To media kifil

በተለያዩ ጊዜያት ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ለተመረቃችሁ እህቶችና ወንድሞች በሙሉ

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ኮርስና ልዩ ልዩ መርሐ ግብራትን የሚያከናውንበት የመማሪያ አዳራሽ እያሰራ ይገኛል። ነገር ግን ይህን አዳራሽ በራሱ ሰርቶ ለማጠናቀቅ የሚያስችል አቅም የለውም።

ስለሆነም ይህን አዳራሽ ለማጠናቀቅ የሁላችንም ኦርቶዶክሳዊያን ሐላፊነት ነውና በተለያዩ ጊዜያት የተመረቃችሁ የቀድሞው የግቢ ጉባኤው አባላት እንዲሁም ሌሎች በአዳራሽ ሥራው መሳተፍ የምትፈልጉ ኦርቶዶክሳዊያን በሙሉ በሚከተለው የግቢ ጉባኤው የሒሳብ ቁጥር የምትችሉትን ገንዘብ በማስገባት ድጋፋችሁንና እርዳታችሁን ታደርጉ ዘንድ ግቢ ጉባኤው ጥሪውን ያስተላልፋል። የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ 1000139923058 (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አክሱም ቅርንጫፍ) ለተጨማሪ መረጃ፡ 0918052641 (በላቸው መስፍን – የግቢ ጉባኤው አዳራሽ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ)

To media kifil

በጅማ ማእከል የጽ/ቤት ግንባታ ለማካሔድ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ

የማኅበረ ቅዱሳን በጅማ ማዕከል ለሚያስገነባው ባለ አራት ፎቅ ሕንፃ የመሠረት ድንጋይ ታህሳስ 24 ቀን 2008 ዓ.ም ተቀመጠ፡፡የጅማ፣ ኢሊባቦር እና ጋምቤላ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የመሠረት ድንጋዩን ካስቀመጡ በኋላ በሰጡት ትምህርት “€œበመከከላችን መደማመጡ፣ መተባበሩ፣ ሲኖር እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ይሆናልና ፤የሀገረ ስብከቱን ሁለገብ ሕንፃ ከእለት ጉርሳችሁ ቀንሳችሁ እንደገነባችሁ ይህንንም ሕንፃ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ አድባራት እና መላው ምእመናን ጥረት በማድረግ የቤተ-ክርስቲያኒቷን አገልግሎት እንድታፋጥኑ” በማለት መልእክትና መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

የጅማ ማዕከል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ማሞ መኮንን ባደረጉት ንግግር ቤዝመንቱን ጨምሮ ስድስት ወለል ያለው ሕንፃ እንደሚገነባ ገልጸው፤ “€œሕንፃው ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚከናወንባቸው የአገልግሎት ክፍሎች ፣የስብሰባና የስልጠና ይኖሩታል” ብለዋል፡፡
እንደ አቶ ማሞ ገለጻ ሕንፃው ከ12 ሺህ በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች ከሚማሩበት የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፊት ለፊት መገንባቱ ማኅበሩ በከፍተኛ ተቋም ውስጥ የሚማሩ ኦርቶደክሳዊያን ወጣቶች ከዘመናዊ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የቤተክርስቲያናቸውን ትምህርተ ሃይማኖት፣ታሪክ፣ሥርዓትና ትውፊት ተምረው የቤተ-ክርስቲያኒቷ ተረካቢ እንዲሆኑ ለማስቻል ማኅበሩ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንደሚያግዘው አስረድተዋል፡፡
ሕንፃውን ለማጠናቀቅ ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ የተናገሩት አቶ ማሞ ለግንባታው መጠናቀቅ መላው የቤተ-ክርስቲያኒቱ አባላት ሁሉ “€œየድርሻችንን እንወጣ”€ በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የሕንፃ ግንባታውን ሥራ በገንዘብ ለማገዝ የምትፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለE.0.T.C MAHIBERE KIDUSAN TS/BET BUILIDING. ሒሳብ አካውንት ቁጥር 1000143436989 ብሎ መላክ እንደሚቻል አስታውቀዋል፡፡

