰረዘ ነው የሚሠራው ባንክ አካውንቱን አያሳውቅም ይላሉ እንጂ ባንክ አካውንቱን ማየት ይችላሉ። በማኅበረ ቅዱሳን በየወሩና በየሁለት ወሩ በምትሰበስብ ገንዘብ ሥራ እየሠራን ነው የምንቀጥለው። እዚህ የሚሰጠው አገልግሎት በአበልና በደመወዝ የተንበሸበሹ አድርገው ነው የሚያስቡት። ይሄ በሙሉ ግን የተሳሳተ ነው። ስለዚህ ከፍተኛ ገንዘብ አለና ያንን ገንዘብ እንቆጣጠራለን የሚል ስሜት እንዳለ አንዳንድ ፍንጮችን እያየን ነው። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ጋር ያለውን ግልጽ አሠራር አሁንም የበለጠ ግልጽ እያደረገ አባቶችም እንዲረዱ እያደረግን፥ ለቅዱስ ሲኖዶስም እያሳወቅን እንቀጥላለን። በተለይም በአሁኑ ሲኖዶስ የመናፍቃንን እንቅስቃሴ ጉዳይ እና ለዚህ ተባባሪ ሆነው እየሠሩ ያሉትን የመምሪያው ኃላፊዎች ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ እልባት መስጠት አለበት ብለን እናስባለን። ውሳኔ ያገኛሉ ብለንም እናስባለን። ማኅበረ ቅዱሳንም በተሰጠው መተዳደሪያ ደንብ መሥራት አለመሥራቱን ቅዱስ ሲኖዶስ ራሱ ማረጋገጥ የሚችለው ጉዳይ ነው። በየሀገረ ስብከቱ ከአባቶች ጋር ነው የምንሠራው አየር ላይ አይደለም እየሠራን ያለነው። የማኅበሩን አገልግሎት ብፁዓን አባቶች አቅም አላቸው ሥልጣኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ነው። መወሰን የሚችለውም ቅዱስ ሲኖዶስ ነው ብለን እናምናለን።
•    በመጨረሻም ቀረ የሚሉት ካለ?

በሚጻፉና በሚባሉ በሚሰራጩ የውሸት ፕሮፓጋንዳዎችና የስም ማጥፋት ዘመቻዎች ምእመናንም ሆኑ የማኅበሩ አባላት መረበሽ የለባቸውም። የፈለገ ያህል ፈተና ቢመጣ ደግሞ ፈተና እንደሚኖር ማወቅ አለባቸው፡፡ ከፈተና የራቀ አገልግሎት የለም። ስለዚህ የሚነሡትን ነገሮች በሙሉ በመከታተልና በማወቅ ለግንዛቤ ከመያዝ ባሻገር፥ ሥራን ለማቆም አገልግሎትን ለመተው ማሰብ የለባቸውም። በእልህም ደግሞ ወደ ሌላ መጥፎ ተግባር ውስጥ መግባት የለባቸውም፤ ይገባሉ ብዬም አልጠብቅም፡፡ ሁል ጊዜም በትክክለኛና በሕጋዊ መንገድ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል ዛሬም ወደፊትም ጠንካራ ሆኖ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል። ከዚህ የበለጠ ፈተና ሠይጣን ሊያመጣባቸው ይችላል። ሙሉ በሙሉም የማኅበሩ አገልግሎት በከፍተኛ ሁኔታ የማደናቀፍ ሥራ ሊፈጥር ይችላል ብለን ብናስብ እንኳን ይሄ በሙሉ የሠይጣን ፈተና መሆኑን አውቀን ከመንፈሳዊ አገልግሎታችን ምንጊዜም ቢሆን ወደኋላ ማለት የለብንም። በአጥቢያችን፣ በወረዳችን፣ በሀገረ ስብከታችን ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ትጉዎች መሆን ነው ያለብን፤ ለስም አይደለም የምንሠራው፣ ለማኅበረ ቅዱሳንም አይደለም የምንሠራው ለቤተ ክርስቲያናችን ነው። የምንሠራው በተጨማሪም አጽራረ ቤተ ክርስቲያንን ነቅተን መጠበቅና ምላሽ ለመስጠት ዝግጁዎች መሆን ይጠበቅብናል:: ይሄን ነው ለማስተላለፍ የምወደው፡፡
•    እግዚአብሔር ይስጥልን፡፡

እኔም እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ቢሮ ያከናውናቸውን ተግባራት አስታወቀ።

በይብረሁ ይጥና

ሥራዎቹንም የሚያሳይ ዓውደ ጥናት በኢትዮጵያ የስብሰባ ማእከል እንደሚካሔድ ተገልጧል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ  መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውንና በቀጣይ ሊሠራ ያቀዳቸውን ተግባራት አስታወቀ፡፡
 
የፕሮግራሙ ማስተባበሪያ ቢሮ ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ እንዳስታ ወቁት በ2001 እና 2002 ዓ.ም ፕሮግራሙን ለምእመናን የማስተዋወቅና የመቅረጽ ሥራ ተሠርቶ በተወሰነ ደረጃ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡

በ2003 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት ለትምህርትና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ክፍል የተነደፈውን ፕሮግራም እንዲያውቀው ተደርጓል፡፡ መምሪያውም ለፕሮግራሙ ማስፈጸሚያ የሚሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ተገብቷል፡፡

እንደዚሁም ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መምሪያ ጋር በመሆን ፕሮግራሙ ተግባራዊ ከሚደረግባቸው ሃያ ሀገረ ስብከቶች ለተውጣጡ ሥራ አስኪያጆችና ሰባክያነ ወንጌል በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ፕሮግራሙን የማስተዋወቅ ሥራ ከተሠራ በኋላ ለተግባራዊነቱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ደብዳቤ ተበትኗል ሲሉ አመልክተዋል፡፡

ፕሮግራሙ በዋናነት የሚያተኩረው ስብከተ ወንጌልን ለምእመናን ማዳረስ ሲሆን የንድፈ አሳቡ መነሻ ደግሞ በተለይ በጠረፋማና ገጠራማ አካባቢ ለሚገኙ ምእመናን ጉባኤ ማካሔድና ሰባኬ ወንጌል ከመመደብ ጀምሮ ለአካባቢው ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር አባላትም የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ነው፡፡

ፕሮግራሙ በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ ዐርባ አምስት ሀገረ ስብከቶች መካከል ችግሩ ይበልጥ ይከፋል ተብሎ በታመ ነባቸው ሃያ ሀገረ ስብከቶች መሆኑን አቶ ዳንኤል  ጠቁመው፣ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል በሚገኙ ጠረፋማና ገጠር አካባቢዎች ልዩ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል፡፡

የፕሮግራሙ ማስተባበሪያ ቢሮው በ2003 ዓ.ም እሠራቸዋለሁ ብሎ ካቀዳቸው ዕቅዶች መካከል፤ ዐሥር ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ፣ ሃያ የሕዝብ ጉባኤያትን ማካሔድ፣ በተለያዩ ቋንቋዎች ዐሥራ ሁለት የስብከame=”Medium List 2 Accent 5″/> » አለው፡፡

ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከእስራኤል ሽማገሌዎች ጋር በኮሬብ በነበረው ዐለት ያደረገው ስብሰባ በሐዲስ ዘመን ከተሰበሰቡት ሲኖዶሶች /ጉባኤዎች/ ጋር ይመሳሰላል፡፡

ሙሴ በሌላ ጊዜ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ከእስራኤል ሽማግሌዎችና ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ለመውጣት ያደረገው ስብሰባ ከሲኖዶስ ጋር የሚመሳሰል ነው፤/ዘፀ.19፡1-25/፡፡ በተለይም የእግዚአብሔርን ክብር ያዩ ዘንድ ሙሴና የእስራኤል ሽማግሌዎች፣ ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ወጥተው በሩቅ ቆመው ለእግዚአብሔር ክብር ስግደት በማቅረብ የተሰበሰቡት ስብሰባ ሲኖዶስን የሚመስል ነው እንላለን፡፡ /ዘፀ.24111/፡፡

