ማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ቢሮ ያከናውናቸውን ተግባራት አስታወቀ።

በይብረሁ ይጥና

ሥራዎቹንም የሚያሳይ ዓውደ ጥናት በኢትዮጵያ የስብሰባ ማእከል እንደሚካሔድ ተገልጧል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ  መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውንና በቀጣይ ሊሠራ ያቀዳቸውን ተግባራት አስታወቀ፡፡
 
የፕሮግራሙ ማስተባበሪያ ቢሮ ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ እንዳስታ ወቁት በ2001 እና 2002 ዓ.ም ፕሮግራሙን ለምእመናን የማስተዋወቅና የመቅረጽ ሥራ ተሠርቶ በተወሰነ ደረጃ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡

በ2003 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት ለትምህርትና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ክፍል የተነደፈውን ፕሮግራም እንዲያውቀው ተደርጓል፡፡ መምሪያውም ለፕሮግራሙ ማስፈጸሚያ የሚሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ተገብቷል፡፡

እንደዚሁም ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መምሪያ ጋር በመሆን ፕሮግራሙ ተግባራዊ ከሚደረግባቸው ሃያ ሀገረ ስብከቶች ለተውጣጡ ሥራ አስኪያጆችና ሰባክያነ ወንጌል በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ፕሮግራሙን የማስተዋወቅ ሥራ ከተሠራ በኋላ ለተግባራዊነቱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ደብዳቤ ተበትኗል ሲሉ አመልክተዋል፡፡

ፕሮግራሙ በዋናነት የሚያተኩረው ስብከተ ወንጌልን ለምእመናን ማዳረስ ሲሆን የንድፈ አሳቡ መነሻ ደግሞ በተለይ በጠረፋማና ገጠራማ አካባቢ ለሚገኙ ምእመናን ጉባኤ ማካሔድና ሰባኬ ወንጌል ከመመደብ ጀምሮ ለአካባቢው ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር አባላትም የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ነው፡፡

ፕሮግራሙ በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ ዐርባ አምስት ሀገረ ስብከቶች መካከል ችግሩ ይበልጥ ይከፋል ተብሎ በታመ ነባቸው ሃያ ሀገረ ስብከቶች መሆኑን አቶ ዳንኤል  ጠቁመው፣ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል በሚገኙ ጠረፋማና ገጠር አካባቢዎች ልዩ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል፡፡

የፕሮግራሙ ማስተባበሪያ ቢሮው በ2003 ዓ.ም እሠራቸዋለሁ ብሎ ካቀዳቸው ዕቅዶች መካከል፤ ዐሥር ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ፣ ሃያ የሕዝብ ጉባኤያትን ማካሔድ፣ በተለያዩ ቋንቋዎች ዐሥራ ሁለት የስብከame=”Medium List 2 Accent 5″/> » አለው፡፡

ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከእስራኤል ሽማገሌዎች ጋር በኮሬብ በነበረው ዐለት ያደረገው ስብሰባ በሐዲስ ዘመን ከተሰበሰቡት ሲኖዶሶች /ጉባኤዎች/ ጋር ይመሳሰላል፡፡

ሙሴ በሌላ ጊዜ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ከእስራኤል ሽማግሌዎችና ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ለመውጣት ያደረገው ስብሰባ ከሲኖዶስ ጋር የሚመሳሰል ነው፤/ዘፀ.19፡1-25/፡፡ በተለይም የእግዚአብሔርን ክብር ያዩ ዘንድ ሙሴና የእስራኤል ሽማግሌዎች፣ ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ወጥተው በሩቅ ቆመው ለእግዚአብሔር ክብር ስግደት በማቅረብ የተሰበሰቡት ስብሰባ ሲኖዶስን የሚመስል ነው እንላለን፡፡ /ዘፀ.24111/፡፡

በሌላ በኩል የእስራኤል ልጆች ወደ ምድረ ከነዓን ለመግባት በሲና ምድረ በዳ በሚጓዙበት ወቅት የሚበላ ዳቦና የሚጠጣ ውኃ ሲያጡ ወደ ሙሴ ይጮኹ ነበር፡፡ ሙሴም የሕዝቡን ችግር ለእግዚአብሔር እያሰማ ሕዝቡ ማግኘት የፈለጉትን ያሰጣቸው ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት አንድ ቀን የእስራኤል ልጆች እጅግ ጎምጅተው «የምንበላው ሥጋ ማን ይሰጠና? በግብፅ ሳለን ያለዋጋ ዓሣውንም፣ ዱባውንም፣ በጢሁንም፣ ነጭ ሽንኩርቱንም፣ ቀይ ሽንኩርቱንም እንደ ልብ እንበላ ነበር፡፡ አሁን ግን ሰውነታችን ደረቀች፣ ዐይናችንም ከዚህ መና በቀር የሚያየው የለም» ብለው አጉረመረሙ፡፡


በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ሙሴን ጠርቶ ከሕዝቡ ሰባ ሽማግሌዎችን የሕዝቡ አለቆችና ሸማግሌዎች ይሆኑ ዘንድ መርጦ ወደ መገናኛው ድንኳን እንዲያቀርባቸው አዘዘው፡፡ ሙሴም እግዚአብሔር እንዳዘዘው ሰባዎቹን ሰዎች ከሕዝቡ መርጦ ወደ ማደሪያው ድንኳን አቀረባቸው፡፡ እግዚአብሔርም ለሙሴ ከሰጠው መንፈስ ወስዶ በእነርሱ አሳደረባቸው፡፡ መንፈስም
/መንፈስ ቅዱስ/ በሰባው ሰዎች ላይ ባደረ ጊዜ ትንቢት ተናገሩ፡፡ በዚያው ወቅትም ከሰባው ጋር ተመርጠው ወደ ድንኳኑ ሳይመጡ በሕዝቡ ሰፈር የቀሩ ኤልዳድና ሞዳድ የተባሉ ሰዎች ነበሩ፡፡ መንፈስም ባሉበት ወረደባቸው፡፡ እነርሱም ትንቢትን ተናገሩ፡፡ ከዚያ በኋላ ከእነዚህ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎች ጋር ሙሴ የሕዝቡን ችግር እንዲሸከም ታዘዘ፡፡ ከዚያም እግዚአብሔር ከእነዚህ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎች /72 ሊቃናት/ ፊት በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል ልጆች ሥጋ አዘነበላቸው፤/ዘኁል.11፥115/፡፡