የጂንካ ማእከል የመጀመሪያውን የሐዊረ ሕይወት ጉዞ ወደ ስብከት ኬላ አደረገ

ጂንካ ማእከል

በጂንካ ማእከል በማኅበረ ቅዱሳን ጂንካ ማእከል የመጀመሪያውን የሐዊረ ሕይወት ጉዞውን በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት፣ በበና ጸማይ ወረዳ፣ ጫሊ ቅድስት ሥላሴ ስብከት ኬላ ታኅሣሥ 17 ቀን 2008 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ፡፡በጉዞው ላይ የደቡብ ኦሞ ሀ/ስብከት የመምሪያ ሓላፊዎች፣ የጂንካ ከተማ ገዳም፣ አስተዳደርና የአቢያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የመጡ ተጋባዥ እንግዶች፣ ሰባኬ ወንጌልና ዘማሪያን በአጠቃላይ 1000 ምእመናን ተሳትፈዋል፡፡

ጉዞው ቤተ ክርስቲያን ባልታነፀበት የስብከት ኬላ እና ሁልጊዜም “አጥምቁን እና ቤተ ክርስቲያን ሥሩልን” ወደሚሉት አርብቶ አደር ወገኖቻችን ጋር መደረጉ ከሌሎች ማእከላት ልዩ ያደርገዋል ተብሏል፡፡

ጉዞው ታኅሣሥ 17 ቀን 2008 ዓ.ም ጠዋት 12፡30 ላይ በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በተገኙበት በአንቀጸ ብፁዓን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም አበምኔት ቆሞስ መ/ር አባ ኤፍሬም ፈቃዴ በጸሎት የተከፈተ ሲሆን በአስተባባሪዎች አማካኝነት ሁሉም ምእመናን ወደተዘጋጀላቸው መኪና ከገቡ በኋላ ጉዞው ተጀመረ፡፡ በጉዞው ላይ በአስተባባሪዎች አማካኝነት በክርስትና ሕይወት ዙሪያ ውይይት እየተደረገ መዝሙር እየተዘመረ እና ከተጓዦች ጥያቄ እየተሰበሰበ የጉዞው ቦታ ላይ ተደርሷል፡፡ በቦታውም ያሉ አርብቶ አደር ምእመናን “ሁሌም አጥምቁን ቤተ ክርስቲያን ሥሩልን” የሚሉን በርካታ ምእመናን በቋንቋቸው በዝማሬ ተጓዦችን ተቀብለዋል፡፡

የጧዋቱ መርሐ ግብር በካህናት ጸሎተ ወንጌል የተከፈተ ሲሆን ትምህርትም በመምህራን ወንጌል ተሰጥቷል ፡፡ከሰዓት በኋላ ከጂንካ አጥቢያ በተገኙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በቆሞስ መ/ር አባ ኤፍሬም ፈቃዴ የአንቀጸ ብፁዓን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም አበምኔት ከሕዝብ የተነሳውን ጥያቄዎችን፣ ሊቀ ብርሃናት ኤልያስ ዘውዴ በቤተ ክርስቲያን የምእመናን ድርሻ ምንድነው? መሪጌታ ዘመልአክ የበዓታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የልጆች አስተዳደግ ምን መምሰል አለበት? በሚል ርእስ ለምእመናን በቂ መልስ የሰጡ ሲሆን፣ በጉባኤው ላይ የተገኙት ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም ደግሞ ስለ ቅዱስ ጋብቻ እና የንስሐ ሕይወት ዙሪያ ከአባታዊ ምክር ና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ስለ ጫሊ ስብከት ኬላ አመሠራረትና አሁን ስላለው የአገልግሎት እንቅስቃሴ እና ስለ ቀጣዩ ዕቅዳቸው በጥያቄና መልስ የተብራራ ሲሆን፤ ስብከት ኬላውም ጳጉሜ 3 በ1999 ዓ/ም በአቡነ ዕንባቆም እንደተባረከ ተገልጧል፡፡

በመጨረሻም የጂንካ ማዕከል ሰብሳቢ አቶ ዘላለም ጌታቸው አጠቃላይ መልእክት፣ ማሳሰቢያና ለስብከት ኬላው ገቢ በማሰባሰብ እና በጉዞው አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና በማቅረብ በጂንካ ደብረ ቀራኒዮ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ አማካኝነት በጸሎት ተዘግቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ ከተጓዦች መካከል እንግዶች በሰጡት አስተያየት ጉዞው ቢደገምና ሌሎችም እንዲህ ዓይነቱን ዝግጅት ቢካፈሉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ማኅበሩም የአገልግሎት ማኅበር መሆኑን ተገንዝበናል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

alt

የአርባ ምንጭ ማዕከል ሐዊረ ሕይወት አካሄደ

alt

በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል የተዘጋጀው ልዩ መንፈሳዊ የጉዞ መርሐ-ግብር “ሐዊረ ሕይወት” የሕይወት ጉዞ ታህሳስ 24/2008 ዓ/ም ወደ ምዕራብ አባያ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተደረገ፡፡