በሌላ በኩል የእስራኤል ልጆች ወደ ምድረ ከነዓን ለመግባት በሲና ምድረ በዳ በሚጓዙበት ወቅት የሚበላ ዳቦና የሚጠጣ ውኃ ሲያጡ ወደ ሙሴ ይጮኹ ነበር፡፡ ሙሴም የሕዝቡን ችግር ለእግዚአብሔር እያሰማ ሕዝቡ ማግኘት የፈለጉትን ያሰጣቸው ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት አንድ ቀን የእስራኤል ልጆች እጅግ ጎምጅተው «የምንበላው ሥጋ ማን ይሰጠና? በግብፅ ሳለን ያለዋጋ ዓሣውንም፣ ዱባውንም፣ በጢሁንም፣ ነጭ ሽንኩርቱንም፣ ቀይ ሽንኩርቱንም እንደ ልብ እንበላ ነበር፡፡ አሁን ግን ሰውነታችን ደረቀች፣ ዐይናችንም ከዚህ መና በቀር የሚያየው የለም» ብለው አጉረመረሙ፡፡


በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ሙሴን ጠርቶ ከሕዝቡ ሰባ ሽማግሌዎችን የሕዝቡ አለቆችና ሸማግሌዎች ይሆኑ ዘንድ መርጦ ወደ መገናኛው ድንኳን እንዲያቀርባቸው አዘዘው፡፡ ሙሴም እግዚአብሔር እንዳዘዘው ሰባዎቹን ሰዎች ከሕዝቡ መርጦ ወደ ማደሪያው ድንኳን አቀረባቸው፡፡ እግዚአብሔርም ለሙሴ ከሰጠው መንፈስ ወስዶ በእነርሱ አሳደረባቸው፡፡ መንፈስም
/መንፈስ ቅዱስ/ በሰባው ሰዎች ላይ ባደረ ጊዜ ትንቢት ተናገሩ፡፡ በዚያው ወቅትም ከሰባው ጋር ተመርጠው ወደ ድንኳኑ ሳይመጡ በሕዝቡ ሰፈር የቀሩ ኤልዳድና ሞዳድ የተባሉ ሰዎች ነበሩ፡፡ መንፈስም ባሉበት ወረደባቸው፡፡ እነርሱም ትንቢትን ተናገሩ፡፡ ከዚያ በኋላ ከእነዚህ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎች ጋር ሙሴ የሕዝቡን ችግር እንዲሸከም ታዘዘ፡፡ ከዚያም እግዚአብሔር ከእነዚህ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎች /72 ሊቃናት/ ፊት በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል ልጆች ሥጋ አዘነበላቸው፤/ዘኁል.11፥115/፡፡

በመሆኑም የእነዚያ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎችና የሙሴ በማደሪያው ድንኳን መሰብሰብና የመንፈስ ስጦታን መቀበል በዘመነ ሐዲስ ከተደረጉት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤዎች ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ኢያሱም ከሙሴ ዕረፍት በኋላ ሕዝበ እስራኤልን ለመምራት እንዲችል በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሙሴ ኢያሱን በማኅበሩ ሁሉ ፊት /በጉባኤ ፊት/ በአንብሮተ እድ እንደሾመው መጽሐፍ ይነግረናል፤ /ዘኁል.27፥1523/፡፡ ስለሆነም የኢያሱ በጉባኤው ፊት መሾም ሰባቱን ዲያቆናት በአንብሮተ እድ ከሾሙት ከሐዋርያት ጉባኤ ጋር የሚመሳሰል ነው፤ /ሐዋ.6፥16/፡፡

እንደዚሁም በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ በምዕራፍ 2፥12 እና በምዕራፍ 4፥30 ላይ እንደተገለጸው፤ ደቂቀ ነቢያት በነቢዩ በኤልሳዕ ፊት ያደረጉት ስብሰባ ከቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ስለዚህ በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳን ሐዋርያት ካደረጉት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በፊት በዘመነ ብሉይ በሕዝበ እስራኤል መካከል የተከሰተውን ችግር ለማስወገድና ሕዝበ እስራኤንም በጉባኤ ውሳኔ ለመምራት ቅዱስ ሲኖዶስን የመሰሉ ስብሰባዎች መደረጋቸውን በአጭሩ ለማስረዳት ተሞክሮአል፡፡

ሲኖዶስ ዘቅዱሳን ሐዋርያት

የቤተክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስረዳን የክርስቶስን ቤተክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ መምራት የጀመሩት ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በሥምረት ለመምራት በዘመናቸው የተለያዩ ጉባኤዎችን እንዳደረጉ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ይኸውም በአስቆሮታዊው ይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ ለመምረጥ ያደረጉት ስብሰባ ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞተና ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ቅዱስ ሉቃስ እንደመሰከረው ለደቀመዛሙርቱ አርባ ቀን እየተገለጸላቸው፣ ስለእግዚአብሔር መንግሥትም እየነገራቸው /እያስተማራቸው/ በብዙም ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖና ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን ለእነርሱ እየታያቸው ቆየ /ሐዋ.1፥1-4/፡፡

ስለ እርሱ የተጻፉትንም መጻሕፍት ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፡፡ እንዲህም አላቸው፣ «ክርስቶስ መከራ ይቀበላል፣ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ይነሣል፣ በስሙም ንስሐና ኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል» ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል፡፡ እናንተም ስለዚህ ምስክሮቼ ናችሁ፡፡ እነሆም «አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ብሎ አዘዛቸው፡፡ ከዚያም ወደ ቢታንያ ወደ ደብረ ዘይት አወጣቸው፣ እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው፣ ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ፣ ወደ ሰማይም ዐረገ» /ሉቃ.24፥41-53/፡፡ እነርሱም ጌታ ወዳረገበት ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች /ሁለት መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ፡፡ ደግሞም እንዲህ አሉአቸው «እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ ትኩር ብላችሁ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችሁ? እነሆ ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁ እንዲሁ ይመጣል» ሲሉ ነገሩአቸው፡፡ /ሐዋ.1፥6-11/፡፡

ሐዋርያትም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፡፡ ከዚያም ዘወትር እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያወደሱ /እየባረኩ/ በመቅደስ /በጽርሐ ጽዮን/ ኖሩ /ሉቃ.24፥50/፡፡ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ በአጠቃላይ መቶ ሃያ ሰዎች ያህል ባሉበት ቅዱስ ጴጥሮስ ተነሥቶ በይሁዳ ቦታ ሌላ ሰው መተካት እንዳለበት ንግግር አደረገ፡፡ «ወንድሞች ፥ሆይ፣ ኢየሱስን ለያዙት መሪ ስለሆናቸው ስለ ይሁዳ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው ይፈጸም ዘንድ የተገባ ሆነ፤ እርሱም ከእኛ ጋር ተቆጥሮ ነበርና፣ ለዚህም ሐዋርያዊ አገልግሎት ታድሎ ነበርና» ብሎ በመናገር ስለ አስቆሮቱ ሰው ስለ ይሁዳ ዐመፅና አሟሟት ገለጻ አደረገ፡፡ ከዚያም ይሁዳን ስለሚተካው ሰው አስመልክቶ «ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ እኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፣ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣ ኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል» ብሎ ገለጸ፡፡

ወዲያውም በጉባኤው ስምምነት መሠረት የመቶ ሃያው ማኅበር አባላት ከነበሩት መካከል በርያስ የተባለውን ዮሴፍንና ማትያስን፣ሁለቱን በመካከል አቆሙአቸው፡፡ ስለ እነርሱም ሲጸልዩ፤ «የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ፣ ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ይሔድ ዘንድ በተዋት በዚህች አገልግሎትና ሐዋርያነት ቦታን እንዲቀበል የመረጥኸውን ከእነዚህ ከሁለቱ አንዱን ሹመው» ብለው ጸለዩ፡፡ ቀጥሎም ዕጣ ተጣጣሉላቸው፤ ዕጣውም ለማትያስ ወደቀ /ወጣ/፡፡ እርሱም ዐሥራ አንዱ ሐዋርያት ጋር ተቆጠረ» /ሐዋ.1፥15-26/፡፡

