lideteEgzie

እድለኞቹ እረኞች /ለሕፃናት/

ጥር 3/2004 ዓ.ም

በእኅተ ፍሬስብሐት
lideteEgzie
በአንድ ምሽት በቤተለሔም አካባቢ እረኞች በጎቻቸውን ተኩላዎች እንዳይበሉባቸው ይጠብቁ ነበር፡፡ እኩለ ሌሊት ሲሆን በዚያ አካባቢ ልዩ ብርሃን ታየ፡፡ እረኞቹ ያንን ብርሃን ሲያዩ በጣም ተገረሙ፡፡ በዚያም መልአክ መጣ እና በዚያች ሌሊት የዓለም መድኀኒት የሚሆን ሕፃን መወለዱን፤ ያም ሕፃን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ለእረኞቹ ነገራቸው፡፡ እረኞቹም ተደሰቱ ፈጥነው ሕፃኑ ወደ ተወለደበት ወደ ቤተልሔም ሔዱ፡፡ መልአኩ ቦታውን ነግሯቸው ነበር፡፡ በዚያም ሲደርሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑን ታቅፋ አገኟት፡፡ በአጠገቧም አንድ ሽማግሌ ሰው ቆሞ ነበር፡፡ ያ ሽማግሌ እመቤታችንን ይጠብቃት የነበረው ዮሴፍ ነበር፡፡ እረኞቹም ወደ ሕፃኑ ቀርበው ሰገዱለት ምስጋናም አቀረቡ፡፡