ሙሻ ዘር
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የሁለተኛውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹ሙሻ ዘር›› እናስተምራችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1010 entries already.
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የሁለተኛውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹ሙሻ ዘር›› እናስተምራችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
የምድርን መከራ፣ ችግርና ሥቃይ አልፎ በእምነት ጽናትና በመልካም ምግባር ለሚኖር ሰው የቅድስና ሕይወት እጅግ ጣፋጭ ናት፡፡ በጠቧቧ መንገድ በእውነት በመጓዝ ፍቅር፣ ሰላምንና የመንፈስ እርካታን በማጣጣም ጥዑመ ነፍሰ ምግብን እየተመገበ የመንፈስን ፍሬ ለመብላት በሚያበቃው በክርስትና ሕይወትም ይኖራል፡፡ መስቀልን የጦር መሣሪያ ወንጌልን ጋሻ መከታ አድርጎ ጠላት ዲያብሎስን ድል የነሣ እንደ እነ አቡነ ተክለሃይማኖት ዓይነት ጻድቅ ደግሞ በቅድስና ማዕረግ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይጓዛል፡፡
በርግጥም በቅድስና ሕይወት ሁሉም ተመሳሳይ ችሎታና ትጋት ሊኖረው አይችልም፤ እግዚአብሔር በሰጠው መክሊት ግን አትርፎ በከበረ ሞት ወደ ፈጣሪው መሄድ ይቻለው ዘንድ የአምላካች ቅዱስ ፈቃድ ነው፡፡ ሰው በመንፈሳዊ ብርታት ፈታናውን ሁሉ ማለፍ ከቻለ ለተለያዩ ክብር እንደሚበቃ ቅዱሳት መጻሕፍት ምሥክሮች ናቸው፡፡ ቅዱሳን በገድልና በትሩፋት ብዛት የሚያገኟቸው ዐሥር ማዕረጋት አሉ፡፡ ‹ጽማዌ፣ ልባዌ፣ ጣዕመ ዝማሬ፣ አንብዕ (አንብዐ ንስሓ)፣ ኩነኔ፣ ፍቅር፣ ሑሰት፣ ንጻሬ መላእክት፣ ተሰጥሞ እና ከዊነ እሳት› የሚል ስያሜም አላቸው፡፡ የንጽሐ ሥጋ፣ የንጽሐ ነፍስና የንጽሐ ልቡና ማዕረጋት በመባል ደግሞ በሦስት ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ወርኃ ክረምቱ እንዴት ነው? መቼም ዝናቡና ቅዝቃዜው እንደፈለግን እንዳንጫወት አድርጎናልና ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስም አያመችም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ቤት ውስጥ እንደምንቆይ ይታወቃል፡፡ ታዲያ ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም መጻሕፍትን ማንበብ፣ ለቀጣዩ ዓመት የትምህርት ጊዜ የሚረዱንን ጥናቶች በማድረግ ልንዘጋጅ ያስፈልጋል፤ ጊዜያችንን በአግባቡ በቁም ነገር ላይ ማዋል አለብን! ደግሞም በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታም እየደረሰች ነው!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የቅድስት መስቀል ክብራን ታሪክ ነው፡፡
በመከራ ጊዜ ረዳት የሆነው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ዑራኤል በዘመናት ለነገሡ የሀገራችን ነገሥታት ያደረገው ውለታ እጅግ ብዙ ነው፡፡ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለ ንዋየ ማርያም በነገሠበት ዘመነ መንግሥት ቅዱስ ዑራኤል በጸሎቱ በመራዳትና እስከ ግዛቱ ፍጻሜ ባለመለየት ሀገሩን እንዲመራ አድርጓል፡፡…
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለወርኃ ክረምቱ አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ቸርነት፣ የተዘራው እህል በቅሎ ምድር ድርቀቷ ተወግዶ በአረንጓዴ ለምለም የምታጌጥበት ወቅት ነው፡፡ ለምድር ዝናምን ሰጥቶ፣ በዝናብ አብቅሎ፣ በነፋስ አሳድጎና በፀሐይ አብስሎ ፍጥረታቱን የሚመግብ የእግዚአብሔር ቸርነቱን እያወሳን ለምስጋና የምንተጋበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ የዕረፍት ጊዜያችን ለቀጣይ የትምህርት ዘመን እየተዘጋጀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር በመሄድ በርትተን፣ ውለታውን እያሰብን ለጸሎት ለቅዳሴ መትጋት አለብን!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ታሪክ ነው፡፡
ሜሶፖታሚያ በምትገኝ ንጽቢን ከተማ ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች መካከል በ፫፻፮ ዓ.ም ገደማ የተወለደው ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም አባቱ ክርስትናን የሚጠላ ሰው እንደነበር ይነገራል፡፡ እንዲያውም ካህነ ጣዖት ስለመሆኑ መጽሐፈ ስንክሳር ይጠቅሳል፡፡ (ስንክሳር ሐምሌ ፲፭)
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የመጀመሪያውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ክፍል ሁለትን እናቀርብላችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ለሰው ሰውነቱ
ከአፈር መስማማቱ
የሸክላ ብርታቱ
እሳት ነው ጉልበቱ
ውኃ ደም ግባቱ
ነበር መድኃኒቱ!
በሀገረ ሮም ከአባቱ ንጉሥ አብያ ከእናቱ አንሰራ ተወለደ፡፡ ደጋግና ቅዱሳን ወላጆቹም እግዚአብሔርን በመፍራት እየኖሩበት በነበረበት ወቅት ይህን የተመረጠ አባት ሰጣቸው፤ አባ ኪሮስ የተወለደው በታኅሣሥ ፰ ቀን ነበር፡፡ ጻድቁ አባት በቅድስና ሕይወትና ትጋት ማዕረግ አባ ኪሮስ ከመባሉ በፊት ‹ዲላሶር› ተብሎ ይጠራ እንደነበር ታሪኩ ይገልጻል፡፡
‹‹ኮከበ ክብር ጽዱል ፀሐዬ አግዓዚ ብሩህ አቡነ ጊዮርጊስ ጥዑመ ስመ ወሠናየ ግዕዝ መጋቤ ሃይማኖት ወመሠረተ ቤተ ክርስቲያን፤ አባታችን ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የሚያበራ የክብር ኮከብ፣ የኢትዮጵያ ብሩህ ፀሐይ፣ ስሙ የሚጣፍጥ፣ ምግባሩ የቀና ነው።›› (ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)