ማትያስን መርጠው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንዲሾመው ከጸለዩ በኋላ ቁ ሩ ከሰብዐ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የነበረው ረድእ ማትያስ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተሹሞ ከቀሩት ሐዋርያት ጋር ገብቶ ተቆጠረ፡፡ በዚህ ሁኔታ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ከአርያም /ከሰማይ/ የሚላክላቸውን ኃይል ማለት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ደጅ እየጠኑና እየተጠባበቁ በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ሰነበቱ፡፡ በዓለ ሃምሳም የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜ ጌታ ባረገ በዐሥረኛው ቀን ሁሉም በአንድነት አብረው እየጸለዩ ሳለ ድንገት እንደሚነጥቅ አውሎ ነፋስ ከሰማይ ወደ እነርሱ ድምፅ መጣ፡፡ ተቀምጠው የነበሩበትንም ሁሉ ሞላው፤ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች /የእሳት ላንቃ/ የመሰሉ ታዩአቸው፤ በእያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጠባቸው፣ መንፈስ ቅዱስም ይናገሩ ዘንድ እንደሰጣቸው በልዩ ልዩ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር፤ /ሐዋ.2፥1-5/፡፡

በዚህ ጊዜ ጌታችን ከትንሣ ኤው በፊት «እኔ በአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ /ጰራቅሊጦስ/ ከአብ የሚወጣ /ዘይሠርጽ/ የጽድቅ /የእውነት/ መንፈስ በመጣ ጊዜ ስለ እኔ ይመሰክራል፣ እናንተም ደግሞ ከመጀመሪያ ጀምሮ ከእኔ ጋር ኖራችኋልና ትመሰክራላችሁ» ብሎ የተናገረው ተስፋ ተፈጸመ፡፡ ደግሞም ወደ ሰማይ በሚያር ግበት ወቅት «እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ» ሲል የሰጠው ሰማያዊ ተስፋ ተፈጸመ፤ /ሉቃ.24፥49፤ሐዋ.2፥43/፡፡

ከዚህ በላይ እንዳየነው ከበዓለ ሃምሳ ዋዜማ ጀምሮ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን የተካሔደው የመጀመሪያው የሐዋርያትና የሰብዓ አርድእት ጉባኤ እጅግ በጣም ታላቅ ጉባኤ ስለነበረ የመጀመሪያው የሐዋርያት ሲኖዶስ ሊባል ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም፦

1. ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም የነበረችበት ጉባኤ በመሆኑ፤
2. ቅዱስ ማትያስን የመረጠና የሾመጉባኤ በመሆኑ፤
3. ለሐዋርያትና ከእነሱ ጋር በጸሎት ተሰብስበው ለነበሩት ሁሉ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ጉባኤ በመሆኑ፤
4. በዚያው ቀን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በመውረዱ ምክንያት በሐዋር ያት ስብከት ሦስት ሺሕ የሚያህል ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የቤተክርስቲያን አባል የሆነበት ቀን በመሆኑ ጉባኤው የቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ ይገባል፡፡ በመሆኑም  ቤተክርስቲያን ታሪክ የቅዱስ ሲኖዶስ ታሪካዊ አመሠራረት ከዚህ ቀዳሚው ጉባኤ መሆኑ የሚያከራክር አይደለም፡፡ በሌላ መንገድም በቤተክርስቲያን ታሪክ እንደተመዘገበው ከሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው በተለያዩ ቦታና ዘመን የተደረጉ የአህጉረ ስብከት /Regionsl or local/ ሲኖዶሶችና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ ሲኖዶሶች መሠረታቸው የኢየሩሳሌሙ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ ነው ቢባል እርግጥ ነው፡፡

ሁለተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ

ሁለተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ የሚገባው ጉባኤ፤ ራሳቸው ሐዋርያት ተሰብስበው የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን በአንብሮተ እድየሾሙት ዐቢይ ሲኖዶስ ተደርጎ እንደነበረ መጽሐፍ ያረጋግጥልናል፡፡ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት /ደቀመዛሙርት/ ምእመናንን በሙሉ ጠርተው፤ «እኛ የእግዚአብሔርን ቃል /ወንጌልን/ ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም፡፡ ወንድሞች ሆይ በመልካም የተመሰከረላቸውን፣ መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፣ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፣ እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን» ብለው ገለጹላቸው፡፡ ይህም ቃል /ንግግር/ ሕዝቡን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፡፡ ስለዚህም እምነትና መንፈስ ቅዱስም የመላበትን ሰው እስጢፋኖስን፣ ፊልጶስንም ጵሮኮ ሮስንም፣ ኑቃሮናንም ጰርሜናንም መረጡ፡፡ በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው ሐዋርያት ከጸለዩ በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው /ሐዋ. 6፥1-7/፡፡

ከላይ እንደተገለጸው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ከአርድእትና ከምእመናኑ ጋር ተሰብስበው ከተወያዩ በኋላ፤ ሐዋርያት በወሰኑት ውሳኔ ሕዝቡ በሙሉ ተደስተው ሰባቱን የቤተክርስቲያን አገልጋዮች መርጠው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አቅርበው የሾሙት ጉባኤ በመሆኑም ጉባኤው ከወሰነው ታላቅ ቁም ነገር የተነሣ  «ሲኖዶስ» ተብሎ ሊጠራ ይችላል፡፡ ነገር ግን እንደሚታወቀው በቤተ ክርቲያን ታሪክ መሠረት በተለምዶ የመጀመሪያው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ወይም የመጀመሪያው ሲኖዶስ ተብሎ የሚጠራው በኢየሩሳሌም 50/51 ዓ.ም የተደረገው ጉባኤ ነው፡፡

ሦስተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ

ይህ በኢየሩሳሌም የተደረገው ሦስተኛው የሐዋርያት ጉባኤ ቅዱስ ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ ይገባል፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ /ሲኖዶስ/ እየተባለ መጠራቱ ሁሉም የሚያውቀው ነው፡፡ ጉባኤው ሊደረግ የተፈለገበት ዋና ምክንያት የሚከተለው ነው፡፡ በሐዋርያት ዘመን በአንጾኪያ ከተማ በነበረችው ቤተክርስቲያን ነቢያትና መምህራን ነበሩ፡፡ እነርሱም በርናባስ፣ ኔጌር የተባለው ስምዖን፣ የቀሬናው ተወላጅ ሉክዮስ፣ የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረው የሄሮድስ ባለሟል ምናሔና ሳውል እነዚህ ሁሉ ጌታን እያመለኩና እየጾሙ ሳለ መንፈስ ቅዱስ፤ «በርናባስንና ሳውልን ለጠ ራኋቸው ሥራ ለዩልኝ፤ ፍልጥዎሙ ሊተ ለበርናባስ ወለሳውል ለገብር ዘፈቀድክዎሙ» አላቸወ፡፡ እነርሱም መንፈስ ቅዱስ እንደነገራቸው አደረጉ፡፡ ከጾሙ ከጸለዩና እጃቸውንም ከጫኑ በኋላ አሰናበቱአቸው   /ሐዋ.13፥1-3/፡፡