በመሆኑም የእነዚያ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎችና የሙሴ በማደሪያው ድንኳን መሰብሰብና የመንፈስ ስጦታን መቀበል በዘመነ ሐዲስ ከተደረጉት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤዎች ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ኢያሱም ከሙሴ ዕረፍት በኋላ ሕዝበ እስራኤልን ለመምራት እንዲችል በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሙሴ ኢያሱን በማኅበሩ ሁሉ ፊት /በጉባኤ ፊት/ በአንብሮተ እድ እንደሾመው መጽሐፍ ይነግረናል፤ /ዘኁል.27፥1523/፡፡ ስለሆነም የኢያሱ በጉባኤው ፊት መሾም ሰባቱን ዲያቆናት በአንብሮተ እድ ከሾሙት ከሐዋርያት ጉባኤ ጋር የሚመሳሰል ነው፤ /ሐዋ.6፥16/፡፡

እንደዚሁም በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ በምዕራፍ 2፥12 እና በምዕራፍ 4፥30 ላይ እንደተገለጸው፤ ደቂቀ ነቢያት በነቢዩ በኤልሳዕ ፊት ያደረጉት ስብሰባ ከቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ስለዚህ በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳን ሐዋርያት ካደረጉት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በፊት በዘመነ ብሉይ በሕዝበ እስራኤል መካከል የተከሰተውን ችግር ለማስወገድና ሕዝበ እስራኤንም በጉባኤ ውሳኔ ለመምራት ቅዱስ ሲኖዶስን የመሰሉ ስብሰባዎች መደረጋቸውን በአጭሩ ለማስረዳት ተሞክሮአል፡፡

ሲኖዶስ ዘቅዱሳን ሐዋርያት

የቤተክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስረዳን የክርስቶስን ቤተክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ መምራት የጀመሩት ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በሥምረት ለመምራት በዘመናቸው የተለያዩ ጉባኤዎችን እንዳደረጉ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ይኸውም በአስቆሮታዊው ይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ ለመምረጥ ያደረጉት ስብሰባ ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞተና ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ቅዱስ ሉቃስ እንደመሰከረው ለደቀመዛሙርቱ አርባ ቀን እየተገለጸላቸው፣ ስለእግዚአብሔር መንግሥትም እየነገራቸው /እያስተማራቸው/ በብዙም ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖና ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን ለእነርሱ እየታያቸው ቆየ /ሐዋ.1፥1-4/፡፡

ስለ እርሱ የተጻፉትንም መጻሕፍት ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፡፡ እንዲህም አላቸው፣ «ክርስቶስ መከራ ይቀበላል፣ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ይነሣል፣ በስሙም ንስሐና ኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል» ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል፡፡ እናንተም ስለዚህ ምስክሮቼ ናችሁ፡፡ እነሆም «አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ብሎ አዘዛቸው፡፡ ከዚያም ወደ ቢታንያ ወደ ደብረ ዘይት አወጣቸው፣ እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው፣ ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ፣ ወደ ሰማይም ዐረገ» /ሉቃ.24፥41-53/፡፡ እነርሱም ጌታ ወዳረገበት ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች /ሁለት መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ፡፡ ደግሞም እንዲህ አሉአቸው «እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ ትኩር ብላችሁ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችሁ? እነሆ ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁ እንዲሁ ይመጣል» ሲሉ ነገሩአቸው፡፡ /ሐዋ.1፥6-11/፡፡

ሐዋርያትም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፡፡ ከዚያም ዘወትር እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያወደሱ /እየባረኩ/ በመቅደስ /በጽርሐ ጽዮን/ ኖሩ /ሉቃ.24፥50/፡፡ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ በአጠቃላይ መቶ ሃያ ሰዎች ያህል ባሉበት ቅዱስ ጴጥሮስ ተነሥቶ በይሁዳ ቦታ ሌላ ሰው መተካት እንዳለበት ንግግር አደረገ፡፡ «ወንድሞች ፥ሆይ፣ ኢየሱስን ለያዙት መሪ ስለሆናቸው ስለ ይሁዳ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው ይፈጸም ዘንድ የተገባ ሆነ፤ እርሱም ከእኛ ጋር ተቆጥሮ ነበርና፣ ለዚህም ሐዋርያዊ አገልግሎት ታድሎ ነበርና» ብሎ በመናገር ስለ አስቆሮቱ ሰው ስለ ይሁዳ ዐመፅና አሟሟት ገለጻ አደረገ፡፡ ከዚያም ይሁዳን ስለሚተካው ሰው አስመልክቶ «ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ እኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፣ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣ ኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል» ብሎ ገለጸ፡፡

ወዲያውም በጉባኤው ስምምነት መሠረት የመቶ ሃያው ማኅበር አባላት ከነበሩት መካከል በርያስ የተባለውን ዮሴፍንና ማትያስን፣ሁለቱን በመካከል አቆሙአቸው፡፡ ስለ እነርሱም ሲጸልዩ፤ «የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ፣ ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ይሔድ ዘንድ በተዋት በዚህች አገልግሎትና ሐዋርያነት ቦታን እንዲቀበል የመረጥኸውን ከእነዚህ ከሁለቱ አንዱን ሹመው» ብለው ጸለዩ፡፡ ቀጥሎም ዕጣ ተጣጣሉላቸው፤ ዕጣውም ለማትያስ ወደቀ /ወጣ/፡፡ እርሱም ዐሥራ አንዱ ሐዋርያት ጋር ተቆጠረ» /ሐዋ.1፥15-26/፡፡

