የማኅበሩ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተራዘመ

ኅዳር 11 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የማኅበረ ቅዱሳን የኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል በኢቢኤስ የቴሌቪዥን መርሐ ግብር ለመጀመር ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በእኛ በኩል ዝግጅታችንን ለመጀመር ዝግጁ ሆነን እየተጠባበቅን የምንገኝ ሲሆን ከኢቢ ኤስ ቴሌቪዥን  በኢትዮጵያና በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት የጀመረው ስርጭት ከኅዳር 5 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ካልታወቀ አቅጣጫ በተደረገ ከፍተኛ የሳተላይት ሲግናል ማዛባትና እቀባ ወይም “ጃሚንግ” እክል እንደደረሰበት አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ስርጭቱ እንደተስተካከለ የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መርሐ ግብር የሚቀጥል ሲሆን በትእግሥት እንድትጠባበቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