ከዚያም ጳውሎስ በርናባስና ማርቆስ ከሌሎቹ ጋር ወደ ቦታው ሁሉ እየዞሩ ወንጌልን ሰበኩ፡፡ በየሰንበቱም በአይሁድ ምኩራብ እየተገኙ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነትና ስለ ትንሣ ኤው ይሰብኩ ነበር፡፡ እንደዚሁም በልስጥራ፣ በደርቤን፣ በጲስድያ፣ በጵንፍልያ፣ በጴርጋሞን፣ በጵርሄንም የእግዚአብሔርን ቃል /ወንጌልን/ እየሰበኩ ሕዝቡን ያጽናኑ ነበር፡፡ አንጾኪያም በደረሱ ጊዜ ቤተክርስቲያንን /ምእመናንን/ ሰብስበው እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ሁሉ ለአሕዛብም የሃይማኖት ደጅ አንደተከፈተላቸው ተናገሩ፡፡
ነገር ግን በዚያን ጊዜ አንዳንዶች ከይሁዳ ሀገር ወደ አንጾኪያና ወደ ሌሎቹ አውራጃዎች ወረዱና «እንደሙሴ ሥርዓት ካልተገረዛችሁ ትድኑ ዘንድ አትችሉም» እያሉ ወንድሞችን /ምእመናንን/ ያስተምሩ ጀመር፡፡ በዚያን ጊዜ በእነዚያ ሰዎች በጳውሎስና በበርናባስ መካከል ብዙ ጠብናክርክር ተፈጠረ፡፡ ጠቡና ክርክሩ እያየለ በሔደ ጊዜ ጳውሎስ፣ በርናበስና ከእርሱ ጋር የነበሩ የወንጌል አገልጋዮች ተነጋግረው ወደ ሐዋርያት ለመሔድ ወሰኑ፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም በደረሱጊዜ ቤተክርስቲያን /ምእመናን/ ሐዋርያትና ቀሳውስት /Aposstles and the elders/ ተቀበሉአቸው፡፡ እነ ጳውሎስም በዞሩባቸው አህጉረ ስብከት ሁሉ ያደረጉትን /የፈጸሙትን/የወንጌል አገልግሎትና የገጠማቸውን ችግር ሁሉ በዝርዝር ሪፖርት አቀረቡ፡፡ በዚያን ጊዜ በጌታ ካመኑት ከፈሪሳውያን ወገን የሆኑት ሰዎች ተነሥተው «ትገርዙአቸው ዘንድና የሙሴንሕግ እንዲጠብቁ ታዝዙአቸው ዘንድ ይገባል» ብለው ለሐዋርያት ተናገሩ፡፡ እነሆም በዚያን ጊዜ ሐዋርያትናቀሳውስት /Apostles and the elders/ ለመመካከርና ለመወሰን በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ የዚህ ዐቢይ ሲኖዶስ ሰብሳቢ /ሊቀመንበርም/ ቅዱስ ያዕቆብ ኤጲስ ቆጶስ ዘኢየሩሳሌም እንደነበር በቤተክርስቲያን ታሪክ ተገልጿል፡፡ በጉባኤውም በቀረበው ጉዳይ ላይ ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያውን ንግግር አደረገ፡፡ ከቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር በኋላም ጳውሎስና በርናባስ ተነሥተው እግዚአብሔር በእጃቸው በአሕዛብ መካከል ያደረገውን ምልክትና ድንቅ ነገር ሁሉ ለሲኖዶሱ ተረኩ፡፡ ከዚያም የጌታ ወንድም እየተባለ የሚጠራው የኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስና የጉባኤው ሰብሳቢ ቅዱስ ያዕቆብ ንግግር አደረገ፡፡ ከቅዱስ ያዕቆብ ንግግር በኋላ
ሐዋርያትና ቀሳውስት /Apostles and the elders/ ከቤተክርስቲያኑ /ምእመናኑ/ሁሉ ጋር ከእነርሱ የተመረጡትን ሰዎች ከጳውሎስና ከበርናባስ ጋር ወደ አንጾኪያ ይልኩ ዘንድ ተስማሙ፡፡ ከእነ ጳውሎስ ጋር እንዲሔዱ የተመረጡትም በርስያን የተባለው ይሁዳናሲላስ ነበሩ፡፡ የጉባኤውም አባላት በጉባኤ የተወሰነውን ውሳኔ ጽፈው በተመረጡት ወንድሞች እጅ ላኩ፡፡ መልእክተኞቹም ተሰናብተው ወረዱ፤ ሕዝቡንም ሰብስበው ከሐርያት ጉባኤ የተላከውን ደብዳቤ ሰጡአቸው፡፡ ባነበቡትም ጊዜ ከምክሩ የተነሣ  ደስ አላቸው፡፡ ይሁዳና ሲላስም ደግሞ ነቢያት ነበሩና ወንድሞችን በብዙ ቃል መክረው አጽናኑአቸው፡፡ አያሌ ቀንም ከእነርሱ ጋር ከተቀመጡ በኋላ ከወንድሞቻቸው በሰላም ተሰና ብተው ወደ ሐዋርያት ተመለሱ፡፡ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊትና ሲኖዶሳዊት ለመሆንዋ ተደጋግሞየተነገረ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የተመሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ቤተክርስቲያንን በስብከተ ወንጌል ስለአሰባሰቡና ስለአጠናከሩ ቤተክርስቲያን በሲኖዶስ እየተመራች ከዚህ ዘመን በመድረስዋ ሲኖዶሳዊት /ጉባኤያዊት/ እየተባለች ትጠራለች፡፡

ከቅዱሳን ሐዋርያት ቀጥለው የተነሡት አባቶችም ቤተክርስቲያንን በሚመሩበት ወቅት፡-
ሀ. የቤተክርስቲያንን ቅዱሳት መጻሕፍት ከመናፍቃን መጻሕፍት ለመለየትና ቁጥራቸውን
    በቀኖና /በሕግ/ ለመወሰን፤
ለ. ሥርዐተ ቅዳሴንና ሥርዐተ ጸሎትን በቀኖና /በሕግ/ ለመመደብ፤
ሐ. አጽዋማትንና በዓላትንም ለመወሰን የሲኖዶስ ስብሰባ በማድረግ ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ ወስነዋል፡፡ በሌላ በኩልም ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው መናፍቃን /ሐራ ጥቃዎች/ በተነሡ ጊዜ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን አባቶች ርትዕት፣ ስብሕት /ኦርቶዶክስ/ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሐራጥቃዎችን በቀኖናዋ ውግዘት ለማስወገድ በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ ይወስኑ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በየሀገሩ የአካባቢ ሲኖዶሶች /Regional or Local synods/ ተደርገዋል፡፡ ከተደረጉት ሲኖዶሶችም ለአብነት ጥቂቶቹን ቀጥለን እንመለከታለን

1.    በ257ዓ.ም በካርቴጅ የተደረገው ሲኖዶስ፡- በዚህ የአካባቢ /regional/ ሲኖዶስ ሰማንያ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሳትፈዋል፡፡ የሲኖዶሱ ሰብሳቢ ቅዱስ ሲፕሪያኖስ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ሥርዓተ ጥምቀትንና መናፍቃንን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የኤጲስ ቆጶሳትን ሥልጣን የተመለከቱ ቀኖናዎች ተወስነዋል፡፡
2.    268 – 270 ዓ.ም በተከታታይ በአንጾኪያ ሲኖዶስ ተደርጎአል፡፡ በዚህ ሲኖዶስ ዐሥራ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በምስጢረ ሥጋዌ የኅድረትንና የፅምረትን /ምንታዌ አካላትን/ ትምህርት ማስፋፋት የሞከረውን ኤጲስ ቆጶስ ጳውሎስ ሳምሳጢን መክረው አልመለስ ስላለ አውግዘው ከቤተክርስቲያን ለይተውታል፡፡
3.    በዚሁ ዓይነት በአንካራ በ314 ዓ.ም ፣በጋንግራ 365 ዓ.ም፣ በሳርዲካ በ343ዓ.ም፣ በአንጾኪያ በድጋሚ በ341 ዓ.ም፤ በላኦዶቂያ በ334 እና በ381 ዓ.ም የተጠራው ሲኖዶስ ስድሣ  ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ እንደዚሁም በድጋሚ በካርቴጅ በ419 ዓ.ም የተሰበሰበው ሲኖዶስ )138 ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ ይህ ሲኖዶስ «የአፍሪካ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ» በሚል መጠሪያ ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሐዋርያውያነ አበው /Apostolic Fatheres/ የቤተክርስቲያንን አስተዳደርና የቤተክርስቲያንን ችግር በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ በመመርመርና አስፈላጊውንም በመወሰን ቤተክርስቲያንን መርተዋል፡፡ ያውም ከሰባ ዓ.ም ጀምሮ እስከ 313 ዓ.ም ድረስ የነበረው ጊዜ አሕዛብ በቁር የበዙ በትና በመንግሥት አስተዳደርም አጠቃላይ ሥልጣን ግን የጨበጡበት ዘመን ስለነበረ፤ በዚህ ዘመን ከፀረ እግዚአብሔርና ከፀረ ክርስትና ኃይሎች ጋር በመጋደል በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ስለ ሀልዎተ እግዚአ ብሔርና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው መሥዋዕት ሆነው የተሰውበት ዘመን ነበር፡፡ በመሆኑም ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት እየተባለ ይጠራል፡፡