ማትያስን መርጠው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንዲሾመው ከጸለዩ በኋላ ቁ ሩ ከሰብዐ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የነበረው ረድእ ማትያስ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተሹሞ ከቀሩት ሐዋርያት ጋር ገብቶ ተቆጠረ፡፡ በዚህ ሁኔታ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ከአርያም /ከሰማይ/ የሚላክላቸውን ኃይል ማለት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ደጅ እየጠኑና እየተጠባበቁ በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ሰነበቱ፡፡ በዓለ ሃምሳም የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜ ጌታ ባረገ በዐሥረኛው ቀን ሁሉም በአንድነት አብረው እየጸለዩ ሳለ ድንገት እንደሚነጥቅ አውሎ ነፋስ ከሰማይ ወደ እነርሱ ድምፅ መጣ፡፡ ተቀምጠው የነበሩበትንም ሁሉ ሞላው፤ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች /የእሳት ላንቃ/ የመሰሉ ታዩአቸው፤ በእያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጠባቸው፣ መንፈስ ቅዱስም ይናገሩ ዘንድ እንደሰጣቸው በልዩ ልዩ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር፤ /ሐዋ.2፥1-5/፡፡

በዚህ ጊዜ ጌታችን ከትንሣ ኤው በፊት «እኔ በአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ /ጰራቅሊጦስ/ ከአብ የሚወጣ /ዘይሠርጽ/ የጽድቅ /የእውነት/ መንፈስ በመጣ ጊዜ ስለ እኔ ይመሰክራል፣ እናንተም ደግሞ ከመጀመሪያ ጀምሮ ከእኔ ጋር ኖራችኋልና ትመሰክራላችሁ» ብሎ የተናገረው ተስፋ ተፈጸመ፡፡ ደግሞም ወደ ሰማይ በሚያር ግበት ወቅት «እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ» ሲል የሰጠው ሰማያዊ ተስፋ ተፈጸመ፤ /ሉቃ.24፥49፤ሐዋ.2፥43/፡፡

ከዚህ በላይ እንዳየነው ከበዓለ ሃምሳ ዋዜማ ጀምሮ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን የተካሔደው የመጀመሪያው የሐዋርያትና የሰብዓ አርድእት ጉባኤ እጅግ በጣም ታላቅ ጉባኤ ስለነበረ የመጀመሪያው የሐዋርያት ሲኖዶስ ሊባል ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም፦

1. ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም የነበረችበት ጉባኤ በመሆኑ፤
2. ቅዱስ ማትያስን የመረጠና የሾመጉባኤ በመሆኑ፤
3. ለሐዋርያትና ከእነሱ ጋር በጸሎት ተሰብስበው ለነበሩት ሁሉ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ጉባኤ በመሆኑ፤
4. በዚያው ቀን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በመውረዱ ምክንያት በሐዋር ያት ስብከት ሦስት ሺሕ የሚያህል ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የቤተክርስቲያን አባል የሆነበት ቀን በመሆኑ ጉባኤው የቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ ይገባል፡፡ በመሆኑም  ቤተክርስቲያን ታሪክ የቅዱስ ሲኖዶስ ታሪካዊ አመሠራረት ከዚህ ቀዳሚው ጉባኤ መሆኑ የሚያከራክር አይደለም፡፡ በሌላ መንገድም በቤተክርስቲያን ታሪክ እንደተመዘገበው ከሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው በተለያዩ ቦታና ዘመን የተደረጉ የአህጉረ ስብከት /Regionsl or local/ ሲኖዶሶችና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ ሲኖዶሶች መሠረታቸው የኢየሩሳሌሙ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ ነው ቢባል እርግጥ ነው፡፡

ሁለተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ

ሁለተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ የሚገባው ጉባኤ፤ ራሳቸው ሐዋርያት ተሰብስበው የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን በአንብሮተ እድየሾሙት ዐቢይ ሲኖዶስ ተደርጎ እንደነበረ መጽሐፍ ያረጋግጥልናል፡፡ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት /ደቀመዛሙርት/ ምእመናንን በሙሉ ጠርተው፤ «እኛ የእግዚአብሔርን ቃል /ወንጌልን/ ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም፡፡ ወንድሞች ሆይ በመልካም የተመሰከረላቸውን፣ መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፣ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፣ እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን» ብለው ገለጹላቸው፡፡ ይህም ቃል /ንግግር/ ሕዝቡን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፡፡ ስለዚህም እምነትና መንፈስ ቅዱስም የመላበትን ሰው እስጢፋኖስን፣ ፊልጶስንም ጵሮኮ ሮስንም፣ ኑቃሮናንም ጰርሜናንም መረጡ፡፡ በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው ሐዋርያት ከጸለዩ በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው /ሐዋ. 6፥1-7/፡፡

ከላይ እንደተገለጸው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ከአርድእትና ከምእመናኑ ጋር ተሰብስበው ከተወያዩ በኋላ፤ ሐዋርያት በወሰኑት ውሳኔ ሕዝቡ በሙሉ ተደስተው ሰባቱን የቤተክርስቲያን አገልጋዮች መርጠው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አቅርበው የሾሙት ጉባኤ በመሆኑም ጉባኤው ከወሰነው ታላቅ ቁም ነገር የተነሣ  «ሲኖዶስ» ተብሎ ሊጠራ ይችላል፡፡ ነገር ግን እንደሚታወቀው በቤተ ክርቲያን ታሪክ መሠረት በተለምዶ የመጀመሪያው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ወይም የመጀመሪያው ሲኖዶስ ተብሎ የሚጠራው በኢየሩሳሌም 50/51 ዓ.ም የተደረገው ጉባኤ ነው፡፡

ሦስተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ

ይህ በኢየሩሳሌም የተደረገው ሦስተኛው የሐዋርያት ጉባኤ ቅዱስ ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ ይገባል፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ /ሲኖዶስ/ እየተባለ መጠራቱ ሁሉም የሚያውቀው ነው፡፡ ጉባኤው ሊደረግ የተፈለገበት ዋና ምክንያት የሚከተለው ነው፡፡ በሐዋርያት ዘመን በአንጾኪያ ከተማ በነበረችው ቤተክርስቲያን ነቢያትና መምህራን ነበሩ፡፡ እነርሱም በርናባስ፣ ኔጌር የተባለው ስምዖን፣ የቀሬናው ተወላጅ ሉክዮስ፣ የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረው የሄሮድስ ባለሟል ምናሔና ሳውል እነዚህ ሁሉ ጌታን እያመለኩና እየጾሙ ሳለ መንፈስ ቅዱስ፤ «በርናባስንና ሳውልን ለጠ ራኋቸው ሥራ ለዩልኝ፤ ፍልጥዎሙ ሊተ ለበርናባስ ወለሳውል ለገብር ዘፈቀድክዎሙ» አላቸወ፡፡ እነርሱም መንፈስ ቅዱስ እንደነገራቸው አደረጉ፡፡ ከጾሙ ከጸለዩና እጃቸውንም ከጫኑ በኋላ አሰናበቱአቸው   /ሐዋ.13፥1-3/፡፡

ከዚያም ጳውሎስ በርናባስና ማርቆስ ከሌሎቹ ጋር ወደ ቦታው ሁሉ እየዞሩ ወንጌልን ሰበኩ፡፡ በየሰንበቱም በአይሁድ ምኩራብ እየተገኙ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነትና ስለ ትንሣ ኤው ይሰብኩ ነበር፡፡ እንደዚሁም በልስጥራ፣ በደርቤን፣ በጲስድያ፣ በጵንፍልያ፣ በጴርጋሞን፣ በጵርሄንም የእግዚአብሔርን ቃል /ወንጌልን/ እየሰበኩ ሕዝቡን ያጽናኑ ነበር፡፡ አንጾኪያም በደረሱ ጊዜ ቤተክርስቲያንን /ምእመናንን/ ሰብስበው እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ሁሉ ለአሕዛብም የሃይማኖት ደጅ አንደተከፈተላቸው ተናገሩ፡፡
ነገር ግን በዚያን ጊዜ አንዳንዶች ከይሁዳ ሀገር ወደ አንጾኪያና ወደ ሌሎቹ አውራጃዎች ወረዱና «እንደሙሴ ሥርዓት ካልተገረዛችሁ ትድኑ ዘንድ አትችሉም» እያሉ ወንድሞችን /ምእመናንን/ ያስተምሩ ጀመር፡፡ በዚያን ጊዜ በእነዚያ ሰዎች በጳውሎስና በበርናባስ መካከል ብዙ ጠብናክርክር ተፈጠረ፡፡ ጠቡና ክርክሩ እያየለ በሔደ ጊዜ ጳውሎስ፣ በርናበስና ከእርሱ ጋር የነበሩ የወንጌል አገልጋዮች ተነጋግረው ወደ ሐዋርያት ለመሔድ ወሰኑ፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም በደረሱጊዜ ቤተክርስቲያን /ምእመናን/ ሐዋርያትና ቀሳውስት /Aposstles and the elders/ ተቀበሉአቸው፡፡ እነ ጳውሎስም በዞሩባቸው አህጉረ ስብከት ሁሉ ያደረጉትን /የፈጸሙትን/የወንጌል አገልግሎትና የገጠማቸውን ችግር ሁሉ በዝርዝር ሪፖርት አቀረቡ፡፡ በዚያን ጊዜ በጌታ ካመኑት ከፈሪሳውያን ወገን የሆኑት ሰዎች ተነሥተው «ትገርዙአቸው ዘንድና የሙሴንሕግ እንዲጠብቁ ታዝዙአቸው ዘንድ ይገባል» ብለው ለሐዋርያት ተናገሩ፡፡ እነሆም በዚያን ጊዜ ሐዋርያትናቀሳውስት /Apostles and the elders/ ለመመካከርና ለመወሰን በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ የዚህ ዐቢይ ሲኖዶስ ሰብሳቢ /ሊቀመንበርም/ ቅዱስ ያዕቆብ ኤጲስ ቆጶስ ዘኢየሩሳሌም እንደነበር በቤተክርስቲያን ታሪክ ተገልጿል፡፡ በጉባኤውም በቀረበው ጉዳይ ላይ ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያውን ንግግር አደረገ፡፡ ከቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር በኋላም ጳውሎስና በርናባስ ተነሥተው እግዚአብሔር በእጃቸው በአሕዛብ መካከል ያደረገውን ምልክትና ድንቅ ነገር ሁሉ ለሲኖዶሱ ተረኩ፡፡ ከዚያም የጌታ ወንድም እየተባለ የሚጠራው የኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስና የጉባኤው ሰብሳቢ ቅዱስ ያዕቆብ ንግግር አደረገ፡፡ ከቅዱስ ያዕቆብ ንግግር በኋላ
ሐዋርያትና ቀሳውስት /Apostles and the elders/ ከቤተክርስቲያኑ /ምእመናኑ/ሁሉ ጋር ከእነርሱ የተመረጡትን ሰዎች ከጳውሎስና ከበርናባስ ጋር ወደ አንጾኪያ ይልኩ ዘንድ ተስማሙ፡፡ ከእነ ጳውሎስ ጋር እንዲሔዱ የተመረጡትም በርስያን የተባለው ይሁዳናሲላስ ነበሩ፡፡ የጉባኤውም አባላት በጉባኤ የተወሰነውን ውሳኔ ጽፈው በተመረጡት ወንድሞች እጅ ላኩ፡፡ መልእክተኞቹም ተሰናብተው ወረዱ፤ ሕዝቡንም ሰብስበው ከሐርያት ጉባኤ የተላከውን ደብዳቤ ሰጡአቸው፡፡ ባነበቡትም ጊዜ ከምክሩ የተነሣ  ደስ አላቸው፡፡ ይሁዳና ሲላስም ደግሞ ነቢያት ነበሩና ወንድሞችን በብዙ ቃል መክረው አጽናኑአቸው፡፡ አያሌ ቀንም ከእነርሱ ጋር ከተቀመጡ በኋላ ከወንድሞቻቸው በሰላም ተሰና ብተው ወደ ሐዋርያት ተመለሱ፡፡ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊትና ሲኖዶሳዊት ለመሆንዋ ተደጋግሞየተነገረ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የተመሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ቤተክርስቲያንን በስብከተ ወንጌል ስለአሰባሰቡና ስለአጠናከሩ ቤተክርስቲያን በሲኖዶስ እየተመራች ከዚህ ዘመን በመድረስዋ ሲኖዶሳዊት /ጉባኤያዊት/ እየተባለች ትጠራለች፡፡

