ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የጾመ ፍልስታ ወቅት እንዴት ነበር? እንኳን አደረሳችሁ! የክረምት ወቅት አልፎ አዲሱን ዓመት ልንቀበል ቀናት ብቻ ቀርተውናል! እህቶቻችንን ለዚህ ያደረሰንን ፈጣሪ በዝማሬ ያመሰግናሉ፤ ልጆች! ለመሆኑ አበባ አየሽ ወይ? እያልን የምንዘምረው “የተዘራው ዘር በቅሎ ቅጠል ከዚያም ደግሞ አበባን ሰጥቷል፤ ቀጥሎ ደግሞ ፍሬን ይሰጣል” በማለት የምሥራችን እያበሠሩ ለዚህ ያደለንን ፈጣሪ ያመሰግናሉ፡፡ ልጆች! ሌላው ደግሞ መዘንጋት የሌለባችሁ ነገር ለመጪው የትምህርት ዘመን ዝግጅት ማድረግ እንዳለባችሁ ነው፤ መልካም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ነው፤