ከቅዱሳን ሐዋርያት ቀጥለው የተነሡት አባቶችም ቤተክርስቲያንን በሚመሩበት ወቅት፡-
ሀ. የቤተክርስቲያንን ቅዱሳት መጻሕፍት ከመናፍቃን መጻሕፍት ለመለየትና ቁጥራቸውን
    በቀኖና /በሕግ/ ለመወሰን፤
ለ. ሥርዐተ ቅዳሴንና ሥርዐተ ጸሎትን በቀኖና /በሕግ/ ለመመደብ፤
ሐ. አጽዋማትንና በዓላትንም ለመወሰን የሲኖዶስ ስብሰባ በማድረግ ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ ወስነዋል፡፡ በሌላ በኩልም ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው መናፍቃን /ሐራ ጥቃዎች/ በተነሡ ጊዜ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን አባቶች ርትዕት፣ ስብሕት /ኦርቶዶክስ/ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሐራጥቃዎችን በቀኖናዋ ውግዘት ለማስወገድ በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ ይወስኑ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በየሀገሩ የአካባቢ ሲኖዶሶች /Regional or Local synods/ ተደርገዋል፡፡ ከተደረጉት ሲኖዶሶችም ለአብነት ጥቂቶቹን ቀጥለን እንመለከታለን

1.    በ257ዓ.ም በካርቴጅ የተደረገው ሲኖዶስ፡- በዚህ የአካባቢ /regional/ ሲኖዶስ ሰማንያ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሳትፈዋል፡፡ የሲኖዶሱ ሰብሳቢ ቅዱስ ሲፕሪያኖስ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ሥርዓተ ጥምቀትንና መናፍቃንን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የኤጲስ ቆጶሳትን ሥልጣን የተመለከቱ ቀኖናዎች ተወስነዋል፡፡
2.    268 – 270 ዓ.ም በተከታታይ በአንጾኪያ ሲኖዶስ ተደርጎአል፡፡ በዚህ ሲኖዶስ ዐሥራ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በምስጢረ ሥጋዌ የኅድረትንና የፅምረትን /ምንታዌ አካላትን/ ትምህርት ማስፋፋት የሞከረውን ኤጲስ ቆጶስ ጳውሎስ ሳምሳጢን መክረው አልመለስ ስላለ አውግዘው ከቤተክርስቲያን ለይተውታል፡፡
3.    በዚሁ ዓይነት በአንካራ በ314 ዓ.ም ፣በጋንግራ 365 ዓ.ም፣ በሳርዲካ በ343ዓ.ም፣ በአንጾኪያ በድጋሚ በ341 ዓ.ም፤ በላኦዶቂያ በ334 እና በ381 ዓ.ም የተጠራው ሲኖዶስ ስድሣ  ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ እንደዚሁም በድጋሚ በካርቴጅ በ419 ዓ.ም የተሰበሰበው ሲኖዶስ )138 ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ ይህ ሲኖዶስ «የአፍሪካ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ» በሚል መጠሪያ ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሐዋርያውያነ አበው /Apostolic Fatheres/ የቤተክርስቲያንን አስተዳደርና የቤተክርስቲያንን ችግር በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ በመመርመርና አስፈላጊውንም በመወሰን ቤተክርስቲያንን መርተዋል፡፡ ያውም ከሰባ ዓ.ም ጀምሮ እስከ 313 ዓ.ም ድረስ የነበረው ጊዜ አሕዛብ በቁር የበዙ በትና በመንግሥት አስተዳደርም አጠቃላይ ሥልጣን ግን የጨበጡበት ዘመን ስለነበረ፤ በዚህ ዘመን ከፀረ እግዚአብሔርና ከፀረ ክርስትና ኃይሎች ጋር በመጋደል በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ስለ ሀልዎተ እግዚአ ብሔርና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው መሥዋዕት ሆነው የተሰውበት ዘመን ነበር፡፡ በመሆኑም ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት እየተባለ ይጠራል፡፡

ዓለም አቀፍ ሲኖዶሶች

ከዚህ በላይ ለማየት እንደተሞ ከረው በአካባቢ በሚገኙት አብያተ ክርስቲያናት ዙሪያ ወይም ውስጥ የቀኖና ወይም የዶግማ ችግሮች ሲከሰቱ በአቅራቢያ ሀገሮች ከሚገኙ ኤጲስ ቆጳሳት ሲኖዶሶች እየተጠሩ ለተነሡት ችግሮች መፍትሔ ይሰጡ ነበር፡፡

ነገር ግን በአካባቢ በሚደረጉት ሲኖዶሶች የማይፈቱ ከሆኑ በዚያኑ ጊዜ ዓለም አቀፍ ከሚባለው የዓለም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት የጋራ የሆነ ዐቢይ ዓለም አቀፍ ጉባኤ /Ecumerical council/ እያደረጉ ችግሮቹን በመመርመር መፍትሔ ይሰጡ ነበር፡፡

የመጀመሪያው የኒቂያ ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ በ325ዓ.ም ኒቂያ በተባለች ከተማ ከመደረጉ በፊት አርዮስና ኑፋቄአዊ ትምህርቱን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት አርዮስ በኖረበትና በተነሣ በት ሀገር በእስክንድርያ በመጀመሪያ በ320 ዓ.ም፤ ቀጥሎም በ321 ዓ.ም ሲኖዶስ ተደረገ፡፡ የዚያሲኖዶስ ሰብሳቢ የእስክንድርያ ሊቀ ጰጳስ የነበረው እለ እስክንድሮስ ዘእስክንድርያ ነበር፡፡ ችግሩ በዚያ ዓይነት ይፈታል ተብሎ ቢሞከርም ሰባት መቶ ደናግል፣ ዐሥራ ሁለት ዲያቆናት፣ ስድስት ቀሳውስት /የደብር አለቆች/ ከሦስት የሚበልጡ ኤጲስ ቆጶሳት ትምህርቱን ተቀብለው አርዮስን ስለደገፉ አርዮስ በሲኖዶሱ ምክር ሊመለስ አልቻለም፡፡ ስለዚህ ከአራት ዓመት በኋላ በሊቀ ኤጲስ ቆጶሳት እለእስክንድሮስ አስተባባሪነት በንጉሠ ነገሥቱ በቆስጠንጢኖስ ተባባሪነት 318 አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት በኒቂያ ከተማ በ325 ዓ.ም የሲኖዶስ ስብሰባ አድርገው ከኑፋቄው አልመለስ ያለውን እልከኛውን አርዮስንና ትምህርቱን አውግዘው ሃይማኖትን አጸኑ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በአንድ ልብ ሆነው «አንቀጸ ሃይማኖት /ጸሎተ ሃይማኖት/» የተባለውን የዶክትሪን ዐዋጅ አጸደቁ፡፡ ከሃያም ያላነሱ ቀኖናዎችን አጽድቀው አሠራጩ ፡፡

ከዚያም በመቀጠል ከሃምሳ ስድስት ዓመት በኋላ መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አምላክ መሆኑን የካዱ መናፍቃን /ሐራጥቃዎች/ /heretics/ ተነሥተው በምሥራቅ በኩል የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ባስቸገሩ ጊዜ በቁስጥንጥንያ ከተማ በ381 ዓ.ም ከመላው ዓለም አንድ መቶ ሃምሳ አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰበሰቡ፡፡ «መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ያነሰ ነው /ሕጹጽ ነው/» ብለው የተነሡትን መቅዶን ዮስንና ተከታዮቹን ተመክረውና ተለምነው ከክሕደታቸው ስላልተ መለሱ አወገዙአቸው፡፡ ትምህርታቸውንም በማውገዝ ውሳኔ አሳለፉ፡፡ በመቀጠልም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመመርኮዝ «መንፈስ ቅዱስ እንደ አብና እንደ ወልድ ፍጹም አምላክ መሆኑን፣ ጌታና ማኅየዊ እየተባለም ከአብና ከወልድ ጋር አንድ ባሕርይ ስለሆነ ከሁለቱ አካላት ጋር በአንድ መለኮት እንደ ሚመሰገንና እንደሚሰገድለት፤ እንዲሁም ከአብ ብቻ መሥረጹን ገልጸው ወሰኑ» ውሳኔውም ከኒቂያው አንቀጸ ሃይማኖት/ከጸሎተ ሃይማኖት/ ጋር ተጨምሮ እንዲጻፍ አደረጉ፡፡ በዚሁም መሠረት በአሁኑ ዘመን በመላው ዓለም በየቤተክር ስቲያኑ በተለያየ ቋንቋ የሚጸለየው ጸሎተ ሃይማኖት «የኒቂያ- ቁስጥ ንጥንያ አንቀጸ ሃይማኖት»/ Nicene-constantinople creed/ እየተባለ ይጠራል፡፡

