Entries by Mahibere Kidusan

ግእዝ ዘኢትዮጵያ

እፎ ኃደርክሙ…

ተናገረው ይውጣ እንጂ አንደበትህ አይዘጋ
የአባቶችህ መገለጫ ዜማቸውን አትዘንጋ

‹‹እግዚአብሔር ከእኛ በላይ ለእኛ ያውቃል›› (ሮሜ ፷፥፳፯)

ሰዎች በሕይወት ዘመናችን ውስጥ በሁለት ነገሮች ታጥረን እንጸልያለን፤ እንሠራለን፤ እንኖራለን፡፡ ሁለቱ ነገሮችም እኛ የምንፈልጋቸውና የሚያስፈልጉን ናቸው፡፡ እነርሱንም ይዘን ከእግዚአብሔር ፊት በመቆም የሚያስፈልገንን ነገር እንጠይቀዋለን፡፡ ነገር ግን የፈለግነውን ወይም የጠየቅነውን ሁሉ ሳይሆን የሚያስፈልገንን አምላካችን ለእኛ ያደርግልናል፤ ወይም ይሰጠናል፡፡

የነነዌ ጾም

ነነዌ የሜሶፖታምያ ከተሞች ከሆኑት መካከል አንዷ ናት፡፡ ከሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ ፫፻፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደ ነበረች በታረክ ይነገራል፡፡ በ፵፻ (ዐራት ሺህ) ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በናምሩድ በኩል ከተቆረቆረችም በኋላ በ፲፻፬፻ (አንድ ሺህ ዐራት መቶ) ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የአሦራውያን ዋና ከተማ ሆናለች፡፡ (ዘፍ.፲፥፲፩፣፪ኛነገ.፲፱፥፴፮)

በከተማዋም ታዋቂ የነበረ አስታሮት የተባለ የጣዖት ቤተ ነበረ፡፡ በዚህች ከተማ የሚኖሩት ሰዎች የሚሠሩት ክፋትና ኃጢአት እጅግ ከመብዛቱ የተነሣ ጽዋው ሞልቶ መጥፊያቸው ስለ ደረሰ ለፍጥረቱ ርኅራኄ ያለው እግዚአብሔር ግን ንስሓ ይገቡ ዘንድ ነቢዩ ዮናስን ልኮላቸዋል፡፡ ይህ ነቢይ ከአሕዛብ ወደ አሕዛብ ወደ ንስሓ ይጠራቸው ዘንድ ነበር የተላከ ነው፡፡

‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ››(ኢሳ.፷፮፥፲፫)

የእግዚአብሔር ነቢይ ኢሳይያስ በዚያን ዘመን ይኖሩ ለነበሩት እስራኤላውያን እንዲናገር በታዘዘው መሠረት ይህን ቃል ነገራቸው፤ ‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ፡፡›› (ኢሳ.፷፮፥፲፫) ከነበሩበት መከራና ከጭንቀታችው ሁሉ እንደሚያጽናናቸው እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አማካኝነት ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ይህ ቃል በዚያን ዘመን ላለው ሕዝብ ብቻ የሚያልፍ ሳይሆን ዛሬ ያለነውም ትውልድ በተለይም እኛ ልናስተውለው የሚገባ ቃል ነው፡፡

‹‹አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ የበሉትም ወንዶች አምስት ሺህ ነበሩ›› (ማር.፮፥፵፬)

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከሞተ በኋላ ወደ በረሃ ሄደ፡፡ ሕዝቡም ሰምቶ ተከተለው፡፡ በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሕዝቡን እንዲያሰናብት ጠየቁት፡፡ ይህም ለዚያ ሁሉ ሕዝብ የሚሆን ምግብ ስለሌለ የሚበሉትን እንዲገዙ ነበር፡፡ እርሱ ግን ለጊዜው የተገኘውን አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ ባርኮ ሁሉንም እስኪጠግቡ ድረስ መገባቸው፡፡ ተርፎም አሥራ ሁለት መሶብ ተነሣ፡፡ የተመገቡትም ሕዝብ ሴቶችና ሕፃናት ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ ወንዶች ነበሩ፡፡ ‹‹አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ የበሉትም ወንዶች አምስት ሺህ ነበሩ›› እንዲል፤ ሴቶቹ ያልተቆጠሩበት ምክንያት በዐደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው፤ ሕፃናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ስለሚበዛ ነው፡፡ (ማር.፮፥፵፬)

ዐበይት አናቅጽ እና ዐሥራው

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን ስለ አዕማድ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና አምስቱ አዕማድን እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ሀልዎተ እግዚአብሔር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው እየበረታችሁ ነውን? በርቱ!
ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለእግዚአብሔር መኖር (ሀልዎተ እግዚአብሔር) በተሰኘ ርእስ ይሆናል፤ እንደተለመደው በአጽንኦት (በትኩረት ሆናችሁ) እንድትማሩ አደራ እንላለን፡፡

ዐራቱ የእግዚአብሔር ሠራዊት

‹‹በእግዚአብሔር ዘንድ ዐራት ሠራዊት አየሁ፡፡ ሰባቱ ነጎድጓድ በተናገሩ ጊዜ ልጽፍ አሰብሁ፤ ከሰማይም ‹ሰባቱ ነጎድጓድ የተናገሩትን ነገር በማኅተም ዝጋው፤ አትጻፈውም› የሚል ድምጽ ሰማሁ››፤…

በዓለ ሢመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ በመሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ በጥር ፳፪ ቀን የተሾመ መልአክ ነው፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ እንደተገለጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሠማራል፡፡ ለነቢዩ ሄኖክም የሰማይን ምሥጢርና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ የገለጸለት፤ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ (ሄኖ.፳፰፥፲፫)

‹‹የቅድስት ማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል›› ቅዱስ ያሬድ

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኵሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው፤ የቅድስት ማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል›› በማለት የመሠከረው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍት ነው፡፡ እርሷ በምድር ላይ በአይሁድ ክፋት ብዙ መከራና ኃዘን ካሳለፈች በኋላ በዘመነ ሉቃስ፣ ጥር ሃያ አንድ ቀን፣ በዕለተ እሑድ፣ በስድሳ ዐራት ዓመቷ ወደ ዘለዓለም ደስታ ትገባ ዘንድ ዐርፋለችና፡፡ (ጾመ ድጓ)