theology1

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ 397 ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ


በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀን በማታና በርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት እሑድ ሰኔ 10 ቀን 2004 ዓ.ም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ፡፡

theology1

ኮሌጁ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሥር ሆኖ ከተቋቋመበት ከ1953 ዓ.ም ጀምሮ ለቅድስት ቤተክስቲያንና ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ደቀመዛሙርትን አሰልጥኖ ማውጣቱን የኮሌጁ ምክትል ዲን ዶክተር አባ ኃይለማርያም መለስ ለመካነድራችን ሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዶክተር አባ ኃይለማርያም በዚሁ መግለጫቸው፡-“የዘንድሮውን የምርቃት መርሐ ግብር ልዩ ከሚያደርጉት ነጥቦች አንዱ ከሌሎቹ ጊዜያት በተለየ መልኩ በቁጥር ከፍ ያሉ ሴት ተማሪዎች መመረቃቸው እና አብዛኛዎቹም የመአረግ ተመራቂዎች መሆናቸው ነው፡፡” ብለዋል፡፡

theologyከመንፈሳዊ ኮሌጁ የሬጅስትራር ጽ/ቤት ባገኘነው መረጃ በዚህ ዓመት በድኅረ ምረቃ ዲፕሎማ (P.G.D) 16፣ በዲግሪ 95፣በዲፕሎማ 72፣ በግእዝ ቋንቋ 14፣ እንዲሁም 200 ተማሪዎች በሰርተፍኬት መርሐ ግብር ተመርቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚህ ዓመት በደቀ መዝሙር ኢያሱ ጥጋቡ የተመዘገበው 3.98 ነጥብ በኮሌጁ ታሪክ እስከአሁን ከተመዘገቡት ከፍተኛው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በመንበረ ፓትርያርክ አካባቢ ራሳቸውን “ጉባኤ አርድዕት” ብለው የሰየሙ ቡድኖች እየተፈጠሩ መሆናቸው ተገለፀ፡፡

ሰኔ 09 ቀን 2004 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ባለፉት ረጅም ዓመታት በርካታ ፈተናዎችን አልፋ የተጓዘች መሆኗ ይታወቃል፡፡ በተለይም ራሳቸውን ተሐድሶ ብለው የሰየሙ ቡድኖች ተመሳስለው ውስጧ በመግባት ውስጥ ለውስጥ ሲያደሟት ቆይተዋል፡፡

የእነዚህ ድብቅ ቡድኖች አካሄድ ለብዙ ጠንካራ ኦርቶዶክሳውያን ግልፅ የነበረ በመሆኑ ላለፉት ተከታታይ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤያት ማንነታቸው ተገልጾ ውግዘት የተላለፈባቸውና በሕግ የሚጠየቁትም በሕግ እንዲጠየቁ መወሰኑ ይታወሳል፡፡

ነገር ግን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተገልጾ ለምዕመናን እንዲደርስ ለማድረግ ሰፊ ሥራ እየተሠራ ባለበት በአሁኑ ወቅት በ25 አባላት መሰራችነት የሚመራ አዲስ ቡድን በመንበረ ፓትርያርክ አካባቢ ብቅ ማለት ጀምሯል፡፡

የቡድኑ ዋና አላማ ነው ተብሎ ከተገለፀው መካከል የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሥራ ላይ እንዳይውል የሚያደርጉትን ጥፋት መደገፍና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሆኑ ሊቃነ ጳጳሳትን ከማስፈራራት ጀምሮ ማንኛውንም ጫና በማድረግ ሀሳባቸውን እንዲቀይሩ ማድረግ ነው ተብሏል፡፡

የጉባኤ አርድዕት መሪዎችና መስራቾች “ማኅበር ለቤተ ክርስቲያን አያስፈልግም” ብለው ሲሟገቱ የነበሩ ሲሆን ለእነርሱ እስከጠቀማቸው ድረስ “ጉባኤ አርድዕት” ወደ “ማኅበረ አርድዕት” ለመቀየር ሀሳብ ያላቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ziway abune gorgorios1

ዝክረ አቡነ ጎርጎርዮስ ሊካሄድ ነው

ሰኔ 09 ቀን 2004 ዓ.ም

በእንዳለ ደም

የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል የማኅበሩን 20ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ “ዝክረ አቡነ ጎርጎርዮስ” በሚል ርእስziway abune gorgorios1 የጥናትና የውይይት መድረክ ሰኔ 16 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም አዲሱ አዳራሽ አዘጋጅቷል፡፡