ከቁስጥንጥንያው ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ በኋላ ሃምሳ ዓመታት ቆይቶ ንስጥሮስ የተባለ መናፍቅ ተነሣ ፡፡ እሱም የቁስጥንጥንያ ትርያርክ ነበር፡፡ ከ426ዓ.ም ጀምሮ በቁስጥንጥንያ ምስጢረ ሥጋዌን በማፋለስ «ክርስቶስ ሁለት አካላት፣ ሁለት ገጻት፣ ሁለት በመስተጻምር /በሲናፊያ/ አንድ የሆኑ ባሕርያት ያሉት ነው» እያለ አስተማረ፡፡ በዚህም መርሖ መሠረት «ቃለ እግዚአብሔር /ሎጎስ/ እና ክርስቶስ በመስተፃመር /በሲናፊያ/ አንድ ስለሆኑ ክርስቶስ አንድ ነው» ብሎ አስተማረ፡፡

ከዚሁም አያይዞ «ድንግል ማርያም እግዚአብሔርን ልትወልድ አትችልም፤ ከእርስዋ የተወለደው ክርስቶስ ነው፡፡ ስለሆነም እርስዋን ወላዲተ ክርስቶስ እንጂ ወላዲተ እግዚአብሔር /ወላዲተ አምላክ/ አንላትም» በማለት አስተማረ፡፡ በዚሁ ችግር ምክንያት በ431 ዓ.ም ከመላው ዓለም አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳትና ኤጲስ ቆጶሳት በኤፌሶን ተሰብስበው ሦስተኛውን ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ አደረጉ፡፡

ንስጥሮስን ሦስት ጊዜ ጠርተውት አልቀርብም ስላለ የጻፋቸውን መልእክታት ተመልክተውና ስሙን ጠርተው አወገዙት፡፡ ክርስቶስንም «ወልድ ዋሕድ፣ ፍጹም  አምላክ፣ ፍጹም ሰው፣ ከሁለት ባሕርይ / ከመለኮትና ከትስብእት/ አንድ ባሕርይ፣ አንድ አካል» መሆኑን የሚያረጋግጡትን የቅዱስ ቄርሎስን መልእክታት ተቀብለው አጸደቁ፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምንም «በአማን ወላዲተ አምላክ» መሆንዋን አረጋገጡ፡፡

በሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ዮሐንስ ዘአንጾኪያ እየተመራ ወደ ኤፌሶን የመጣው የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶሳት ቡድን ግን የንስጥሮስን ውግዘት ተቃወመ፡፡ በዚህ ምክንያት የአንጾኪያ ቤተክርስቲያን በኤፌሶን ከተሰበሰቡት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ተለየች፡፡ እስከ 433 ዓ.ም በእስክ ንድርያና በአንጾኪያ አብያተ ክርስቲያናት መካከል መለያየት ጠነከረ፤ የጠብ ግድግዳም ተመሠረተ፡፡ በ433 ዓ.ም ግን በንጉሠ ነገሥት ቴኦዶስዮስ ካልዕ አስታራቂነት ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት ታረቁ፡፡ በቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንደርያና በዮሐንስ ዘአንጾኪያ መካከልም ሰላም ተመሠረተ፡፡ በዚሁ ዕርቅ መሠረት አንጾኪያውያን አበው በኤፌሶን የተወሰነውን ውሳኔ ተቀበሉ፡፡ በንስጥሮስ መወገዝና መወገድም ተስማሙ፡፡ አንድነትም ተመሠረተ፡፡

ቅዱስ ቄርሎስ በ444 ዓ.ም ሲያርፍ በኋላ የሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ  የነበረው ዲዮስቆሮስ ዘእስክንድርያ ትርያርክ ሆኖ ተሾመ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በኋላ በ488ዓ.ም ከቁስጥ ንጥንያ በሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ፍላቭያን የሚመራ የአካባቢው ኤጲስ ቆጶሳት የተሳተፉበት ሲኖዶስ /Local Synods/ ተደረገ፡፡ ወደዚህም ሲኖዶስ አውጣኪ ተከሶ ቀረበና ተወገዘ፡፡ እርሱም ወደ ሮምና ወደ እስክንድርያ ትርያክ«አላግባብ ተወገዝሁ» ብሎ አቤቱታ ጻፈ፡፡

«የአውጣኪን ጉዳይ ለመመርመርና ተረፈ ንስጥሮሳውያንን ለማስወገድ» በሚል አጀንዳ ለሁለተኛ ጊዜ በ449 ዓ.ም በኤፌሶን ሲኖዶስ ተደረገ፡፡ በስብሰባውም አንድ መቶ ሠላሳ ስአምስት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰበሰቡ፡፡ የሲኖዶሱ ሊቀ መንበር ትርያክ ዲዮስቆሮስ ሆነ፡፡ በአጀንዳው መሠረትጉዳዮች ተመረመሩ፡፡ አውጣኪንም መረመሩት፡፡ ሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ፍላቭያኖንስና ፌኦዶሪትን ግን ጉባኤው መርምሮ መንፈቀ ንስጥሮሳውያን ሆነው ስላገኛቸው በጊዜያዊ ውግዘት ተቀጥተውና ታስረው እንዲቆዩ ተደረገ፡፡ የፖፕ ልዮን ጦማረ ሃይማኖትም ቀርቦ በዲዮስቆሮስና በሌሎች የጉባኤው አባላት ተመርምሮ ከንስጥሮስ ትምህርት ጋር ተዛምዶ ስለተገኘ በጦማሩና በጦማሩ ባለቤት ላይ ውግዘት አከል ተግሳጽ እንዲተላለፍባቸው ተደረገ፡፡ ፖፕ ልዮን ግን ይህንን ታሪክ ሰምቶ በዲዮስቆሮስ ጥርሱን ነከሰ፡፡

ጉባኤውንም «የወረበሎች ጉባኤ» /Synodd of listriks/ ብሎ ጠራው፡፡ ከዚህ ንዴት የተነሣ  በሁለተኛው ዓመት በ451 ዓ.ም በኬልቄዶን ጉባኤ እንዲደረግ ተወሰነ፡፡ በዚህ ጉባኤስድስት መቶ ሠላሳ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በልዮን መልእክተኞች እየተመሩ ቅዱስ ዲዮስቆሮስን ከንጉሡ ጋር ተሻርከው ከመንበሩ አወረዱት፡፡ ታስሮም በደሴተ ጋግሪ ሦስት ዓመት ተቀመጠ፡፡ ከዚያም እንዳለ በእስራትና በበሽታ ምክንያት 454 ዓ.ም ዐረፈ፡፡ከቅዱሳን ሐዋርያት ዘመን ጀምሮ እስከ አምስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ያየነው ታሪክ እንደሚያስረዳን ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያን መሪ እንደሆነ ነው፡፡ ቤተክርስቲያንምከተጠቀሰው የመጀመሪያው ዘመን ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ መለኮታዊ አገልግሎትዋን ስታካሒድ የኖረችው በመንፈስ ቅዱስ በሚመራው በቅዱስ ሲኖዶስ በመመራት ነው፡፡ በቤተክርስቲያናችን ትውፊት መሠረትም የሐዋርያትንና የአርድእት ቀኖናዎች የሊቃውንትም ጭምር ሲኖዶስ /መጽሐፈ ሲኖዶስ/ እየተባለ ይጠራል፡፡ ከዚህ በላይ እንደተ መለከትነውና እንደምናውቀው በአካባቢ የተነሡትን የሃይማኖትም ሆኑ የቀኖና ችግሮች በመጀመሪያ በአካባቢው ሀገሮች ባሉት ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ ወሳኝነት ይፈቱ ነበር፡፡ ከእነርሱም አቅም በላይ ሆነው የተገኙ ችግሮች ደግሞ «ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ» /Ecumerical Synods/ እየተጠራ ሲወሰን እንደነበረ ተመልክተናል፡፡

