Entries by Mahibere Kidusan

ግዝረት

ጥር 5/2004 ዓ.ም

በዲ/ን አሻግሬ አምጤ

ግዝረት ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው፡፡ እነዚህ ንዑሳን በዓላት የሚባሉትም ስብከት፣ ብርሃን፣ ኖላዊ፣ ግዝረት፣ ቃና ዘገሊላ፣ ልደተ ስምዖን፣ ደብረ ዘይት፣ የመጋቢት መስቀልና መስቀል ናቸው፡፡ ነቢያት ይወርዳል፤ ይወለዳል ብለው በትንቢት ይጠባበቁት የነበረው መሲሕ የዓለም ብርሃን፣ የነፍሳት ጠባቂ መሆኑን አምነን የምናከብራቸው ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ ይባላሉ፡፡ ከእናቱና ከደቀመዛሙርቱ ጋር በሰርግ ቤት የተገኙበት ቃና ዘገሊላ፣ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበትና አረጋዊ ስምዖንን የሰላሳ ዓመት ጎልማሳ የሆነበት “ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ዐይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና” በማለት የተናገረበት ልደተ ስምዖን ከንዑሳን በዓላት ይመደባሉ፡፡ የዚህ ጽሑፍ ትኩረት ግዝረት በመሆኑ ሀተታዬን ወደ እሱ እመልሳለሁ፡፡

በዲታ ወረዳ የቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን በአጽራረ ቤተ ክርስቲያን የቃጠሎ አደጋ ደረሰበት

ጥር 5/2004 ዓ.ም

ምንጭ፡- አርባ ምንጭ ማእከል

በጋሞ ጎፋ ሀገረ ስብከት፣ በዲታ ወረዳ፣ ጋና ደሬ ቀበሌ፣ የቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ታኅሣሥ 29 ቀን 2004 ዓ.ም. ከሌሊቱ በስድስት ሰዓት አካባቢ በእሳት ቃጠሎ አደጋ ደረሰበት፡፡

Begamogofa

የቦታው አቀማመጥና አደጋው የደረሰበት ሰዓት ሌሊት በመሆኑ በቦታው ምንም ዓይነት ነዋያተ ቅድሳት ማትረፍ እንዳልተቻለ በቦታው የሚገኙት የደብሩ አገልጋይ ገልጸዋል፡፡ የአደጋውን መከሰት ሰምተው የመጡት የአካባቢው ምዕመናን ከሌሊት ጀምሮ ጥልቅ ሀዘናቸውን በለቅሶ ሲገልጹ እንደነበር በቦታው የተገኙት የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ዘግበዋል፡፡

በችግር ላይ የሚገኘው የበኬ ቅድስት ማርያም የአብነት ትምህርት ቤት እርዳታ ተደረገለት፡፡

ጥር 5/2004 ዓ.ም

በይበልጣል ሙላት
Beke 1

በአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል የተዘጋጀ ጉዞ ወደ በኬ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የአብነት ትምህርት ቤት የተካሔደ ሲሆን የጉዞውም ዋነኛ አላማ በአስከፊ ሁኔታ ላይ ለሚገኙት ለደብሯ የአብነት መምህራንና ተማሪዎች ጊዜያዊ የቁሳቁስ እርዳታ /ድጋፍ/ ለማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በጉዞውም በክፍሉ አስተባባሪነት ከምእመናንና ከማኅበሩ አባላት የተሰበሰቡና የተዘጋጁ  11 ኩንታል ስንዴ ዱቄት፣ 230 ሱሪ፣ 398 ሹራብና ቲሸርት፣ 145 ኮትና ጃኬት፣ 25 የአልጋ ልብስና አንሶላ፣ 43 የተለያዩ ልብሶች፣ 230 ግራም 249 የልብስ ሳሙና እና ለመማሪያ የሚሆኑ 11 መጻሕፍት ተበርክተዋል፡፡

