Beke 1

በችግር ላይ የሚገኘው የበኬ ቅድስት ማርያም የአብነት ትምህርት ቤት እርዳታ ተደረገለት፡፡

ጥር 5/2004 ዓ.ም

በይበልጣል ሙላት
Beke 1

በአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል የተዘጋጀ ጉዞ ወደ በኬ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የአብነት ትምህርት ቤት የተካሔደ ሲሆን የጉዞውም ዋነኛ አላማ በአስከፊ ሁኔታ ላይ ለሚገኙት ለደብሯ የአብነት መምህራንና ተማሪዎች ጊዜያዊ የቁሳቁስ እርዳታ /ድጋፍ/ ለማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በጉዞውም በክፍሉ አስተባባሪነት ከምእመናንና ከማኅበሩ አባላት የተሰበሰቡና የተዘጋጁ  11 ኩንታል ስንዴ ዱቄት፣ 230 ሱሪ፣ 398 ሹራብና ቲሸርት፣ 145 ኮትና ጃኬት፣ 25 የአልጋ ልብስና አንሶላ፣ 43 የተለያዩ ልብሶች፣ 230 ግራም 249 የልብስ ሳሙና እና ለመማሪያ የሚሆኑ 11 መጻሕፍት ተበርክተዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በአብነት ትምህርት ቤቱ ከ160 በላይ ተማሪዎች በ3ቱ ጉባኤያት ማለትም በቅዳሴ፣ የአቋቋም እና የቅኔ ትምህርት በመማር ላይ የሚገኙ ሲሆን ከቅርብ ጊዜBeke 3  (1) በፊት ቁጥራቸው 300 ይደርስ እንደነበር የገለጹት በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት አባ ገ/አማኑኤል አሮጌ አያኔ እንዲህ ቁጥራቸው ሊቀንስ የቻለው በአብነት ትምህርት ቤቱ ባለው ስር የሰደደ ችግር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ በፊትም ሆነ አሁን ተማሪዎቹ ሲማሩ የነበሩትና በመማር ላይ የሚገኙት የቀን ሥራ እየሠሩ ሲሆን ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ እንደሌላቸውና ሲያገኙ በልተው ሲያጡ ጾማቸውን እያደሩ እንደሚማሩ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ጥሙን እርዛቱን መቋቋም ያልቻሉ ትምህርታቸውን እያቋረጡ የተሻለ እናገኛለን እያሉ መሔዳቸውን የደብሩ አስተዳዳሪ ገልጸው አያይዘውም በቦታው የድጓ መምህርና ተማሪዎች የነበሩ ሲሆን  ማለትም በምግብ፣ በልብስ፣ በመጠለያ ችግር ምክንያት ጉባኤው ሊበተን እንደቻለ አስታውሰዋል፡፡ ችግሩ በዚሁ ከቀጠለ አሁንም በመካሔድ ላይ ያሉት በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ልክ እንደ ድጓው ቁጥራቸው ቀንሶ የማይችልበት ምንም ምክንያት እንደማይኖር አስገንዝበዋል፡፡ ስለዚህ የሚመለከተው ሁሉ ከላይም ከታችም ከሊቅ እስከ ደቂቅ በጋራ ሁነን ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ጌጥ፣ ምንጭ የሆነውን የአብነት ትምህርት ቤት በተለይም በአሁኑ ሰዓት በአስከፊ ሁኔታ ላይ ለሚገኘው ለበኬ ቅድስት ማርያም አብነት ትምህርት ቤት ልንደርስለትና ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈለግለት በአብነት ትምህርት ቤቱ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም በቤተ ክርስቲያን ስም ተማጽኖአቸውን አቅርበዋል፡፡

Beke 4ይህንንም ጥሪ ሰምቶና አጣርቶ የአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል ከምእመኑና የማኅበሩ አባላት ጋር በመሆን ከላይ የተጠቀሰውን ጊዜያዊ ድጋፍ እንዳደረጉ የክፍሉ ተጠሪ ወ/ሪት መቅደስ አለሙ ገልጸዋል፡፡ ለወደፊትም የአብነት ትምህርቱን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከምእመኑና አባላቱ እና ድጋፍ ሰጪ አካላት ጋር በመተባበር ትልቅ የጉዞ መርሐ ግብር እንደሚያዘጋጅና ቋሚ ፕሮጀክት በመቅረጽ የአብነት ትምህርት ቤቱን የመጠለያና የምግብ ችግር ለመፍታት በመንቀሳቀስ ላይ እንዳለ የገለጹት የክፍሉ ተጠሪ  አያይዘውም ምእመኑና ድጋፍ ሰጭ አካላት በዚህ የተቀደሰ አላማ እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡

ከርክክቡ በኋላ ዐሳባቸውን የገለጹት አንዳንድ መምህራንና ተማሪዎች በተደረገላቸው ነገር ሁሉ መደሰታቸውን ነው፡፡

 

Beke 3  (2)የደብሩ የአቋቋም መምህር የሆኑ አባት ይህ የተደረገላቸው ድጋፍ በጣም ከመጠን በላይ እንዳስደሰታቸውና ለመግለጽ ቃላት እንደሚያጥራቸው ገልጸው ይህን ነገር እግዚአብሔር ተመልክቶ የበለጠ እንድትሠሩ ያደርጋል፤ ብለው አያይዘውም በቋሚነት ችግራቸው የሚፈታበትን መንገድ እንዲፈለግ ተማጽነዋል፡፡

 

የቅዳሴ ተማሪ የሆኑት አክሊለ ማርያም ይህ ከስጦታ ሁሉ በላይ እንደሆነና ከሁሉም በላይ ያስደሰታቸው የክርስቲያናዊ ወንድማማችነቱ የመጠያየቁ የአብሮነቱ እንዲሁም የመተሳሰቡ  ስሜት እንደሆነና ይህን ከላይ ከቤተ ክህነት ነበር የምንጠብቀው ብለው ተስፋችን ለምልሟል ልባችንም አርፏል በማለት ስሜታቸውን አጋርተዋል፡፡ አያይዘውም ለወደፊቱ በቋሚነት ልባችን ተረጋግቶ ጸንተን የምንማርበት ሁኔታ እንዲታሰብበት እና ዘላቂ መፍትሔ የሚመጣበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተማጽነዋል፡፡

 

በአጠቃላይ የአብነት ትምህርት ቤት ችግር የቤተ ክርስቲያን ችግር የቤተ ክርስቲያን የመኖርና ያለመኖር፣ የመሠረተ እምነቷ ችግር መሆኑን አውቆ ሁሉም የዚህ የአብነት ትምህርት ቤት ችግር እንዲቀረፍ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክትየአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል አስተባባሪዋ አሳስበዋል፡፡