የጥናትና ምርምር ማእከሉ ም/ዳይሬክተር አቶ ሰይፉ አበበ መርሐ ግብሩን አስመልክቶ እንደገለጹት “የጥናት መድረኩ ዋና ዓላማ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሕይወት ዘመናቸው ለቤተ ክርስቲያን ያበረከቱትን አገልግሎት፣ የሕይወት ልምዳቸውን፣ ወጣቱን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በአንድ ዓላማ ለማሰለፍ ያደረጉትን ተጋድሎ እንዲሁም ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት የነበራቸውን ርዕይ የሚዘክር ይሆናል” ብለዋል፡፡

ziway abune gorgoriosበተጨማሪም ለማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ጉልህ አስተዋጽኦ የነበራቸው አባት በመሆናቸው ማኅበሩ 20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በሚያከብርበት ወቅት ብፁዕነታቸውን መዘከር ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ላይ ለሚገኙ አገልጋዮችና ደቀ መዛሙርቶቻቸው በተለይም ወጣቶችን የሚያተጋ በመሆኑ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ገልጸዋል፡፡

በጥናት መድረኩ ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ በዘርፉ የተሰማሩ ተመራማሪዎች፣ ደቀ መዛሙርቶቻቸው ፣ የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ምእመናን ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

library

ቤተ መጻሕፍቱ የመጻሕፍትና ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ፡፡

ሰኔ 04 ቀን 2004 ዓ.ም

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖአምላክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን ቤተ መጻሕፍት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ ለመቀጠል ይረዳው ዘንድ የመጻሐፍትና ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ፡፡

library

በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል ሥር የሚገኘው ቤተመጻሕፍት ፡-“ስትመጣ …በርኖሱንና መጻሕፍቱን ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ” (2ኛ ጢሞ.4÷13) በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው በዚሁ የመጻሐፍትና ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር፡-

 

•    ሃይማኖታዊ፣ ታሪካዊ፣ ምክርና ትምህርት የሚሰጡ መጻሕፍት፣ መዛግብት፣ መጽሔቶችና ጋዜጦችን፣ የአስኳላ (አካዳሚካል) መጻሕፍት፣
•    ጥናታዊ ጹሑፎችን እንዲሁም
•    ቤተመጻሕፍቱን ለማደራጀት የሚያግዙ ቁሳቁሶችን በመስጠት ምእመናን የበኩላቸውን እገዛ እንዲያበረክቱ ጠይቋል፡፡

 

‹‹ቤተመጽሐፍቱ ቅዳሜን ጨምሮ በሌሎቹም መደበኛ የሥራ ቀናት ለአንባቢያን አገልግሎት እየሰጠ ነው፤›› ያሉት  የቤተ መጻሕፍት አገልጋይ  አቶ ደጀኔ ፈጠነ፤ በአሁኑ ወቅት በርካታ አንባቢያን በቤተ መጻሕፍቱ እየተጠቀሙ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ስለመርሐ ግብሩ ዓላማ የተጠየቁት አቶ ደጀኔ “ ቤተ መጻሕፍቱን በመጻሕፍት ዓይነትና ብዛት ክምችቱን ማሳደግ÷ አገልግሎቱን በኮምፒውተር የታገዘ÷ አስፈላጊ በሆኑ የመገልገያ መሣሪያዎች የተሟላ፤ ለተገልጋዮችም ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን ሁኔታ ማመቻቸት የመርሐ ግብሩ ዓላማ ነው፡፡” ብለዋል፡፡

ለለጋሾች በቀላሉ መጻሕፍትን ገዝተው ማበርከት ይችሉ ዘንድ በማኅበሩ ሕንፃ ከተዘጋጀው ጊዜያዊ ሽያጭ በተጨማሪ አዲስ አበባ በሚገኙ የማኅበሩ ሱቁች የሽያጭና የመረከብ አገልግሎት ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡

ከሰኔ 7 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2004 ዓ.ም ድረስ በሚቆየዉ መርሐ ግብር በርካታ መጻሕፍት፣መጽሔቶችና ለቤተመጻሐፍት አገልግሎት የሚረዱ ኮምፒውተሮች፣ ወንበሮች፣ ጠረጴዛዎች፣ መደርደሪያዎችና ሌሎች አስፈላጊ መገልገያዎችን  ለማሰባሰብ ታቅዷል፡፡

mk20thyearCD

ኢንኅድግ ማኅበረነ

mk20thyearCD

የማኅበሩ 20ኛ አመት ምሥረታ ተከበረ

ግንቦት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ አመት የምሥረታ በኣል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. ተከበረ፡፡ ከረፋዱ 4፡ 00 ስኣት ጀምሮ የተካሔደው መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የኢሉባቦርና ጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ መሪነት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ  ተከፍቷል፡፡

ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን ‹‹ ክርስቶስ ወደዚህ አለም ሳይመጣ ፤ወንጌል ከመሰበኩ በፊት እግዚአብሔርን አምነን የተገኘን እትዮጵያውያን ነን፡፡ እግዚአብሔር ምስጢሩን ፤ጥበቡን የገለጠውና ያረጋገጠው ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንና ለኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ነው፡፡ ስለ  ምሥጢረ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  የሚስተካከልና የሚተካ አንድም የለም፡፡ ቤተክርስቲያን ራሷን ከቻለችበት ጊዜ አንስቶ በሊቃውንት ፤ በመምህራን ተጠብቃ አስተምህሮውንም አመስጥራ ፤ተርጉማ የተገኘች ናት በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ብፁዕነታቸው ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት  ‹‹ ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ምእመናን ከዓላማውና ከእንቅስቃሴው ጎን  ናቸው” ብለዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያን የፈተና ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበሩ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳትወድቅ ፤ፈታኝ እንዳይጥላት እግዚአብሔር ያቋቋመው ማኅበር ነው፡፡ አባቶች ያላዩትን ወጣቶች ሲሰሩት በጣም ያስደስታል፡፡ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገዳማት ፤አድባራትና አብነት ት/ቤቶች ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ማህበር የአባቶችን አደራ እየተወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ አምናለሁም በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ‹‹ ነፋስ ይነፍሳል፤ ወደ ወደደው ይነጉዳል ፤ድምጹን ትሰማላችሁ፡፡ ብዙ ወጀብ ፤ብዙ ንፋስ አለ በዘመናችን፡፡ ወጣቶችን የሚያምታታ፤ እምነት የሚያሳጣ፡፡ ያ! ሁሉ ሳይበግራችሁ በዚህ ማኅበር አንድ ሆናችሁ እምነታችሁን ይዛችሁ፤ ለሌሎችም እየመሰከራችሁና እያስመሰከራችሁ ስለምትገኙ በራሴና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ›› ብለዋል፡፡

በጉባኤው ላይ  ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የከምባታ ሃዲያ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ፤ብፁዕ አቡነ እንባቆም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤  የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ የሰ/ት/ቤቶች አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የሕይወት ታሪክ ፤ የማኅበሩ የ20 አመት ጉዞ ፤ ያሬዳዊ ዝማሬ፤ ግጥምና ሌሎች መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል፡፡

የማኅበሩ 20ኛ አመት ምሥረታ በድምቀት ተከበረ
ግንቦት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.                                                                                     በእንዳለ ደምስስ
የማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ አመት የምሥረታ በኣል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. በድምቀት ተከበረ፡፡ ከረፋዱ 4፡ 00 ስኣት ጀምሮ የተካሔደው መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የኢሉባቦርና ጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ መሪነት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ  ተከፍቷል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን ‹‹ ክርስቶስ ወደዚህ አለም ሳይመጣ ፤ወንጌል ከመሰበኩ በፊት እግዚአብሔርን አምነን የተገኘን እትዮጵያውያን ነን፡፡ እግዚአብሔር ምስጢሩን ፤ጥበቡን የገለጠውና ያረጋገጠው ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንና ለኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ነው፡፡ ስለ  ምሥጢረ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  የሚስተካከልና የሚተካ አንድም የለም፡፡ ቤተክርስቲያን ራሷን ከቻለችበት ጊዜ አንስቶ በሊቃውንት ፤ በመምህራን ተጠብቃ አስተምህሮውንም አመስጥራ ፤ተርጉማ የተገኘች ናት በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ብፁዕነታቸው ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት  ‹‹ ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ምእመናን ከዓላማውና ከእንቅስቃሴው ጎን  ናቸው” ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያን የፈተና ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበሩ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳትወድቅ ፤ፈታኝ እንዳይጥላት እግዚአብሔር ያቋቋመው ማኅበር ነው፡፡ አባቶች ያላዩትን ወጣቶች ሲሰሩት በጣም ያስደስታል፡፡ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገዳማት ፤አድባራትና አብነት ት/ቤቶች ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ማህበር የአባቶችን አደራ እየተወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ አምናለሁም በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ‹‹ ነፋስ ይነፍሳል፤ ወደ ወደደው ይነጉዳል ፤ድምጹን ትሰማላችሁ፡፡ ብዙ ወጀብ ፤ብዙ ንፋስ አለ በዘመናችን፡፡ ወጣቶችን የሚያምታታ፤ እምነት የሚያሳጣ፡፡ ያ! ሁሉ ሳይበግራችሁ በዚህ ማኅበር አንድ ሆናችሁ እምነታችሁን ይዛችሁ፤ ለሌሎችም እየመሰከራችሁና እያስመሰከራችሁ ስለምትገኙ በራሴና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ›› ብለዋል፡፡
በጉባኤው ላይ  ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የከምባታ ሃዲያ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ፤ብፁዕ አቡነ እንባቆም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤  የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ የሰ/ት/ቤቶች አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የሕይወት ታሪክ ፤ የማኅበሩ የ20 አመት ጉዞ ፤ ያሬዳዊ ዝማሬ፤ ግጥምና ሌሎች መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል፡፡
የማኅበሩ 20ኛ አመት ምሥረታ በድምቀት ተከበረ
ግንቦት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.                                                                                     በእንዳለ ደምስስ
የማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ አመት የምሥረታ በኣል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. በድምቀት ተከበረ፡፡ ከረፋዱ 4፡ 00 ስኣት ጀምሮ የተካሔደው መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የኢሉባቦርና ጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ መሪነት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ  ተከፍቷል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን ‹‹ ክርስቶስ ወደዚህ አለም ሳይመጣ ፤ወንጌል ከመሰበኩ በፊት እግዚአብሔርን አምነን የተገኘን እትዮጵያውያን ነን፡፡ እግዚአብሔር ምስጢሩን ፤ጥበቡን የገለጠውና ያረጋገጠው ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንና ለኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ነው፡፡ ስለ  ምሥጢረ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  የሚስተካከልና የሚተካ አንድም የለም፡፡ ቤተክርስቲያን ራሷን ከቻለችበት ጊዜ አንስቶ በሊቃውንት ፤ በመምህራን ተጠብቃ አስተምህሮውንም አመስጥራ ፤ተርጉማ የተገኘች ናት በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ብፁዕነታቸው ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት  ‹‹ ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ምእመናን ከዓላማውና ከእንቅስቃሴው ጎን  ናቸው” ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያን የፈተና ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበሩ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳትወድቅ ፤ፈታኝ እንዳይጥላት እግዚአብሔር ያቋቋመው ማኅበር ነው፡፡ አባቶች ያላዩትን ወጣቶች ሲሰሩት በጣም ያስደስታል፡፡ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገዳማት ፤አድባራትና አብነት ት/ቤቶች ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ማህበር የአባቶችን አደራ እየተወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ አምናለሁም በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ‹‹ ነፋስ ይነፍሳል፤ ወደ ወደደው ይነጉዳል ፤ድምጹን ትሰማላችሁ፡፡ ብዙ ወጀብ ፤ብዙ ንፋስ አለ በዘመናችን፡፡ ወጣቶችን የሚያምታታ፤ እምነት የሚያሳጣ፡፡ ያ! ሁሉ ሳይበግራችሁ በዚህ ማኅበር አንድ ሆናችሁ እምነታችሁን ይዛችሁ፤ ለሌሎችም እየመሰከራችሁና እያስመሰከራችሁ ስለምትገኙ በራሴና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ›› ብለዋል፡፡
በጉባኤው ላይ  ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የከምባታ ሃዲያ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ፤ብፁዕ አቡነ እንባቆም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤  የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ የሰ/ት/ቤቶች አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የሕይወት ታሪክ ፤ የማኅበሩ የ20 አመት ጉዞ ፤ ያሬዳዊ ዝማሬ፤ ግጥምና ሌሎች መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል፡፡