እድለኞቹ እረኞች /ለሕፃናት/

ጥር 3/2004 ዓ.ም በእኅተ ፍሬስብሐት በአንድ ምሽት በቤተለሔም አካባቢ እረኞች በጎቻቸውን ተኩላዎች እንዳይበሉባቸው ይጠብቁ ነበር፡፡ እኩለ ሌሊት ሲሆን በዚያ አካባቢ ልዩ ብርሃን ታየ፡፡ እረኞቹ ያንን ብርሃን ሲያዩ በጣም ተገረሙ፡፡ በዚያም መልአክ መጣ እና በዚያች ሌሊት የዓለም መድኀኒት የሚሆን ሕፃን መወለዱን፤ ያም ሕፃን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ለእረኞቹ ነገራቸው፡፡ እረኞቹም ተደሰቱ ፈጥነው ሕፃኑ ወደ ተወለደበት ወደ ቤተልሔም […]

መካነ ጉባኤያት ወላዴ ሊቃዉንት ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ዕድሳት ሊደረግለት ነዉ፡፡

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ
  • ለዕድሳቱ 1.5 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል፡፡

frontመካነ ጉባኤያት የሆነዉን ታሪካዊዉንና ጥንታዊዉን ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ለማደስ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ተካሔደ፡፡ታኅሣሥ 22 ቀን 2004 ዓ.ም . በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ በተካሄደዉ በዚህ ጉባኤ የአራቱ ጉባኤያት የትርጓሜ መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃዉንት ዕዝራ ሐዲስና የደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ አስተዳዳሪና የድጓ መምህር የሆኑት መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋ ጉባኤያቸዉን ትተዉ የተገኙበት ሲሆን፣ ከአዲስ አበባም በአሁኑ ጊዜ የሊቃዉንት ጉባኤ ሰብሳቢ የሆኑት መልአከ ሰላም ዐምደ ብርሃን እና  መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁን፣ ሊቀ ስዩማን ራደ አስረስና ሌሎች የሊቃዉንት ጉባኤ አባላት እንዲሁ ም በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳዉሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር የሆኑትን መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤን ጨምሮ በቦታዉ የተማሩና የጉባኤ ቤቱን ታሪክ የሚያዉቁ በርካታ ሊቃዉንት በጉባኤዉ ላይ ተገኝተዋል፡፡

 

“እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል” (ሉቃ.2፡11)

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በዲ/ን በረከት አዝመራው እና በዲ/ን አሉላ መብራቱ


“ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ፤

ለእርሱ ሰብአ ሰገል የሰገዱለት፣ የልደቱ ክብር ድንቅ ነው።”

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}ledete2004{/gallery}

እግዚአብሔርን በእምነት ደስ ያሰኙ ቅዱሳን ከእስራኤላውያን ተነሥተው ነበር።(ዕብ.11) የአባቶች አለቃ ከሆነው ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ሰው መሆን (ዘመነ ሥጋዌ) ድረስ ብዙ ታላላቅ አባቶችና እናቶች በእስራኤል ዘንድ ተገኝተዋል።

 

የእስራኤል ታሪክ ሁልጊዜ መልካም ታሪክ ብቻ ግን አይደለም፤ እግዚአብሔርን ያሳዘኑባቸው ጊዜያት ጥቂቶች አይደሉም። በዚህ ጊዜ በዙሪያቸው ባሉ ነገሥታት እየተማረኩ ወደ ፋርስ፣ ባቢሎንና ግብጽ እየወረዱ ለአሕዛብ የተገዙበትና የገበሩበት ጊዜም ነበር። ንስሐ ገብተው ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ደግሞ እግዚአብሔር ከእነርሱ መካከል ሰው እያስነሣ ያድናቸው ነበር። ለአባቶቻቸው የገባውን የዘለዓለም ቃልኪዳን እያሰበ ይረዳቸውም ነበር። (መዝ.77 (78))

