Entries by Mahibere Kidusan

አብረን እንዘምር!

ጌታ ተወለደ በትንሿ ግርግም፤

በከብቶቹ በረት ከድንግል ማርያም፡፡

እርሷም ታቀፈችው የተወደደ ልጇን፤

ሰማይና ምድር የማይወስነውን፡፡

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ፤ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

ጾመ ገሀድ

የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ አዝዘዋል፤ ይህም ጾመ ገሀድ ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና።

ስምንቱ አርእስተ ግሥ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹ባለቤትና ተሳቢ›› በሚል ርእስ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስምንቱን የግሥ አርእስት እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

በእንተ ልደቱ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት

የዳሞት አውራጃ ገዚ ሞተለሚ በነበረበት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ በኢቲሳ መንደር ካህኑ ጸጋዘአብና እግዚኀረያ በትዳር ተወስነው ይኖሩ ነበር። ጸጋ ዘአብ በክህነቱ እግዚኀረያ በደግነቷና በምጽዋት ጸንተው በመኖራቸው በሕጉና በሥርዓቱ ለሚኖሩት ቀናዒ በመሆኑ እግዚአብሔር አምላክ ጎበኛቸው። ሃይማኖታቸውን የሚረከብ፣ እንዳባቱ ጸጋዘአብ የሚባርክ የአብራካቸውን ክፋይ ሊሰጣቸው ወደደ።

ብሥራተ ገብርኤል

ብሥራታዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጦ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ መወለድ ያበሠራት ዕለት ታኅሣሥ ፳፪ ‹‹ብሥራተ ገብርኤል›› ታላቅ በዓል ነው፡፡

‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ›› (ሉቃ.፩፥፲፱)

የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ ‹‹እግዚእ ወገብር፤ አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ›› ማለት ነው፤ ‹‹ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኢይተረጐም ምሥጢር ባሕቱ ይመስል ብሂለ እግዚእ ወገብር፤ ገብርኤል ሆይ ተመራምሮ ለማይደረስበት ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፤ ነገር ግን አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ይመስላል›› እንዲል፡፡ (መልክዐ ቅዱስ ገብርኤል)

‹‹ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ›› (ፊልጵ.፬፥፬)

ከመከራው በላይ የእግዚአብሔርን ቸርነት እያሰበ የሚያመሰግን ሰው፥ ዘወትር ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ የተነሣ ደስተኛ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ እስር ቤት ሁኖ በደቀ መዝሙሩ በአፍሮዲጡ አማካኝነት በወንጌል ለተከላቸው ተክሎች ምእመናን በላከላቸው መልእክት እንዲህ ይላቸዋል፦ ‹‹ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፥ ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ!›› (ፊልጵ.፬፥፬)

የቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› (መዝ.፳፪፥፲) በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን፤ አሜን!