“በዚህ ዓመት ለ2ኛ ጊዜ የተደረገ የሕይወት ጉዞ ሲሆን በአርባምንጭ ከተማ እና አካባቢዋ የሚኖሩ ከ900 በላይ ማኅበረ ምእመናን ተሳትፈውበታል፡፡ ይህ ታላቅ መንፈሳዊ የሕይወት ጉዞ በወርኃ-ታኅሣሥ ጾመ ነቢያት ወቅት መደረጉ ምእመናን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲበረቱና በገጠር የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትንና ገዳማትን ሁለንተናዊ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት እንዲደግፉ ለማድረግ ነው” በማለት የጉዞው አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አሥራት ገዛኸኝ ገልጸዋል፡፡ alt
መርሐ-ግብሩ በሁለት ምዕራፎች የተከፈለ ሲሆን በጋሞ ጎፋ ሀገረ ስብከት ተወካይ በጸሎት ተከፍቷል፡፡ በጠዋቱ ምዕራፍ የወንጌል ትምህርትን አስከትሎ ምዕመናን በታላቅ ናፍቆት የሚጠብቁት ምክረ-አበው ክፍል አንድ በጎንደር መንበረ መንግሥት መድሃኔ ዓለም ጉባኤ ቤት መምህር የሆኑት መምህር በጽሐ ዓለሙ እና ከደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በተጋበዙ መምህር ኃይለማርያም ዘውዱ አማካኝነት ምእመኑ ማብራሪያ በሚሻባቸው ርእሶች ዙሪያ ጥልቅ የነገረ ሃይማኖት ትንተና አድርገዋል፡፡ መምህራኑ በዋናነት ለቅዱሳን፣ ጻድቃን እና ሰማዕታት የምንሰጠው ክብርና አማላጅነታቸውን፤ ስለ ጾም፣ ጸሎትና ስግደት ከቤተክርስቲያናችን ሥርዓት አንጻር ቅዱሳት መጻህፍትን አጣቅሰው አመስጥረው አስተምረዋል፡፡ በምዕራፍ ሁለት የከሰዓቱ መርሐ-ግብር ደግሞ መምህራኑ በወቅታዊ የቤተክርስቲያን ፈተናዎች፣ የተሐድሶ አራማጆች ግራ በሚያጋቧቸው የኑፋቄ አስተምህሮዎች ዙሪያ፣ የጸበል ሥርዓትን በተመለከተ እና በጋብቻ ላይ ለምእመኑ የሕይወት ስንቅ ይሆን ዘንድ በስፋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እውነተኛ ሥርዓት መክረዋል፤ አስተምረዋል፡፡alt በሌላ መልኩ የአርባ ምንጭ ማዕከል የበገና ተማሪዎች ነፍስን በሚያለመልም ዝማሬ እግዚአብሔርን ያመሰገኑ ሲሆን፤ በ2007 ዓ/ም በጋሞ ጎፋ ሀ/ስብከት፣ በኮንሶ ወረዳ ቤተ ክህነትና በማኅበረ ቅዱሳን ትብብር ተጠምቀው የመንፈስ ቅዱስን ልጅነት ያገኙት የጉኛራና ኮልሜ አዳዲስ ተጠማቂያን በተጋባዥ እንግዳነት መርሐ-ግብሩን ተሳትፈዋል፡፡ እንግዶቹም ከተቋቋመ አንድ ዓመት እንኳን ያልሞላው የሰንበት ት/ቤት በኮንስኛና በአማርኛ መዝሙር በማቅረብ እግዚአብሔርን አመስግነዋል፡፡ በተያያዢነት ተጓዡ ምዕመን የደብሩን አጸደ ሕጻናት ትምህርት ቤት የመናፍቃን ጫና እና የዐቅም ውስንነት ለመቅረፍ ከ7000 ብር በላይ ሰብስቦ በዕለቱ ድጋፍ አድርጓል፡፡ በመጨረሻም ምእመኑ ይህ መሰሉ የሕይወት ጉዞ በተደጋጋሚ ወደተለያዩ ቅዱሳት መካናት መዘጋጀት እንዳለበትና ምአመኑም በሚችለው ሁሉ ከማኅበሩ ጋር አብሮ ለመሥራት ተነሳሽነቱን አሳይቷል፡፡ በመሆኑም 3ኛው ሐዊረ ሕይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በዚሁ ዓመት ወርኃ ሚያዝያ ውስጥ ወደ ዶርዜ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እንደሚደረግ የጉዞ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ታህሳስ 25/2008 ዓ/ም

