Entries by Mahibere Kidusan

የዩኒቨርሲቲዎች የታሪክ እይታ ከድጥ ወደ ማጡ

በመጀመሪያ ደረጃ ቤተ ክርስቲያን መንግሥትን እየተከተለች፣ በጦር እያስፈራራች ሃይማኖቷን እንዳስፋፋች አድርጎ ማቅረብ የተዛባ አስተሳሰብ የወለደው መሆኑን መናገር እንፈልጋለን። ይህ ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያኗን ታሪክ በማዛባት የቀረበው ሐሳብ እንዲስተካከል እንጠይቃለን። እውነቱ ግን በተቃራኒው ነው። ቤተ ክርስቲያን ያለሰለሰችው የአረማውያን እና የአሕዛብ ልቡና ወደ ማእከላዊ መንግሥት ለመታቀፍ እንዳላስቸገረ እና መንግሥት የራሱን ሥራ ለመሥራት እንዳገዘው መረዳት ይገባል። ያለፈው ሥርዓት ፈጽሞታል ለሚሉት ጥፋት ቤተ ክርስቲያንን ተጠያቂ ማድረግ አንደበቷን ዘግታ እንድትቀመጥ ለማድረግ የተሸረበ ሴራ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል። ገለጻው እውነታን ያላገናዘበ መሆኑን መረዳት እና ተገቢውን መልስ መስጠት አስፈላጊ ሲሆን በሕግ መጠየቅ ይገባል።

የዩኒቨርሲቲዎች የታሪክ እይታ ከድጥ ወደ ማጡ

የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በአራት የዩኒቨርሲቲ መምህራን “የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ፤The History of Ethiopia and the Horn” በሚል እርስ ለመጀመሪያ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማስተማሪያ የሚሆን ጥራዝ አዘጋጅቷል። ዝግጅቱ ለመስከረም አልደርስ ብሎ ይሁን ሌላ ምክንያት ኖሮት ባይታወቅም ለሁለተኛው መንፈቀ ዓመት ሊሰጥ መታሰቡ ተሰምቷል። ስርጭት ላይ ሊውል የተቃረበ የሚመስለው ጥራዝ በሙያው ብቃት ባላቸው ምሁራን መዘጋጀቱም ተገልጧል፡፡ የታሪክ ትምህርት እንዳይሰጥ ተከልክሎ የቆየው የገዥው መደብ መጠቀሚያ ሆኖ ስለኖረ እንደ ገና በአዲስ መልክ መጻፍ አለበት ተብሎ መሆኑን ልብ ማለት ይገባል።

‹‹አንተም÷ የሰው ልጅ ሆይ÷ ጡቡን ወስደህ በፊት አኑራት፤ የኢየሩሳሌምንም ከተማ ስዕል ሳልባት፤ ክበባት›› (ሕዝ.፬፥፩)

ቅዱሳት ሥዕላትን ለጸሎት እና ለተለያዩ አገልግሎቶች በምንጠቀምበት ጊዜ ልናስተውላቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ፡፡ በዋነኛነትም እንዳይበላሹ እና እንዳይደበዝዙ በክብር ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው፡፡ ሥዕላቱ የሚገልጹት የሥዕሉ ባለቤት የሆነውን አምላክ ወይም ቅዱስ፤ ጻድቅ ወይም ሰማዕት ስለሆነ ተገቢውን ክብር እና ሥርዓተ አምልኮ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ ምእመናን ትክክለኛዎቹን የሥዕሉን ባለቤቶች አውቀው እንዲያከብሩ እና እንዲማጸኑባቸው ሠዓሊዎች የሚሥሉትን ቅዱስ ሥዕል በትክክል መሣልም አለባቸው፡፡

‹‹ማእከለ አሥዋክ ዘጸገየት ጽጌ ሃይማኖት፤ በእሾሆች መካከል የበቀለች የሃይማኖት ተክል- ቤተ ክርስቲያን››

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ማእከለ አሥዋክ ዘጸገየት ጽጌ ሃይማኖት፤ በእሾሆች መካከል የበቀለች የሃይማኖት ተክል›› በማለት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስቀድሞ በድጓው እንደተናገረው ቅድስት ቤተክርስቲያን ከቀደመው ዘመን ማለትም በክርስቶስ ደም ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ አኗኗሯ ሁሉ ውድቀቷንና ጥፋቷን በሚሹ በአሕዛብ በመናፍቃንና በዓላውያን ነገሥታት በእነዚህ እሾሆች መካከል ነው፡፡

‹‹የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ›› (ምሳ. ፩፥፯)

‹‹እግዚአብሔርን መፍራት ለጥበብ ዘውድዋ ነው›› እንደተባለ ከእግዚአብሔር የሆነው ጥበብ መጀመሪያው እርሱን መፍራት ነው፤ (ሲራክ ፩፥፲፰)፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት ስንል በቁጣው ይቀሥፈኛል፣ በኃያልነቱ ያጠፋኛል ከሚል የሥጋትና የጭንቀት መንፈስ ሳይሆን የዓለሙ ፈጣሪና መጋቢ እርሱ መሆኑን በማመን በፈቃዱ መገዛትና መኖር ማለታችን ነው፡፡

በዓታ ለማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም በ፶፻፬፻፹፭ ዓመተ ዓለም ከሐና እና ከኢያቄም በፈቃደ እግዚአብሔር ተወልዳ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ የኖረችው በወላጆቿ ቤት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸውን አስታውሰው ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሰጧት፤

‹‹የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል›› (ዮሐ.፲፮፥፲፫)

ይህች ዓለም ከእውነት የራቀች መኖሪያዋን በሐሰት መንደር ያደረገች መሆኗ ይታወቃል፡፡ ሰው ማንነቱን አጥቶ በበደል ምክንያት በሐሰት ኖሯል፡፡ ሰው በፈቃዱ ጥፋት ምክንያት ከሚፈጽማቸው በደሎች ትልቁ በደል ውሸት ነው፡፡ ውሸት ተሸንፎ ይወድቃል፤ ከሕይወት ይርቃል፡፡ የኀጣአን ሁሉ ራስ ሐሰት ናት፡፡ ክፋትን ከራሱ አንቅቶ የበደለ ዲያብሎስ አቡሃ ለሐሰት፤ የሐሰት አባት የተባለው ለዚህ ነው (ዮሐ.፰፥፵፬)፡፡

ሥርዓተ ንባብ

ውድ አንባብያን በባለፉት ትምህርታችን ስምና የስም ዓይነቶች በሚል ርእስ በተከታታይ ማቅረባችን ይታወሳል፤ በዛሬውና በሚቀጥሉት ተካታታይ ትምህርታችን ደግሞ ስለ ንባብ ምንነት፣ ዓይነትና ስልት እንመለከታለን፤ መልካም ንባብ!

የመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት ተመረቁ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም የመጻሕፍተ ሐዲሳት እና ሊቃውንት ጉባኤ ቤት 18 የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት ኅዳር 21 ቀን 2012 ዓ.ም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመረቁ፡፡