ከቅዱሳን ሐዋርያት ቀጥለው የተነሡት አባቶችም ቤተክርስቲያንን በሚመሩበት ወቅት፡-
ሀ. የቤተክርስቲያንን ቅዱሳት መጻሕፍት ከመናፍቃን መጻሕፍት ለመለየትና ቁጥራቸውን
    በቀኖና /በሕግ/ ለመወሰን፤
ለ. ሥርዐተ ቅዳሴንና ሥርዐተ ጸሎትን በቀኖና /በሕግ/ ለመመደብ፤
ሐ. አጽዋማትንና በዓላትንም ለመወሰን የሲኖዶስ ስብሰባ በማድረግ ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ ወስነዋል፡፡ በሌላ በኩልም ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው መናፍቃን /ሐራ ጥቃዎች/ በተነሡ ጊዜ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን አባቶች ርትዕት፣ ስብሕት /ኦርቶዶክስ/ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሐራጥቃዎችን በቀኖናዋ ውግዘት ለማስወገድ በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ ይወስኑ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በየሀገሩ የአካባቢ ሲኖዶሶች /Regional or Local synods/ ተደርገዋል፡፡ ከተደረጉት ሲኖዶሶችም ለአብነት ጥቂቶቹን ቀጥለን እንመለከታለን

1.    በ257ዓ.ም በካርቴጅ የተደረገው ሲኖዶስ፡- በዚህ የአካባቢ /regional/ ሲኖዶስ ሰማንያ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሳትፈዋል፡፡ የሲኖዶሱ ሰብሳቢ ቅዱስ ሲፕሪያኖስ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ሥርዓተ ጥምቀትንና መናፍቃንን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የኤጲስ ቆጶሳትን ሥልጣን የተመለከቱ ቀኖናዎች ተወስነዋል፡፡
2.    268 – 270 ዓ.ም በተከታታይ በአንጾኪያ ሲኖዶስ ተደርጎአል፡፡ በዚህ ሲኖዶስ ዐሥራ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በምስጢረ ሥጋዌ የኅድረትንና የፅምረትን /ምንታዌ አካላትን/ ትምህርት ማስፋፋት የሞከረውን ኤጲስ ቆጶስ ጳውሎስ ሳምሳጢን መክረው አልመለስ ስላለ አውግዘው ከቤተክርስቲያን ለይተውታል፡፡
3.    በዚሁ ዓይነት በአንካራ በ314 ዓ.ም ፣በጋንግራ 365 ዓ.ም፣ በሳርዲካ በ343ዓ.ም፣ በአንጾኪያ በድጋሚ በ341 ዓ.ም፤ በላኦዶቂያ በ334 እና በ381 ዓ.ም የተጠራው ሲኖዶስ ስድሣ  ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ እንደዚሁም በድጋሚ በካርቴጅ በ419 ዓ.ም የተሰበሰበው ሲኖዶስ )138 ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ ይህ ሲኖዶስ «የአፍሪካ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ» በሚል መጠሪያ ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሐዋርያውያነ አበው /Apostolic Fatheres/ የቤተክርስቲያንን አስተዳደርና የቤተክርስቲያንን ችግር በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ በመመርመርና አስፈላጊውንም በመወሰን ቤተክርስቲያንን መርተዋል፡፡ ያውም ከሰባ ዓ.ም ጀምሮ እስከ 313 ዓ.ም ድረስ የነበረው ጊዜ አሕዛብ በቁር የበዙ በትና በመንግሥት አስተዳደርም አጠቃላይ ሥልጣን ግን የጨበጡበት ዘመን ስለነበረ፤ በዚህ ዘመን ከፀረ እግዚአብሔርና ከፀረ ክርስትና ኃይሎች ጋር በመጋደል በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ስለ ሀልዎተ እግዚአ ብሔርና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው መሥዋዕት ሆነው የተሰውበት ዘመን ነበር፡፡ በመሆኑም ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት እየተባለ ይጠራል፡፡

ከቅዱሳን ሐዋርያት ቀጥለው የተነሡት አባቶችም ቤተክርስቲያንን በሚመሩበት ወቅት፡-
ሀ. የቤተክርስቲያንን ቅዱሳት መጻሕፍት ከመናፍቃን መጻሕፍት ለመለየትና ቁጥራቸውን
    በቀኖና /በሕግ/ ለመወሰን፤
ለ. ሥርዐተ ቅዳሴንና ሥርዐተ ጸሎትን በቀኖና /በሕግ/ ለመመደብ፤
ሐ. አጽዋማትንና በዓላትንም ለመወሰን የሲኖዶስ ስብሰባ በማድረግ ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ ወስነዋል፡፡ በሌላ በኩልም ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው መናፍቃን /ሐራ ጥቃዎች/ በተነሡ ጊዜ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን አባቶች ርትዕት፣ ስብሕት /ኦርቶዶክስ/ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሐራጥቃዎችን በቀኖናዋ ውግዘት ለማስወገድ በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ ይወስኑ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በየሀገሩ የአካባቢ ሲኖዶሶች /Regional or Local synods/ ተደርገዋል፡፡ ከተደረጉት ሲኖዶሶችም ለአብነት ጥቂቶቹን ቀጥለን እንመለከታለን