sundayscl

አገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ እየተካሔደ ነው፡፡

ግንቦት 25 ቀን 2004 ዓ.ም

ዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖአምላክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ አስተባባሪነት አገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መሥራች ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ እየተካሔደ ነው፡፡

sundayscl

በ48 አህጉረ ስብከቶች የሚገኙ የሰ/ት/ቤት ኃላፊዎችና ከ160 ሰ/ት/ቤቶች የተውጣጡ የየሰንበት ትምህርት ቤቱ የሥራ አመራር  አካላት የተገኙበት ጉባኤ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንትና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ዛሬ ግንቦት 25 ቀን 2004 ዓ.ም ረፋድ 4፡30 በጸሎት ተከፍቷል፡፡

በጉባኤው መክፈቻ ላይ የዐቢይ ኮሚቴውን መልእክት በንባብ ያቀረቡት ዲ/ን በላይ ገብረሕይወት “ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሕፃናትና ወጣቶችን የሚያቅፍ መዋቅር ሰንበት ት/ቤት አዋቅራ ልጆቿን ስታስተምር ቆይታለች፡፡ ልጆቿም ቃሏን ሰምተው ሥርዓቷን እያከበሩ በሰንበት ትምህርት ቤት ታቅፈው ሲያገለግሉ አርባ ዓመታት አልፈዋል፡፡ በእነዚህ አርባ ዓመታትም በክፉም ሆነ በደጉም ሁኔታ በጉልበታቸው በዕውቀታቸው ቤተክርስቲያንን እያገለገሉ ብዙዎች አልፈው ይህ ሂደት እኛ ጋር ደርሷል፡፡ይህ በቅንነት ላይ የተመሠረተ አገልግሎት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለማበርከት እንደነዚህ ያሉ የአንድነት ጉባዔያት ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው፡፡ ” ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመላው ዐለም ከ7 ሚሊየን በላይ የተመዘገቡ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዳሏት የገለጹት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ  መምህር እንቈባሕርይ ተከስተ፡-“የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ5 ዓመታት ሀገር አቀፍ መሪ ዕቅድ ላይ ለመወያየት ከመላ ሃገሪቱ ከ600 በላይ የሰንበት ት/ቤት ኃላፊዎች የዚሁ ጉባኤ  ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ይህ ጉባኤ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ጉባኤው የ5 ዓመታት መሪ ዕቅዱን መርምሮና አዳብሮ እንደሚያጸድቀው ይጠበቃል፡ብለዋል፡፡

ከሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ  ንግግር በኋላ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የድሬዳዋ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስና የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት የውጭ ግንኙነት የበላይ ኃላፊ የበዓለ ሃምሳን በተመለከተ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡

ከብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገሪማ በመቀጠል የጉባኤውን መጀመር በይፋ ያበሰሩት ቃለምዕዳን ያሰሙት ቅዱስ ፓትርያርኩ፡-˝ ይህ ዓይነት ስብሰባ ተገቢና ከተገቢም በላይ ነው፡… አትዮጵያውያን ወጣቶች በቤተክርሰቲያን ሊገኙ ይገባቸዋል ፤ ግዴታቸውም ነው፡፡˝  በማለት ጉባኤው የሰመረ እንዲሆን ልባዊ ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

የጠዋቱ መርሐ ግብር ከመጠናቀቁ በፊት ˝የወጣቱ አስተዋጽኦ በቤተክርስቲያን˝ በሚል ርዕስ ዲያቆን ዶ/ር ያየህ ነጋሽ ያዘጋጁትን ጥናታዊsundayscl1 ጽሑፍ አቅርበዋል፡፡

•    አጠቃላይ የወጣቱ አኗኗርና ፈተናዎቹ፤

•    በመፍትሔው ረገድ የቤተ ክርስቲያን ድርሻን መጠቆም

•    በቤተ ክርስቲያን የወጣቱን አስተዋጽኦ መጠቆም …   የጥናታዊው ጽሑፍ ዓላማ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡

ዲ/ን ዶክተር ያየህ ነጋሽ ፡-˝በሰንበት ትምህርት ቤት የዕድሜ ገደብ ዙሪያ የሚነሳው አለመግባባትና የትምህርቱ በዕድሜ በጾታ ተለይቶ በሥርዐተ ትምህርት አለመዘጋጀቱ የሰንበት ት/ቤት አገልግሎት ተግዳሮቶች ናቸው፤˝ ብለዋል ፡፡ ˝ የሰንበት ትምህርት ቤቶችንና የወጣቶችን ተግዳሮቶች ከመቅረፍ አንጻር ዋነኛዋ ባለ ድርሻ ቤተክርስቲያን ናት፤˝ የሚሉት ጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢው፡-˝ ይህንን ድርሻዋን ለመወጣት ቤተክርስቲያን ለሰንበት ት/ቤት ከፍተኛ ትኩረት መስጠት አለባት” በማለት አሳስበዋል፡፡

በጉባዔው ላይ አግኝተን ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ ዲያቆን ሔኖክ አሥራት ˝የዚህ ጉባኤ መካሄድ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ አዳዲስ የሚቋቋሙ ሰ/ት/ቤቶች ከነባሮቹ ልምድና ልዩ ልዩ እገዛ እንዲያገኙ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡” ብሏል፡፡

ዛሬ ረፋድ ላይ የተጀመረው ጉባዔ የሚጠናቀቀው ነገ ግንቦት 26ቀን 2004 ዓ.ም ከቀትር በኋላ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኒዓለም ቤተክርስቲያን በሚካሄደው ጉባኤ እንደሆነ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች ለጉባኤው ከሰጡት መግለጫ ለመረዳት ችለናል፡፡

በዓሉን ለማክበር ርብርቡ ቀጥሏል

ግንቦት 25 ቀን 2004 ዓ.ም

የማኅበሩ 20ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል የእግር ጉዞ በማዘጋጀት አዲሱ ገበያ አካባቢ በሚገኘው በመንበረ ክቡር ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለማክበር ቀደም ብሎ የታቀደ ቢሆንም መርሐ ግብሩ እሑድ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ ለማክበር ተወስኗል፡፡ በዚህም መሠረት መርሐ ግብሩን የተሳካ ለማድረግ የተግባር ቤት (ምግብ ዝግጅት) አገልግሎት እየተቀላጠፈ ይገኛል፡፡ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ ድንኳን በመትከልና ሌሎችም ቅድመ ዝግጅቶች በመካሔድ ላይ ናቸው፡፡

ነገ የሚካሔደውን መርሐ ግብር በማኅበሩ መካነ ድር www.eotcmk.org እና በፌስ ቡክ http://www.facebook.com/mahiberekidusan በቀጥታ ስርጭት የምናስተላልፍ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}mk20th year{/gallery}

