Entries by Mahibere Kidusan

‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ ትጸድቃለህ፤ ከአነጋገርህ የተነሣ በቃልህ ይፈረድብሃልና›› (ማቴ. ፲፪፥፴፯)

በአንደበታችን የምንናገረው ነገር መልካም ሲሆን ጽድቅ ሆኖ እንደሚቆጠርልን ሁሉ መጥፎ ከሆነ ደግሞ ኃአጢት ይሆንና በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂ ያደርገናል፡፡ ኃጢአት በአብዛኛው ከንግግር የሚመነጭ ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው ‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ ትጸድቃለህ፤ ከአነጋገረህ የተነሣ በቃልህ ይፈረድብሃልና።›› ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከት ውስጥ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ ‹‹በወንድሙ ላይ በከንቱ የሚቈጣ ሁሉ እርሱ ይፈረድበታል፤ ወንድሙንም ጨርቅ ለባሽ የሚለው በአደባባይ ይፈረድበታል፡፡›› (ማቴ. ፲፪፥፴፯፣፭፥፳፪)

ቅዱስ ወንጌል

ወንጌል፡- ወንጌል የሚለው ቃል ‹‹ሄዋንጌሊዎን›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ እንደሆነና በግእዝ ቋንቋም ብሥራት፣ ምሥራች፣ አዲስ ዜና፣ መልካም ወሬ፣ ደስ የሚያሰኝ፣ ስብከት ማለት እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ይገልጻሉ፡፡ (በመጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ ገጽ ፫፻፺፬)

ጽድቅ

ጽድቅ ማለት እውነት፣ ርግጥ፣ ቅንነት እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ መጽሐፋቸው ውስጥ ገልጸዋል፡፡ በመጽሕፍ ቅዱስ ላይ እንደተጻፈው ደግሞ ሰው በእግዚአብሔር ታምኖ በፊቱም ክብርና ሞገስ የሚያስገኝለት በጎ ሥራ ጽድቅ ይባላል፡፡ ‹‹መጽሐፍ፥ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ፤ ጽድቅ ሆኖም ተቈጠረለት የሚለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ፤ ሰው በሥራ እንደሚጸድቅ በእምነት ብቻም እንዳይደለ ታያለህን? እንዲሁ ዘማይቱ ረአብ ደግሞ ጕበኞችን ተቀብላ፥ በሌላ መንገድ ባወጣቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን? ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው›› እንዲል፤ (ገጽ ፯፻፵፮፣ ያዕ. ፪-፳፬-፳፮)

ልደተ ክርስቶስ

‹‹እነሆ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፡፡…››

የተስፋው ቃል

በአንዲት ፍሬ ቅጠል ሕይወትን አጥቼ
ርስቴን ተነጠኩ የሞት ሞትን ሙቼ
በግዞት ተነዳሁ በድቅድቅ ጨለማ
ወደ ፍዳ መንደር ወደ ሞት ከተማ…

ልደቱ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት

ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሆኖ የሥላሴን መንበር ያጠነው ጻድቁ አባት አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱበት ዕለት የተቀደሰች ናት፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ለአባታቸው ካህኑ ጸጋ ዘአብና ለእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ ባበሠራቸው መሠረትም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ ኢቲሳ በሚባል ቦታ በታኅሣሥ ፳፬፤ ፲፪፻፲፪ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ በሦስተኛው ቀን እሑድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ አንዱ አብ ቅዱስ ነው፤ አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው፤ አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ!›› (ማቴ.፯፥፲፭)

ነቢይ ማለት ተነበየ፣ ተናገረ ከሚለው የግእዝ ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም ወደፊት ስለሚሆነውና ስለሚመጣው አስቀድሞ መናገር፣ መተንበይ ማለት ነው፡፡ ከዚህም በተመሳሳይ ‹ናቪ› ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተገኘ ስያሜ ነው፤ መምራት፣ ማብሠር፣ መምከር፣ መንገር የሚል ትርጓሜም አለው፡፡ ይህ ቃል ወደ ግሪክ ሲተረጎም ‹ፕሮፌቴስ› ወይንም ‹ፕሮ› እና ‹ፌሚ› ከሚሉት ጥምር-ቃላት የተገኘ በመሆኑ ‹ፕሮ› ቅድሚያ፣ ከአንድ ነገር በፊት ማለትን ሲያመለክት ‹ፌሚ› ደግሞ መናገር፣ ማብሠርና ማሳወቅ ማለት እንደሆነ መምህር ብዙነሽ ስለሺ ‹ትምህርተ ሃይማኖት› በተሰኘው መጽሐፋቸው ውስጥ ገልጸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ‹ፕሮፌቴስ› የወደፊቱን ነገር አስቀድሞ መናገር፣ ማብሠር ወይም ማሳወቅ የሚል ትርጓሜ እንዳለው እንረዳለን፡፡ ምዕራባውያን በመጽሐፍ ቅዱሳቸው ውስጥ ቃሉን ‹ፕሮፌት› በሚለው ሲጠቀሙ የሴሜቲክ ቋንቋ ዘር የሆነው ግእዝ ከዕብራይስጡ ቃል ‹ናቪ› የሚቀራረብ ትርጓሜ በመውሰድ ነቢይ የሚለውን ቃል ይጠቀማል፡፡ (ትምህርተ ነቢያት ገጽ ፲፩)

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል

በንጉሥ ናቡከደነፆር ዘመነ መንግሥት እስራኤላውያንን በባቢሎናውያን ቅኝ ግዛት ሥር በወደቁበት ጊዜ ከአይሁድ ወገን የሆኑ አዛርያ፣ አናንያ እና ሚሳኤል የተባሉ ሦስት ሕፃናትም ተማርከው በባርነት ተወሰዱ፡፡ ንጉሡም መልካቸው ያመረ፣ የንጉሣዊና የመሳፍንት ልጆች የሆኑትን መርጦ ሥነ ጥበብ፣ የመንግሥት አስተዳደርና የባቢሎናውያን ቋንቋዎችን እንዲሠለጥኑ ለማድረግ በቤተ መንግሥቱ አስቀመጦ ይቀልባቸው ጀመር፡፡…

‹‹አባታችሁ አብርሃም የእኔን ቀን ያይ ዘንድ ተመኘ፤ አይቶም ደስ አለው›› (ዮሐ. ፰፥፶፮)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሰበከበት በዘመነ ሥጋዌ እርሱ የሚያስተምረውን ትምህርት እና የሚያደርገውን ገቢረ ተአምራት ወመንክራት ሰምተውና አይተው አይሁድ ቅናት አደረባቸው፡፡ ጌታችንንም በክፋት በሚከታተሉበት ጊዜ የእርሱን ጌትነትና የባሕርይ አምላክነት በትምህርት እየገለጠ ብዙ ተአማራት ቢያሳያቸውም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ እንዲሁም በሥጋ ተገልጦ ሲመላለስ ስላዩት አምላክነቱን ተጠራጥረው እንዲህ አሉት፤ ‹‹በውኑ ከሞተው ከአባታችን አብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማን ታደርጋለህ?›› (ዮሐ. ፰፥፶፫-፶፱)…