1.    በ257ዓ.ም በካርቴጅ የተደረገው ሲኖዶስ፡- በዚህ የአካባቢ /regional/ ሲኖዶስ ሰማንያ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሳትፈዋል፡፡ የሲኖዶሱ ሰብሳቢ ቅዱስ ሲፕሪያኖስ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ሥርዓተ ጥምቀትንና መናፍቃንን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የኤጲስ ቆጶሳትን ሥልጣን የተመለከቱ ቀኖናዎች ተወስነዋል፡፡
2.    268 – 270 ዓ.ም በተከታታይ በአንጾኪያ ሲኖዶስ ተደርጎአል፡፡ በዚህ ሲኖዶስ ዐሥራ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በምስጢረ ሥጋዌ የኅድረትንና የፅምረትን /ምንታዌ አካላትን/ ትምህርት ማስፋፋት የሞከረውን ኤጲስ ቆጶስ ጳውሎስ ሳምሳጢን መክረው አልመለስ ስላለ አውግዘው ከቤተክርስቲያን ለይተውታል፡፡
3.    በዚሁ ዓይነት በአንካራ በ314 ዓ.ም ፣በጋንግራ 365 ዓ.ም፣ በሳርዲካ በ343ዓ.ም፣ በአንጾኪያ በድጋሚ በ341 ዓ.ም፤ በላኦዶቂያ በ334 እና በ381 ዓ.ም የተጠራው ሲኖዶስ ስድሣ  ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ እንደዚሁም በድጋሚ በካርቴጅ በ419 ዓ.ም የተሰበሰበው ሲኖዶስ )138 ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ ይህ ሲኖዶስ «የአፍሪካ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ» በሚል መጠሪያ ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሐዋርያውያነ አበው /Apostolic Fatheres/ የቤተክርስቲያንን አስተዳደርና የቤተክርስቲያንን ችግር በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ በመመርመርና አስፈላጊውንም በመወሰን ቤተክርስቲያንን መርተዋል፡፡ ያውም ከሰባ ዓ.ም ጀምሮ እስከ 313 ዓ.ም ድረስ የነበረው ጊዜ አሕዛብ በቁር የበዙ በትና በመንግሥት አስተዳደርም አጠቃላይ ሥልጣን ግን የጨበጡበት ዘመን ስለነበረ፤ በዚህ ዘመን ከፀረ እግዚአብሔርና ከፀረ ክርስትና ኃይሎች ጋር በመጋደል በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ስለ ሀልዎተ እግዚአ ብሔርና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው መሥዋዕት ሆነው የተሰውበት ዘመን ነበር፡፡ በመሆኑም ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት እየተባለ ይጠራል፡፡

ዓለም አቀፍ ሲኖዶሶች

ከዚህ በላይ ለማየት እንደተሞ ከረው በአካባቢ በሚገኙት አብያተ ክርስቲያናት ዙሪያ ወይም ውስጥ የቀኖና ወይም የዶግማ ችግሮች ሲከሰቱ በአቅራቢያ ሀገሮች ከሚገኙ ኤጲስ ቆጳሳት ሲኖዶሶች እየተጠሩ ለተነሡት ችግሮች መፍትሔ ይሰጡ ነበር፡፡

ነገር ግን በአካባቢ በሚደረጉት ሲኖዶሶች የማይፈቱ ከሆኑ በዚያኑ ጊዜ ዓለም አቀፍ ከሚባለው የዓለም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት የጋራ የሆነ ዐቢይ ዓለም አቀፍ ጉባኤ /Ecumerical council/ እያደረጉ ችግሮቹን በመመርመር መፍትሔ ይሰጡ ነበር፡፡

የመጀመሪያው የኒቂያ ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ በ325ዓ.ም ኒቂያ በተባለች ከተማ ከመደረጉ በፊት አርዮስና ኑፋቄአዊ ትምህርቱን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት አርዮስ በኖረበትና በተነሣ በት ሀገር በእስክንድርያ በመጀመሪያ በ320 ዓ.ም፤ ቀጥሎም በ321 ዓ.ም ሲኖዶስ ተደረገ፡፡ የዚያሲኖዶስ ሰብሳቢ የእስክንድርያ ሊቀ ጰጳስ የነበረው እለ እስክንድሮስ ዘእስክንድርያ ነበር፡፡ ችግሩ በዚያ ዓይነት ይፈታል ተብሎ ቢሞከርም ሰባት መቶ ደናግል፣ ዐሥራ ሁለት ዲያቆናት፣ ስድስት ቀሳውስት /የደብር አለቆች/ ከሦስት የሚበልጡ ኤጲስ ቆጶሳት ትምህርቱን ተቀብለው አርዮስን ስለደገፉ አርዮስ በሲኖዶሱ ምክር ሊመለስ አልቻለም፡፡ ስለዚህ ከአራት ዓመት በኋላ በሊቀ ኤጲስ ቆጶሳት እለእስክንድሮስ አስተባባሪነት በንጉሠ ነገሥቱ በቆስጠንጢኖስ ተባባሪነት 318 አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት በኒቂያ ከተማ በ325 ዓ.ም የሲኖዶስ ስብሰባ አድርገው ከኑፋቄው አልመለስ ያለውን እልከኛውን አርዮስንና ትምህርቱን አውግዘው ሃይማኖትን አጸኑ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በአንድ ልብ ሆነው «አንቀጸ ሃይማኖት /ጸሎተ ሃይማኖት/» የተባለውን የዶክትሪን ዐዋጅ አጸደቁ፡፡ ከሃያም ያላነሱ ቀኖናዎችን አጽድቀው አሠራጩ ፡፡