 

mk 20th year

ሰበር ዜና፡ የእግር ጉዞው መርሐ ግብር ተቀየረ፡፡

ግንቦት 24 ቀን 2004 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስስ

  • መርሐ ግብሩ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ ይካሔዳል፡፡

mk 20th yearግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም ከማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓል ጋር ተያይዞ ሊካሔድ የነበረው የእግር ጉዞ መርሐ ግብር ጠቅላይ ቤተ ክህነት መጻፍ ያለበትን ደብደቤ ባለመጻፉ በታቀደለት  መሠረት ሊከናወን አልቻለም፡፡ መርሐ ግብሩ እሑድ ጠዋት ከ 3፡00 ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ በድምቀት ይከበራል፡፡

 

መርሐ ግብሩ አዲሱ ገበያ አካባቢ በሚገኘው መንበረ ክቡር ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ለማካሄድ እንደ ታቀደ አስታውሰን ለምን እንደተቀየረ ላቀረብንላቸው ጥያቄ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ሲመልሱ “ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በጻፍነው ደብዳቤ ሚያዝያ 27 ቀን 2004 ዓ.ም የእግር ጉዞ እንደምናካሂድ ያሳወቅን ሲሆን ነገር ግን ምእመናን ቀኑ እንዲራዘምላችው በመጠየቃቸው ጉዞው ወደ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም እንዲቀየር ጠይቀናል፡፡ ጉዳዩ በዚህ ሁኔታ ላይ እንዳለ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ደረሰ፡፡ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ማኅበረ ቅዱሳንም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሆን ተወሰነ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ተጠሪነታችን ለጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆኑ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ጉዞውን ለማካሔድ እንድንችል እንዲጻፍልን ጠይቀናል ብለዋል፡፡

 

የጉዞው አስተባባሪ ዲ/ን ዋሲሁን በላይ አያይዘው እንዳስረዱት ከሆነ በብፁዕ  የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊ ፊርማ የወጣው የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መዝገብ ቤት ገብቶ ወደሚመለከታቸው ክፍሎች እንዳይደርስ ´የመዝገብ ቤት ሰራተኞች ደብዳቤው እንዳይወጣ ከበላይ ታዘናል በሚል ደብዳቤው አልወጣም፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ የያዘው ደብዳቤ የጠቅላይ ቤተክህነት የአስተዳደር ሃላፊዎችም አልደረሰንም በሚል እስካሁን ሊጓተት ችሏል፡፡በዚህም ምክንያት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደብዳቤ ለመጻፍ አልቻልንም፡፡”

 

‹‹ነገር ግን መርሐ ግብሩ በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ውስጥ እንዲካሔድ ስለተፈቀደ እሑድ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. ከጧቱ 3፡00 ስዓት መርሐ ግብሮቹ እንደተጠበቁ ይከናወናሉ፡፡ ይህንን የጉዞ መርሐ ግብር በታቀደለት መሰረት ማካሔድ ባለመቻላችን ምእመናንን ይቅርታ እየጠየቅን የጉዞውን ቦታ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዛውረናል፡፡እሁድ ከጧቱ 3፡00 ስዓት ጀምሮ በሚካሔደው መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ውስጥ በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ዋና ጸሐፊው አስታውቀዋል፡፡››

በጎ አድራጊ ምእመናን ለማኅበሩ ሕንፃ ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አደረጉ፡፡

ግንቦት 22/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

•    የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በዮድ አቢሲንያ ተካሄዷል፡፡
•   “ቅዱስ ሲኖዶስ ከእናንተ ጋር ነው፡፡”ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ
•   “ይህን ቤት ለመሥራት የነበረው ውጣ ውረድ፣ የደረሰባቸሁ መከራ ብ
ዙ ነው፡፡ ብዙውን ፈተና አልፋችሁታል፡፡” ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ፡፡