ከዚያም ሌላ በየትኛውም ሀገር የምትገኘው የክርስቶስ ቤተክርስቲያን /Local Synods/ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ አንድ ማእከል አንድ ሲኖዶስ ብቻ እንዳላት ተገንዝ በናል፡፡ ለምሳሌ የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን በአንድ የኢየሩሳሌም ቅዱስ
ሲኖዶስ፣ የእስክንድርያ ቤተክርስቲያን በአንድ የእስክንድርያ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የቁስጥንጥንያ ቤተክርስቲያን በአንድ የቁስጥንጥንያ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የግሪክ ቤተክርስቲያን በአንድ የግሪክ ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ ሲመሩ መኖራቸውን እናውቃለን፡፡

ለአንዲት ነጻ ሀገር አንድ ርላ ሜነት /One Panriament/ ብቻ እንዳላት ሁሉ ለአንዲት ነጻ ቤተክርስቲያንም አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ /Autocephalous Church/ ብቻ እንዳላት የታወቀና የተረጋገጠ ነው፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ስንል /በተለይ ሀገራዊ Local/ የሚከተሉትን ነገሮች ይይዛል፡-
– ኤጲስ ቆጶሳት
– የታወቀ ሕጋዊ መንበር
– ታሪካዊና ሕጋዊ መሠረት
ለምሳሌ የግብፅን ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ብንመለከት
– ወደ ሃምሳ የሚጠጉ ኤጲስ ቆጶሳት
– የእስክንድርያ /የቅዱስ ማርቆስ/ መንበር
– በታሪክ የታወቀና ቅዱስ ሲኖዶሱ ያጸደቀው ሕግ አላቸው

 የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ፦

–    ኤጲስ ቆጶሳት
–    የአዲስ አበባ መንበር /መንበረ ፓትርያክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም የሚገኝ/
በቤተክርስቲያን ሕግ የጸደቀ ከመነሻውም /ሲኖዶስ በኢትዮጵያ ሲጀመር የነበረ ሕግ አላት፡፡
 

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም (ክፍል ሦስት)

ዲ/ን ዮሐንስ ልሳነወርቅ

ግንቦት 4፣ 2003ዓ.ም

ከክፍል ሁለት የቀጠለ

5.የሥጋ(ሰውነት) ክብር (The value of the Body)

ቅዱስ ኤፍሬም የሥጋን ክብር ለመንቀፍ  ከሚሹ ከተወሰኑ የቀድሞ የክርስትና ልማዶች መገለጫ ከሆኑት ከፕላቶናዊ ወይም ከምንታዌ ዝንባሌዎች  ፣  በእጅጉ የራቀ ነው። ለቀና አመለካከቱ መነሻው ነጥብ ሥጋ ከእግዚአብሔር ፍጥረታት መካከል ስለሆነ ሊጠላ አይገባዉም የሚል እውነታ ነው፤ በየትኛዉም መንገድ  ክፉ ተደርጎ ከሚታሰበው አስተሳሰብ  የራቀ ይሁን። ግና በተጨማሪ ቅዱስ ኤፍሬም ሦስት ጠቃሚ ግንዛቤዎች አሉት።

የመጀመሪያው የራሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሥክርነት ነው። 1ቆሮ.619 ላይ ያለውን በመተርጎምሰውነታችሁ ከእናንተ ጋር የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደሆነ አታውቁምን?” ቅዱስ ኤፍሬም እግዚአብሔር ራሱ ሰውነትን ለቅድስት ሥላሴ ማደሪያ በማድረግ የሰጠውን ክብር ይጠቁማል።(የቅ/ኤፍሬም አንድምታ በቅ/ጳውሎስ መልእክታት ላይ ገጽ 62) በኋላም 2ቆሮ.5 ያለውን ሲተረጉም እንዲህ ይላልሰውነታችን ለእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያነት የተገባ እንደሆነ ሁሉ በመጨረሻም ለዘለአለማዊ ክብር የተገባ አድርጎታል።”(የቅ/ኤፍሬም አንድምታ በቅ/ጳውሎስ መልእክታት ላይ ገጽ 96) የሰው ሰውነት በጽዮን ተራራ የነበረውን ቤተ መቅደስ በመተካት አዲሱ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆነ ቅዱስ ኤፍሬም በማንኛዉም ቦታ ይናገራል። (Heresies 42:4)

 

ሁለተኛም እግዚአብሔር ሥጋን የመዋሐዱ እውነታ ስለ ሥጋ ርኩሰት ወይም ለሥጋ አይገባም የምንለው ምንም ነገር እንደሌለ ያመለክታል።(Nativity 9:2) በመጨረሻም ቅዱስ ቁርባን ለቅዱስ ኤፍሬም ስለ ሥጋ ክብር ተመሳሳይ መረጃን ይሰጠዋል። በሚከተለው ጽሑፍ በቅዱስ ቊርባን እያመኑ ነገር ግን  ሰውነትን ርኩስ አድርገው የሚቆጥሩት የክርስቲያን ቡድንን ይሞግታል።

ጌታ ሥጋን እንደ ርኩስ፣ የተጠላና ስሑት

አድርጎ ወቅሶ ቢሆን ኖሮ

ስለዚህ የድሳነት ሕብስቱ ጽዋውም ለእነዚህ መናፍቃን

የተጠላና ርኩስ መሆን አለበት፤

ራሱን በሕብስቱ ውስጥ የሰወረ ሆኖ እያለ

ያ ሕብስት ከዚያ ደካማ ሰውነት ጋር የተዛመደ መሆኑን እያየ

ክርስቶስ ሰውነትን እንዴት ሊንቅ ይችላል።

እንዲሁም እርሱ በማይናገር ሕብስት ተደስቶ ከነበረ

በሚናገርና አመክንዮን ገንዘብ ባደረገ በሰውነትማ

ምን ያህል እጅግ ይደሰት ይሆን!(Heresies 47:2)

እግዚአብሔር የተቀደሰውን ምሥጢር ሥጋዉንና ደሙን በሰው ሰውነት እንዲመገቡት በመፍቀዱ በትክክል ተመሳሳይ ነገር ተጠቁሟል።

ሰውነት ከክፉ ነገር የተገኘ ቢሆን ኖሮ

እግዚአብሔር  ምሥጢራቱን  በሰውነት ላይ ባላሳደረ ነበር።(Heresies 43:3)

ስለዚህም በቅዱስ ኤፍሬም ዓይን ሥጋና ነፍስ እኩል አስፈላጊነት አላቸው፤ የሚጫወቱት የተለያየ ሚና አላቸው።

ሥጋ ላንተ ምሥጋናን ያቀርባል

ምክንያቱም ላንተ መኖሪያ ይሆን ዘንድ ፈጥረኸዋልና፤

ነፍስ አንተን ታመልካለች

ምክንያቱም በመምጣትህ ለሙሽሪትነት አጭተሃታልና። (Heresies 17:5)

ሰውነት የሰርግ ቤትን ሲሆን ሙሽሪት ነፍስ ግን ሰማያዊ ሙሽራን ትገናኛለች።

6.በመንፈሳዊ ትምህርት ጥያቄን ለመጠየቅ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች (The prerequisities for Theological Enquiry)

መንፈሳዊ ትምህርት እንደሌሎች ማናቸውም የህሊና ጥያቄዎች ጥያቄ በሚያቀርበው ሰው ባለው የህሊና ዝንባሌ መሠረት ሦስት የተለያዩ  መልኮች ሊኖረው ይችላል።

በመጀመሪያ ደረጃ ህሊና የጥያቄውን አካል ለመጫንና ለመቆጣጠር ሊፈልግ ይችላል። እንዲህ ዓይነቱ ዝንባሌ ከፍራንሲስ ባኮን ዘመን ጀምሮ በብዛት ለሳይንሳዊና ሌላ ጥያቄ መገለጫ ሆኗል። በትክክልም ይሁን በስህተት ቅዱስ ኤፍሬም ይኽ በዘመኑ ለነበሩ ብዙ የኑፋቄ አሳቢዎች እንደ ዋና ዝንባሌ እንደሆነ አስተውሏል፤በተለይ በመንፈሳዊ ትምህርት መስክ ውስጥ እንዲህ ዓይነት የህሊና ኩራት ለእርሱ ተቀባይነት የሌለው ነው።