ከዚያም በመቀጠል ከሃምሳ ስድስት ዓመት በኋላ መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አምላክ መሆኑን የካዱ መናፍቃን /ሐራጥቃዎች/ /heretics/ ተነሥተው በምሥራቅ በኩል የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ባስቸገሩ ጊዜ በቁስጥንጥንያ ከተማ በ381 ዓ.ም ከመላው ዓለም አንድ መቶ ሃምሳ አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰበሰቡ፡፡ «መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ያነሰ ነው /ሕጹጽ ነው/» ብለው የተነሡትን መቅዶን ዮስንና ተከታዮቹን ተመክረውና ተለምነው ከክሕደታቸው ስላልተ መለሱ አወገዙአቸው፡፡ ትምህርታቸውንም በማውገዝ ውሳኔ አሳለፉ፡፡ በመቀጠልም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመመርኮዝ «መንፈስ ቅዱስ እንደ አብና እንደ ወልድ ፍጹም አምላክ መሆኑን፣ ጌታና ማኅየዊ እየተባለም ከአብና ከወልድ ጋር አንድ ባሕርይ ስለሆነ ከሁለቱ አካላት ጋር በአንድ መለኮት እንደ ሚመሰገንና እንደሚሰገድለት፤ እንዲሁም ከአብ ብቻ መሥረጹን ገልጸው ወሰኑ» ውሳኔውም ከኒቂያው አንቀጸ ሃይማኖት/ከጸሎተ ሃይማኖት/ ጋር ተጨምሮ እንዲጻፍ አደረጉ፡፡ በዚሁም መሠረት በአሁኑ ዘመን በመላው ዓለም በየቤተክር ስቲያኑ በተለያየ ቋንቋ የሚጸለየው ጸሎተ ሃይማኖት «የኒቂያ- ቁስጥ ንጥንያ አንቀጸ ሃይማኖት»/ Nicene-constantinople creed/ እየተባለ ይጠራል፡፡

ከቁስጥንጥንያው ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ በኋላ ሃምሳ ዓመታት ቆይቶ ንስጥሮስ የተባለ መናፍቅ ተነሣ ፡፡ እሱም የቁስጥንጥንያ ትርያርክ ነበር፡፡ ከ426ዓ.ም ጀምሮ በቁስጥንጥንያ ምስጢረ ሥጋዌን በማፋለስ «ክርስቶስ ሁለት አካላት፣ ሁለት ገጻት፣ ሁለት በመስተጻምር /በሲናፊያ/ አንድ የሆኑ ባሕርያት ያሉት ነው» እያለ አስተማረ፡፡ በዚህም መርሖ መሠረት «ቃለ እግዚአብሔር /ሎጎስ/ እና ክርስቶስ በመስተፃመር /በሲናፊያ/ አንድ ስለሆኑ ክርስቶስ አንድ ነው» ብሎ አስተማረ፡፡

ከዚሁም አያይዞ «ድንግል ማርያም እግዚአብሔርን ልትወልድ አትችልም፤ ከእርስዋ የተወለደው ክርስቶስ ነው፡፡ ስለሆነም እርስዋን ወላዲተ ክርስቶስ እንጂ ወላዲተ እግዚአብሔር /ወላዲተ አምላክ/ አንላትም» በማለት አስተማረ፡፡ በዚሁ ችግር ምክንያት በ431 ዓ.ም ከመላው ዓለም አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳትና ኤጲስ ቆጶሳት በኤፌሶን ተሰብስበው ሦስተኛውን ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ አደረጉ፡፡

ንስጥሮስን ሦስት ጊዜ ጠርተውት አልቀርብም ስላለ የጻፋቸውን መልእክታት ተመልክተውና ስሙን ጠርተው አወገዙት፡፡ ክርስቶስንም «ወልድ ዋሕድ፣ ፍጹም  አምላክ፣ ፍጹም ሰው፣ ከሁለት ባሕርይ / ከመለኮትና ከትስብእት/ አንድ ባሕርይ፣ አንድ አካል» መሆኑን የሚያረጋግጡትን የቅዱስ ቄርሎስን መልእክታት ተቀብለው አጸደቁ፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምንም «በአማን ወላዲተ አምላክ» መሆንዋን አረጋገጡ፡፡

በሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ዮሐንስ ዘአንጾኪያ እየተመራ ወደ ኤፌሶን የመጣው የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶሳት ቡድን ግን የንስጥሮስን ውግዘት ተቃወመ፡፡ በዚህ ምክንያት የአንጾኪያ ቤተክርስቲያን በኤፌሶን ከተሰበሰቡት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ተለየች፡፡ እስከ 433 ዓ.ም በእስክ ንድርያና በአንጾኪያ አብያተ ክርስቲያናት መካከል መለያየት ጠነከረ፤ የጠብ ግድግዳም ተመሠረተ፡፡ በ433 ዓ.ም ግን በንጉሠ ነገሥት ቴኦዶስዮስ ካልዕ አስታራቂነት ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት ታረቁ፡፡ በቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንደርያና በዮሐንስ ዘአንጾኪያ መካከልም ሰላም ተመሠረተ፡፡ በዚሁ ዕርቅ መሠረት አንጾኪያውያን አበው በኤፌሶን የተወሰነውን ውሳኔ ተቀበሉ፡፡ በንስጥሮስ መወገዝና መወገድም ተስማሙ፡፡ አንድነትም ተመሠረተ፡፡

ቅዱስ ቄርሎስ በ444 ዓ.ም ሲያርፍ በኋላ የሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ  የነበረው ዲዮስቆሮስ ዘእስክንድርያ ትርያርክ ሆኖ ተሾመ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በኋላ በ488ዓ.ም ከቁስጥ ንጥንያ በሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ፍላቭያን የሚመራ የአካባቢው ኤጲስ ቆጶሳት የተሳተፉበት ሲኖዶስ /Local Synods/ ተደረገ፡፡ ወደዚህም ሲኖዶስ አውጣኪ ተከሶ ቀረበና ተወገዘ፡፡ እርሱም ወደ ሮምና ወደ እስክንድርያ ትርያክ«አላግባብ ተወገዝሁ» ብሎ አቤቱታ ጻፈ፡፡