በግንባታ ላይ የሚገኘውን የማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት ሕንፃ ማስፈጸሚያ የሚውል በበጎ አድራጊ ምእመናን አነሣሽነትና አስተባባሪነት ሰኞ ግንቦት 20 ቀን 2004 ዓ.ም. ቦሌ በሚገኘው ዮድ አቢሲንያ የባሕል ምግብ ቤት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡መርሐ ግብሩ በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በጸሎት የተከፈተ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ረዳትና የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የኢሉባቦርና የጋምቤላ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ ማኅበረ ቅዱሳንንና የማኅበረ ቅዱሳንን እንቅስቃሴ ለመደገፍ በራሳቸው ፍላጎት የተሰበሰቡትን በጎ አድራጊ ባለሀብቶችንና ምእመናንን አመስግነዋል፡፡ በሰጡት ቃለምእዳን፡፡ “መንፈሰ ጠንካሮች ሁኑ፣ በማንኛውም በኩል እንዳትበገሩ፡፡ እኛ በእናንተ ልበ ሙሉ ነን፡፡ እምነታችሁ ጠንካራ ነው፡፡ ሃይማኖት ካለ ማንኛውንም ነገር መሥራት ይቻላል፡፡ እንመካባችኋለን፡፡ ከእኛ ይልቅ ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቃላችሁ፡፡ ይህ ቤት ለመሥራት የነበረው ውጣ ውረድ፣ የደረሰባችሁ መከራ ብዙ ነው፡፡ ብዙውን ፈተና አልፋችኋል፡፡ በዚህ ሳልፍ በጅምር ያለውን ሕንፃ እያየሁ ገንዘብ አጡ ማለት ነው? አቃታቸው እያልኩ ከራሴ ጋር እሟገት ነበር፡፡ ረዳት አጡ? መቼ ይሆን የሚፈጸመው? እነዚህ ልጆች ያሳፍሩን ይሆን እንዴ እያልኩ እሟገታለሁ፡፡ እኔ ተሸጬ ሁሉም ነገር በሆነ፡፡ ሽማግሌን ማን ይገዛል? እግዚአብሔር ሆይ እርዳቸው፣ ቅድስተ ቅዱሳን በደጅሽ ነው ያሉት በረድኤትሽ እርጃቸው እያልኩ ስጸልይ ነው የኖርኩት፡፡ ተስፋ አለን፡፡ ዛሬ የተሰበሰባችሁት ትጨርሱታላችሁ” በማለት አባታዊ ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ፊልጶስም በሰጡት ቃለ ምእዳን እነዚህ ልጆቻችን በትእግሥት ሁሉን አሳልፈው፣ ድል መትተው፣ ድል ተጎናጽፈው እዚህ በመድረሳቸው እግዚአብሔር ከእነሱ ጋር መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሰው የሚታወቀው በሥራው በእምነቱ፣ በአቋሙ ነው፡፡ እነዚህ ልጆቻችን ካየናቸው ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ ያላሉ እንደብረት ምሰሶ የሆኑ፣ አንድነታቸውን አጠናክረው አዋሕደው ወደፊት እንጂ ወደ ኋላ የማይሉ፣ የመጣባቸውንና የሚመጣባቸውን ሁሉ ፈተና በጣጥሰው ያለፉና የሚያልፉ ለሁላችን አብነት የሚሆኑን ለቤተ ክርስቲያናችን መኩሪያና መመኪያዎች ናቸው፡፡ ታግለው ሩጠው እዚህ በመድረሳቸው እግዚአብሔርን ልናመሰግን ይገባል ብለዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አያይዘውም ማኅበረ ቅዱሳን ልጆቻችን 20 ዓመታትን ታግላችሁ አልፋችሁ እዚህ ደርሳችኋል፡፡ ወደፊት ደግሞ የት እንደምትደርሱ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ በርቱ ጠንክሩ፡፡ በርትታችሁ ከሠራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ ከእናንተ ጋር ይሠራል በማለት ማኅበሩን ያበረታቱ ሲሆን በጎ አድራጊ ምእመናን አስመልክቶም እግዚአብሔር በሰጣችሁ ለቤተ ክርስቲያናችሁ፣ ለእምነታችሁ ለታሪካችሁ፣ ለባሕላችሁና ለቅርሳችሁ ካላችሁ ላይ መስጠት፣ መለገስ እናንተን ብፁዓን ያሰኛችኋልና ስጡ ብለዋል፡፡

 

የመርሐ ግብሩ አስተባባሪና የበጎ አድራጊዎቹ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደርቤ ሥነ ጊዮርጊስ መርሐ ግብሩ የተዘጋጀበት ዋነኛ ምክንያት ሲገልጹ “ ማኅበረ ቅዱሳንን ለአራት ዓመታት ያህል በጥልቀት የሚሠራውን ሥራ ለመከታተል ጥረት አድርገናል፡፡ ምንድነው የሚሠሩት? እንዴት ነው ሥራቸውን የሚሠሩት ብለን አጠናን፡፡ 7 የቤተ ክርስቲያን ወንድማማቾች በመሠባሰብ ውይይት አደረግን፡፡ እንዴት ዝም ብለን እንመለከታለን? ይህ ሕንፃ ከተጀመረ 10 ዓመት ሞላው፡፡ ሊጨርሱት አልቻሉም ስለዚህ ለምን እኛ አናስጨርሳቸውም? በማለት የማኅበሩን ጥረት ለማገዝ ተስማማን፡፡ በጀታቸውን ለገዳማትና አድባራት፣ ለአብነት ትምህርት ቤቶች ለሕንፃ ግንባታ ያውሉታል፡፡ ሥራቸውን እየሠሩ ያሉት አቧራ እየጠረጉ ነው፡፡ የምንችለውን ሁሉ አድርገን ይህንን ሕንፃ እናስጨርሳቸው የሚል ዓላማ ያዝን ወንድማችን አቶ ትእዛዙ ኮሬ የዮድ አቢሲንያ የባሕል ምግብ ቤት ባለቤትም `ምእመናንን አሰባስቡ የምግብ ቤቱን አዳራሸና ሙሉ የምሳ ወጪውን እችላለሁ´ በማለቱ የዛሬውን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀነው፡፡” በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም  20 ዓመታት ምንም ሳይረዱ እዚህ ከደረሱ ሕንጻውን አስጨርሰን የቢሮ መሣሪያዎችን ብናሟላላቸው፣ ከጀርባቸው ሆነን ከደገፍናቸው ታላቅ ሥራ ይሠራሉ ብለን እናምናለን፡፡ ማኀበረ ቅዱሳን በእሳት የተፈተነ ወርቅ ነው፡፡ በዚህ ዘመን የተሰጠን ታላቅ ማኅበር ነው፡፡ በጸሎታችሁ ማኅበሩን ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ የምንችለውን ሁሉ አድርገን ማኅበሩን እንደግፍ፣ ከጎኑ እንሰለፍ፡፡ ይህ ኮሚቴ እስከ መጨረሻው ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ለመጓዝ ወስኗል ብለዋል፡፡