እረኝነት እንደ አፍርሃት ሶርያዊ አስተምህሮ

ታኅሣሥ 24/2004 ዓ.ም

ትርጉም

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

መግቢያ

አፍርሃት ያዕቆብ ዘንጽቢን እና “የፋርሱ ጠቢብ” በሚሉ ስያሜዎቹ የሚታወቅ አባት ሲሆን በዐራተኛው ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ የተነሣ ሶርያዊ ተጠቃሽ  ጸሐፊ ነው፡፡ በእርሱ ዘመን ማኅልየ ማኅልይ ዘሶርያና የቶማስ ሥራ የሚባሉት ሥራዎች እንደሚታወቁ ይታመናል፡፡ ስለአፍራሃት የሕይወት ታሪክ ብዙ የሚታወቅ ነገር ባይኖርም አንዳንድ ጥንታዊ ታሪክ ጸሐፊያን አፍራሃት በአሁኑዋ ኢራቅ ትገኝ በነበረችው ማር ማታያ ተብላ በምትታወቀው ገዳም ሊቀ ጳጳስ እንደነበረ ጽፈው ይገኛሉ፡፡ ይህ ግን ተቀባይነት የለው፡፡ አፍራሃት ሃያ ሦስት ድርሳናትን የጻፈ ሲሆን እነርሱም የተለያዩ ርእሶች ያሉዋቸው ናቸው፡፡ እርሱ ከጻፈባቸው ድርሰቶች መካከል ስለእምነት ፣ ስለፍቅር፣ ስለጾም ፣ ስለጸሎት፣ በዘመኑ ስለነበረው የቃልኪዳን ልጆችና ልጃገረዶች፣ ስለትሕትና ጽፎአል፡፡ አፍርሃት ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር ለሶርያ ሥነ ጽሑፍ ፋና ወጊ የሆነ ጸሐፊ ነው፡፡  እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በእረኝነት ላይ የፃፈውን እንመለከታለን፡፡

እረኞች የሕይወት ምግብን ይሰጡ ዘንድ በመንጋው ላይ የተሾሙ አለቆች ናቸው፡፡ መንጋውን የሚጠብቅና ስለእነርሱ የሚደክም እረኛ እርሱ መንጋውን ለሚያፈቅረውና ራሱን ስለመንጎቹ ለሰጠው መልካም እረኛ እውነተኛ ደቀመዝሙር ነው፡፡ ነገር ግን መንጋውን ከጥፋት የማይመልስ እርሱ ለመንጋው ግድ የሌለው ምንደኛ ነው፡፡

የልደት ምንባብ ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ

ታኅሣሥ 24/2004 ዓ.ም

ይህ ጽሑፍ  ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ “መጽሐፈ ምሥጢር”  ምዕራፍ 6 ላይ “የልደት ምንባብ” ከሚለው የተወሰደ ነው፡፡

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}ledet04{/gallery}

“… እግዚአብሔርም ሳሙኤልን “ልዩ ቅብዓት ይዘህ ወደ ቤተልሔም ሒድና ወደ ዕሤይ ቤት ግባ ከልጆቹ እኔ የመረጥኩትን አሳይሃለሁ” አለው፡፡ ሳሙኤልም ወደ ቤተልሔም ደረሰ ከዕሤይ አጥር ግቢ ገብቶ “ልጆችህን አምጣቸው” አለው፡፡ እርሱም ኤልያብን አምጥቶ ለእግዚአብሔር ሹመት የሚገባ ይህ ነው አለ፡፡ እግዚአብሔርም የመረጥኩት ይህን አይደለም አለው፡፡