«የአውጣኪን ጉዳይ ለመመርመርና ተረፈ ንስጥሮሳውያንን ለማስወገድ» በሚል አጀንዳ ለሁለተኛ ጊዜ በ449 ዓ.ም በኤፌሶን ሲኖዶስ ተደረገ፡፡ በስብሰባውም አንድ መቶ ሠላሳ ስአምስት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰበሰቡ፡፡ የሲኖዶሱ ሊቀ መንበር ትርያክ ዲዮስቆሮስ ሆነ፡፡ በአጀንዳው መሠረትጉዳዮች ተመረመሩ፡፡ አውጣኪንም መረመሩት፡፡ ሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ፍላቭያኖንስና ፌኦዶሪትን ግን ጉባኤው መርምሮ መንፈቀ ንስጥሮሳውያን ሆነው ስላገኛቸው በጊዜያዊ ውግዘት ተቀጥተውና ታስረው እንዲቆዩ ተደረገ፡፡ የፖፕ ልዮን ጦማረ ሃይማኖትም ቀርቦ በዲዮስቆሮስና በሌሎች የጉባኤው አባላት ተመርምሮ ከንስጥሮስ ትምህርት ጋር ተዛምዶ ስለተገኘ በጦማሩና በጦማሩ ባለቤት ላይ ውግዘት አከል ተግሳጽ እንዲተላለፍባቸው ተደረገ፡፡ ፖፕ ልዮን ግን ይህንን ታሪክ ሰምቶ በዲዮስቆሮስ ጥርሱን ነከሰ፡፡

ጉባኤውንም «የወረበሎች ጉባኤ» /Synodd of listriks/ ብሎ ጠራው፡፡ ከዚህ ንዴት የተነሣ  በሁለተኛው ዓመት በ451 ዓ.ም በኬልቄዶን ጉባኤ እንዲደረግ ተወሰነ፡፡ በዚህ ጉባኤስድስት መቶ ሠላሳ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በልዮን መልእክተኞች እየተመሩ ቅዱስ ዲዮስቆሮስን ከንጉሡ ጋር ተሻርከው ከመንበሩ አወረዱት፡፡ ታስሮም በደሴተ ጋግሪ ሦስት ዓመት ተቀመጠ፡፡ ከዚያም እንዳለ በእስራትና በበሽታ ምክንያት 454 ዓ.ም ዐረፈ፡፡ከቅዱሳን ሐዋርያት ዘመን ጀምሮ እስከ አምስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ያየነው ታሪክ እንደሚያስረዳን ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያን መሪ እንደሆነ ነው፡፡ ቤተክርስቲያንምከተጠቀሰው የመጀመሪያው ዘመን ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ መለኮታዊ አገልግሎትዋን ስታካሒድ የኖረችው በመንፈስ ቅዱስ በሚመራው በቅዱስ ሲኖዶስ በመመራት ነው፡፡ በቤተክርስቲያናችን ትውፊት መሠረትም የሐዋርያትንና የአርድእት ቀኖናዎች የሊቃውንትም ጭምር ሲኖዶስ /መጽሐፈ ሲኖዶስ/ እየተባለ ይጠራል፡፡ ከዚህ በላይ እንደተ መለከትነውና እንደምናውቀው በአካባቢ የተነሡትን የሃይማኖትም ሆኑ የቀኖና ችግሮች በመጀመሪያ በአካባቢው ሀገሮች ባሉት ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ ወሳኝነት ይፈቱ ነበር፡፡ ከእነርሱም አቅም በላይ ሆነው የተገኙ ችግሮች ደግሞ «ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ» /Ecumerical Synods/ እየተጠራ ሲወሰን እንደነበረ ተመልክተናል፡፡

ከዚያም ሌላ በየትኛውም ሀገር የምትገኘው የክርስቶስ ቤተክርስቲያን /Local Synods/ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ አንድ ማእከል አንድ ሲኖዶስ ብቻ እንዳላት ተገንዝ በናል፡፡ ለምሳሌ የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን በአንድ የኢየሩሳሌም ቅዱስ
ሲኖዶስ፣ የእስክንድርያ ቤተክርስቲያን በአንድ የእስክንድርያ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የቁስጥንጥንያ ቤተክርስቲያን በአንድ የቁስጥንጥንያ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የግሪክ ቤተክርስቲያን በአንድ የግሪክ ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ ሲመሩ መኖራቸውን እናውቃለን፡፡

ለአንዲት ነጻ ሀገር አንድ ርላ ሜነት /One Panriament/ ብቻ እንዳላት ሁሉ ለአንዲት ነጻ ቤተክርስቲያንም አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ /Autocephalous Church/ ብቻ እንዳላት የታወቀና የተረጋገጠ ነው፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ስንል /በተለይ ሀገራዊ Local/ የሚከተሉትን ነገሮች ይይዛል፡-
– ኤጲስ ቆጶሳት
– የታወቀ ሕጋዊ መንበር
– ታሪካዊና ሕጋዊ መሠረት
ለምሳሌ የግብፅን ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ብንመለከት
– ወደ ሃምሳ የሚጠጉ ኤጲስ ቆጶሳት
– የእስክንድርያ /የቅዱስ ማርቆስ/ መንበር
– በታሪክ የታወቀና ቅዱስ ሲኖዶሱ ያጸደቀው ሕግ አላቸው

 የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ፦

–    ኤጲስ ቆጶሳት
–    የአዲስ አበባ መንበር /መንበረ ፓትርያክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም የሚገኝ/
በቤተክርስቲያን ሕግ የጸደቀ ከመነሻውም /ሲኖዶስ በኢትዮጵያ ሲጀመር የነበረ ሕግ አላት፡፡