ለሁለተኛው አቀራረብ በአጀማመሩ እጅግ ተቀባይነት ያለው ይመስላል፤በአሁኑ ዘመን የመንፈሳዊ ትምህርት ጥያቄ መለያ የሆነ መልክ አለው። እዚህ ላይ ህሊና በተቻለ መጠን ከተጽእኖ ነጻ በሆነ መልኩና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የጥያቄውን አካል ለማጥናት ይዘጋጃል። በብዙ አቅጣጫዎች ፍሬያማ የሆነ አቀራረብ ነው፤እንዲሁም ይኽ አቀራረብ ቅዱስ ኤፍሬም የሞከረው መሆኑን ያመለክታል።ግና …

 

ወደ ትምህርትህ መልሰኝ ከኋላ ልቆም ፈልጌ ነበር

ግና እጅግ ደሀ ወደ መሆን እንደመጣሁ አየሁ

ነፍስ ካንተ ጋር ከመነጋገር በቀር

ሌላ ምንም ጥቅም አታገኝምና። (Faith 32:1)

የቅዱስ ኤፍሬም የሆነው ሦስተኛው አቀራረብ ታማኝነት ነው፤ከሁሉም በላይ ለፍቅርና ለአድናቆት የሚደረግ ታማኝነት። ነገር ግን ሁለተኛው አቀራረብ ከህሊና ወደ ተጠያቂው አካል የሚደረግ የአንድ አቅጣጫ እንቅስቃሴ ነው ፤ይኽ ሦስተኛው አቀራረብ በሁለት አቅጣጫ የሆነና ቀጣይነት ያለው ሱታፌ ነው።

ስለ ፈጣሪ እውነተኛነት የሰው እውቀትሊያድግ የሚችለው በእንዲህ ዓይነት የፍቅር መስትጋብር ብቻ ነው።

 

በዚሁ መዝሙር ላይ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ በማለት ይቀጥላል።

አንተን በማሰብ በተመሰጥኩ ጊዜ

ካንተ ፍጹም ዋጋን አገኛለሁ

ስላንተ ባሰብኩበት በየትኛዉም አቅጣጫ

ካንተ ምንጭ ይፈስሳል

እኔ ምንጩን ልይዝበት የምችልበት ምንም መንገድ የለም

ጌታ  ያንተ ምንጭ ስላንተበማሰብ ከማይጠማ ሰው የተሰወረ ነው

አንተን ለማይቀበል ሰው ያንተ ዋጋ ባዶ ይመስለዋል

ፍቅር ያንተ ሰማያዊ ግምጃ ቤት ባለቤት ነው። (Faith 32:2-3)

ስለዚህ እግዚአብሔርንና ስለእኛ የተፈጠረውን ዓለም የምንረዳበት መንገድ በእኛ መሠረታዊ ዝንባሌና አቀራረብ የተደገፈ ነው፤ከእኛ ከራሳችን እነደተለዩ የጥያቄ አካላት የምንረዳቸው እንደሆነ (እነርሱን ለመጫን መሞከር እንችላለን ወይም በአማካይ ከእኛ ጋር እንዳሉ መረዳትእንችላለን) ወይም ራሳችንን ሊቀየር በማይችል መልኩ በጥያቄያችን አካል ላይ እንደተሳተፍን ማየታችን እንዲሁም በምሥጢሩ ለመሳተፍ ፈቃደኞች መሆናችን ይደገፋል። ቅዱስ ኤፍሬም ይኽ የመጨረሻው መንገድ ብቸኛው በእውነት ተቀባይነት ያለው መንገድ ብቻ ሳይሆን የትኛውም የእግዚአብሔር እውቀት ሊሻበት የሚችል ብቸኛው መንገድ እንደሆነ አይጠራጠርም።

ከዚህ ከመነሻው የታማኝነትና ሱታፌ ዝንባሌ ጋር እኩል ጠቀሜታ ያለው የመደነቅና የመገረም ስሜት ነው።እንዲህ ዓይነቱ የመደነቅ ሰሜት በቅዱስ ኤፍሬም በየትኛዉም ጽሑፎች ላይ የሚገኝ ነው።እንዲህ በማለት ይናገራል፤”በሕይወት በሚያጋጥሙ ቀላል ነገሮች አስተሳሰባችን አድናቂ እንዲሆን ያደረገ እርሱ(እግዚአብሔር) ምስጉን ነው።”(Faith 43) ግና ከሁሉም በላይ ተደናቂ የሆነው  ሰውን በመውደድ በእግዚአብሔር ከፍተኛ መገለጥ እርሱ ራሱ ከሥጋ ጋር በተዋሐደ ጊዜ  ነው።(Fast 3:6, Heresies 35:7) የእግዚአብሔር ወደ ትቢያ መውረድ (መምጣት)  የሚያስደንቅ ነው።(Faith 46:11)

መደነቅ ወደ ፍቅርና ወደ ምሥጋና ያደርሳል፤እንዲሁም በፍቅራችን መጠን በማመሥገን በኩል መለኪያ የሌለውን ሕይወት እናገኛለን።(Nisibis 50:5) እንዲያዉም ባለማመስገን መኖር ሙት ሆኖ እነደ መኖር ነው።

 

በምኖርበት ጊዜ ምሥጋናን አቀርባለሁ

እኔ ህልውና እንደሌለኝም አይደለም

በሕይወት ዘመኔ ምሥጋናን አቀርባለሁ

በሕያዋን መካከል እንደሞተ ሰውም አልሆንም

ሥራ ፈትቶ የሚቆም ሰው ሁለት ጊዜ የሞተ ነው

ፍሬ ማስገኘት የተሳናት ምድርም የሚያዘጋጃትን ትከዳዋለች። (Nisibis 50:1)

እንዲሁም ያለ ፍቅር እውነት ሊደረስበት አይችልም።

እውነትና ፍቅር ሊለያዩ የማይችሉ ክንፎች ናቸው

እውነት ያለ ፍቅር መብረር እንደማይችል ሁሉ

እንዲሁም ፍቅር ያለ እውነት ወደ ላይ ሊወነጨፍ አይችልም

የስምምነት ቀንበራቸው አንድ ነው።(Faith 20:12)

የዚህ ግጥም ክፍል ሦስተኛ ስንኝ ለቅዱስ ኤፍሬም ተጨማሪ ጥቅም ወዳለው ጉዳይ ያመጣናል፤ለማንኛዉም ዓይነት መንፈሳዊ ጥያቄ መነሻው ነጥብ በሰው ህሊና የትኞቹ የመንፈሳዊ ትምህርት ክፍሎች ሊመረመሩ እንደሚችሉና የትኞቹ የመንፈሳዊ ትምህርት ክፍሎች ሊመረመሩ እንደማይችሉ ማወቅ ነው፤በሌላ አነጋገር አንድ ሰው በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን የነገረ ህላዌን ልዩነት የት ላይ ማስቀመጥ እነዳለበት በሚገባ ማወቅ አለበት ።ይኽም ማለት አንድ ሰው ከኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርት አቋቋም ካልተነሳ ከመጀመሪያው ጀምሮ ስህተትን ይሠራል፤ስህተት የሆኑ የመነሻ ግንዛቤዎችም ወደ ተጨማሪ ስህተት ብቻ ይመራሉ። ይኽም ቀድመን እንዳየነው ከተለያዩ የአርዮሳዊ አቋቋም ጋር ቅዱስ ኤፍሬም መሠረታዊ ቅራኔ ውስጥ የሚገባበት ጉዳይ ነው። በተመሳሳይ ቅዱሳት መጻሕፍት በአግባቡ ሊተረጎሙ የሚችሉት በኦርቶዶክሳዊ እምነት ብርሃን ብቻ ነው።

ሁሉን ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚከፍቱ የዶግማ ቁልፎች

በእኔ ዓይን ፊት የሥነፍጥረትን መጽሐፍ ፣

የታቦቱን ግምጃ ቤት፣የህጉን ዘውድ ከፍተዋል

ከሌሎች መጻሕፍት ሁሉ በራቀ በትረካው  ፈጣሪን የተረዳና

ሥራዎቹንንም ያስተላለፈ ቅዱስ መጽሐፍ ነው።

ሁሉንም የእርሱ የእጅ ሥራዎችን በማስተዋል

መጽሐፍ ቅዱስ የሥራዎቹን አካላት ገልጿል ። (Paradise 6:1)

ይቆየን…