 

የዮድ አቢሲንያ የባሕል ምግብ ቤት ባለቤት አቶ ትእዛዙ ኮሬ በበኩላቸው የዛሬውን መርሐ ግብር ለማዘጋጀት ምን እንዳነሳሳቸው ሲገልጹ ሁላችንም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ነን፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን የሚሠራውን ሥራ በቅርበት ስንከታተል ቆይተናል፡፡ በየገዳማቱ ያሉትን ችግሮች ለማቃለል፣ የአብነት ት/ቤቶችን ለማጠናከር እያደረገ ያለው ጥረት ተመልክተናል፡፡ ከወር ደመወዛቸው እየቆጠቡ የሚያደርጉትን በመመልከት በተለይም በንግዱ ውስጥ ያለነው የቤተ ክርስቲያን ልጆች እንዴት እንርዳቸው በማለት ለሚፈጽሙት በጎ ሥራ ለማገዝ ነው የተነሳነው፡፡ አቅም በፈቀደ መጠን የድርሻችንን ለመወጣት ይህ ጅምር ነው፡፡ ወደፊት ብዙ ነገሮችን በጋራ እንሠራለን በማለት ገልጸዋል፡፡

 

ቀሲስ ዶ/ር ሰሙ ምትኩ ቤተ ክርስቲያናችን ወደፊት ምን ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚገባት ያመለከተ ጥናት በአጭሩ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁል ጊዜ ስንዱ እመቤት ናት፡፡ የጎደላት አለ አንልም፡፡ ነገር ግን ሁለንተናዊ እድገት ያስፈለጋታል፡፡ እድገቱ የሁላችንም እንደሆነና እኛም ቤተ ክርስቲያን ሆና እንድናያት የምንመኘው ደረጃ እንድትደርስ መጣር አለብን ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ እድገት ያስፈልጋታል ያሏቸውን ዝርዝር ነጥቦችን በመጥቀስ አቅርበዋል፡፡

 

ዶ/ር የራስ ወርቅ አድማሴ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጡትን ምሁራንን በመወከል ባሰሙት ንግግር እንደ ማኅበረ ቅዱሳን ያለ የተደራጀ አካል ሲኖር ቤተ ክርስቲያናችንን ከአደጋ ለማዳን ከጎኑ ልንሆን ይገባል፡፡ ምሁራን የነፃ እውቀት አገልግሎት በመስጠት፣ ባለሀብቱ ደግሞ ገንዘብ በመለገስ ከፍተኛ ሥራ መሥራት ይቻላል፡፡ የሁኔታዎች መቀያየር ከግንዛቤ በማስገባት በፍጥነት ያለንን የአእምሮ፣ የገንዘብና የጉልበት ኀይል አስተባብረን ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር አብረን መሥራት አለብን በማለት ገልጸዋል፡፡

 

በመርሐ ግብሩ ላይ የገቢ ማሰባሰቢያ የቃል ኪዳን መግቢያ ሰነድ በአስተባባሪ ኮሚቴው ተሠራጭቷል፡፡ ምእመናንም እንደ አቅማቸው ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡ በመጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ የወንጌል ትምህርት የተሰጠ ሲሆን “ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት አብረን እንሥራ” በሚል ርእስ በቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የተዘጋጀ ገዳማት በአሁኑ ወቅት ያሉበትን አሳሳቢ ሁኔት የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ቀርቧል፡፡ እንዲሁም ተዋሕዶ የተሰኘ መንፈሳዊ ድራማ በታዋቂ አርቲስቶች የቀረበ ሲሆን ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስና ዘማሪት ማርታ ኀ/ሥላሴ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ታላላቅ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሁራን፣ ባለሀብቶችና ምእመናን የተገኙ ሲሆን በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና ጸሎት መርሐ ግብሩ እንደ ተጠናቀቀ የምሳ ግብዣው ተካሂዷል፡፡