ዳግመኛ ሳሙኤል አሚናዳብን አስመጥቶ፣ በእግዚአብሔር ፊትም አቆመው፡፡ እግዚአብሔር “ይህንንም አልመረጥኩትም አለ፡፡ ዕሤይ ስድስቱን ልጆቹን አቀረበለት፡፡  በሳሙኤል ፊትም የእግዚአብሔር ምርጫ በእነርሱ ላይ አልሠመረም፤ ሳሙኤል ዕሤይን “የቀረ ሌላ ልጅ አለህን?” አለው፡፡ እርሱም፡- “ታናሹ ገና ቀርቶአል፣ እነሆም በጎችን ይጠብቃል” አለ፡፡ ሳሙኤልም “በፍጥነት ልከህ አስመጣው” አለው፡፡ ዳዊትን አምጥተው በሳሙኤል ፊት አቆሙት፤ እግዚአብሔር ሳሙኤልን “ያልኩህ ይህ ነውና ተነሥተህ ቅባው” አለ፡፡ (1ሳሙ.16፡1-13)

“ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ”

ታኅሣሥ  22/2004 ዓ.ም
በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

 

በዛሬው ቀን ዓለም ለመዳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ይሁንታን የፈለገበት ቀን ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ከምንም በላይ የሰውን ነጻ ፈቃድ ስለሚያከብር መልአኩን ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ሲልከው ፈቃዱዋን ይጠይቃት ዘንድ ነበር፡፡ ይህ ማለት ምን ማለት መሰላችሁ “እነሆ በደጅህ ቆሜ አንኳኳለሁ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል”(ራእ.3፡20) እንዳለው ዓይነት ነው፡፡ ነገር ግን በይዘቱ የቅድስት እናታችን  ይሁንታ በጣም የተለየ ነው፡፡ ስለዚህም የዓለም መዳን በእርሱዋ ይሁንታ ላይ ነውና እግዚአብሔር በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በኩል የቅድስት ድንግል ማርያምን ፈቃድ ጠየቀ፡፡ ለእርሱዋም በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል አንደበት እግዚአብሔር ቃል ለሰው ልጆች መዳን ከእርሱዋ ተፀንሶ ለመወለድ ፈቃዱ እንደሆነ፣ እርሱዋንም የዘለዓለም እናቱና የሰው ልጆችን ፍጹም የመውደዱ ምልክት ሊያደርጋት እንደወደደ አበሰራት፡፡ ቅድስት እናታችንም ፍጹም ትወደውና ታመልከው የነበረው እግዚአብሔር ከእርሱዋ ተወልዶ ዓለምን ለማዳን መፍቀዱን ስትሰማ በፍጹም ደስታ ተሞልታ ግሩም በሆነ ትሕትና “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” “እንደቃልህ ይደረግልኝ” በማለት ዓለምን እፎይ አሰኘቻት፡፡ እስከዛች ጊዜ ድረስ ዓለም በጭንቀት ተውጣ የእርሱዋን መልስ በጉጉት ትጠባበቅ ነበር፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ሐዋርያዊ አገልግሎት በአርሲ ሀገረ ስብከት አካሔደ

ታኅሣሥ 20/2004 ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሐዋርየዊ Picture3አገልግሎት በአርሲ ሀገረ ስብከት ከኅዳር 29/2004 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 10/2004 ዓ.ም ለ11 ተከታታይ ቀናት በተለየዩ ወረዳዎች አካሔደ፡፡ 27 አባላት የተሳተፉበት ሐዋርያዊ አገልግሎት በተመረጡ 6 ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ቤተ ክርስቲያናት እንዲሁም በአሰላ ከተማ በተሳካ ሁኔታ የተከናወነ ሲሆን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያፈራቻቸው የማኅበረ ቅዱሳን ሰባኪያነ ወንጌል አማካይነት በአውደ ምሕረት ላይ ለምእመናን ሰፋ ያለ የወንጌል ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ በማኅበሩ መዝሙር ክፍል አባላት አማካይነት ከአባቶች እግር ስር ቁጭ ብለው የተማሩትን የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዓትና ትውፊት የጠበቀ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