6

የሩቅ ምሥራቅ ግንኙነት ጣቢያ ሐዊረ ሕይወት አካሄደ !

6

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በማኅበረ ቅዱሳን የሩቅ ምስራቅ ግንኙነት ጣቢያ ከዐስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ ወደ አስተማረበት ደቡባዊ ሕንድ ኬረላ ግዛት ከታህሣሥ 17 እስከ 25 ቀን 2008 ዓ.ም የሐዊረ ሕይወት ጉዞ አካሂዷል፡፡

በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ በሕንድ የተለያዩ ግዛቶች ከኒው ደሊህ፣ሮርኪ፣ ፐንጃቢ፣ ፑኔ ፣ ሙምባይ ፣አንድራ እና ባንግሎር የሚማሩ እና የሚኖሩ ምእመናን በባቡር ከ 10 እስከ 48 ሰዓት ተጉዘው ተሳታፊ ሆነዋል ፡፡በጉዞው ላይ ኤርትራውያንም ተሳትፈዋል።

የሐዊረ ሕይወት ተሳታፊዎችም ቅዱስ ቶማስ በመጀመርያ መቶ ክፍለ ዘመን የሥራቸዉን አብያተክርስቲያናት የአጽሙ ክፍል ያለበትን ቤተክርስቲያን ፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልብሷ ክፋይ ያለበትን ቤተክርስቲያን ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ የአጽሙ ክፋይ ያለበት ቤተክርስቲያንን ፣ ቅዱሳን አባቶች እና እናቶች የጸለዩባቸዉን ገዳማትና አድባራት፣ የህፃናት ማሳደጊያ ማዕከላትን፣ በተለያዩ ሱሶች የተጠመዱ ሰዎች ማገገሚያ ማዕከልን፣ 200 ዓመት ያስቆጠረዉን ሴሚናሪ(Seminary) መንፈሳዊ ኮሌጅ እና የህንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክን ƒƒƒ‚በመጎብኘት የበረከቱ ተሳታፊ መሆናቸውን የሩቅ ምሥራቅ ግንኙነት ጣቢያ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}../ruqemeseraqe{/gallery}

በሐዊረ ሕይወት ጉዞም የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የማር ጎርጎርዮስ የተማሪዎች ማኅበር ፕረዘዳንት እና የቦምቤ ሀገረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ አባ ቄርሎስ (His Grace Geevarghese Mar Coorilos Metropolitan of Bombay Diocese and Presedant of Mar Gregorios Orthodox Christian Student Movement) ከመጀመሪያ አንስቶ ጉዞው እንዲሳካ በመጸለይና በሀሳብ በመርዳት በመጨረሻም ሀገረ ስብከታቸው ከሚገኝበት ማራሽትራ ግዛት ከሙምባይ ከተማ ተነስተው 1600 ኪ.ሜ በመጓዝ መንበረ ፕትርክናው ከሚገኝበት ኬረላ ግዛት ኮታይም ከተማ ከታህሣሥ 19 እስከ 22 2008 ዓ.ም ድረስ በቦታው በመገኘት ለጉዞው መሳካት ሁኔታዎችን በማመቻቸት እና ከተጓዦች ጋር በየዕለቱ በመገኘት በአባታዊ ምክር እንዲሁም ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ በመስጠት እና የህንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተሐድሶ መናፍቃን ስለደረሰባት ከፍተኛ ፈተና ገላጻ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡

በጉባኤው ላይ መዝሙር እና ወረብ በየአብያተክርስቲያናቱ ገዳማት እና መንፈሳው ኮሌጆችተማሪዎች የቀረበ ሲሆን የተጓዦችን ሕይወት የሚያንጹ ትምህርቶች በተለይም ስለመንፈሳዊነት እና ወጣትነት ውይይት ስለቤተክርስቲያን ወቅታዊ ፈተናዎችና መፍትሔዎቻቸው እንዲሁም ስለ ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ገለጻና ውይይት ተደርጓል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በሁለቱ አብያተክርስቲያናት የወጣት ተማሪዎች ኅብረትን ለማጠናከር ሲባል በሊቀ ጳጳስ አባ ቄርሎስ በተደረገ ግብዣ ከታህሣሥ 15 እስከ 16 ቀን 2008 ዓ.ም ከማኅበረ ቅዱሳን የሩቅ ምሥራቅ ግንኙነት ጣቢያ የተወከሉ አባላት በ107 ኛው የማር ጎርጎርዮስ የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ወጣቶች ሀገር አቀፍ ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በመጨረሻም የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ባስልዮስ ማርቶማ ጳዉሎስ ዳግማዊ (Baselios Marthoma Paulose II Catholicos of the East and Malankara Metropolitan Malankara Orthodox Syrian Church) ለተጓዦች ባደረጉት ግብዣ በመንበረ ፓትርያርክ በመገኘት ለቅዱስነታቸው የኢትዮጵያዊዉን የዜማ ሊቅ የቅዱስ ያሬድ ሥዕል እና ታሪኩን የያዘ ጥራዝ የተበረከተላቸው ሲሆን ተሳታፊዎች በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ እንዲቀመጡ ተደርጎ ስለሕንድ ቤተክርስቲያን ሰፊ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ቅዱስነታቸውም ስለ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እና ስለ ሕንድ ቤተክርስቲያን ገለጻ በማድረግ ለተጓዦች ጸሎትና ቡራኬ በመስጠት የዕለቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል፡፡ በእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ተሳታፊዎችወደ መጡበት ቦታ ከታህሳስ 23 እስከ ታህሳስ 25 2008 ዓ.ምባሉት ጊዚያት በመኪና፣በባቡር እና በአውሮፕላን በመጓዝ በሠላም ተመልሰዋል፡፡

የተሐድሶ መናፍቃን ድፍረት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ለመቀልበስ እስከ መሞከር

ባለፉት ተከታታይ ዕትሞች ስለ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ስልትና ግብ ማቅረባ ችን ይታወቃል፡፡ በዚህ ዕትም ደግሞ ተሐድሶ መናፍቃን ጥፋታቸውን አምነ ውና ተጸጽተው ከመመለስ ይልቅ የቅ ዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ካለመቀበል አልፎ ውሳኔዎችን ለማስቀልበስ እስከ መሞከር ድረስ የሚያደርጉትን ከንቱ ሩጫ እናቀር ባለን፡፡ መልካም ንባብ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ ብዙ ፈተና ዎችን እንዳሳለፈችና ፈተናዎቹ መልካ ቸውን እየለዋወጡ ራሳቸውን የሚደ ግሙ እንጂ አዲሶች እንዳልሆኑ ባለፉት ጽሑፎች ተመልክተናል፡፡ በዚህ ክፍለ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ታላቅ ፈተና የሆኑት ተሐድሶ መናፍቃን አስተም ህሯቸውና ዓላማቸው ፕሮቴስታንታዊ ሆኖ ሳለ ኦርቶዶክሳዊ ነን በማለት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብተው ብዙ የዋሀ ንን ከበረታቸው ለማስወጣት እየሠሩ ነው፡፡ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ በዋናነት የቤተ ክርስቲያን ምንጮችን በመለየት፣ ምንጮቹ ውስጥ ሠርጎ በመ ግባት፣ አስተምህሮ በመቀየርና የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር በመቆጣጠር ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ለመረከብ፣ መረከብ ካልቻሉ ደግሞ እንደ ሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለመክፈል የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው፡፡ በተሐድሶ መናፍቃን የቤተ ክርስቲያን የእምነትና የመንፈሳዊነት ምንጮች ተብለው ለጥፋት ተልእኳቸው ዒላማ የተለዩት ደግሞ የአብነት ትምህርት ቤቶች (የሊቃው ንተ ቤተ ክርስቲያን መፍለቂያ ስለሆኑ)፣ ገዳማት (የሊቀ ጳጳሳትና ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት መፍለቂያዎች ስለሆኑ)፣ መንፈሳዊ ኮሌጆች (የስብከተ ወንጌል ሓላፊ ዎችና የመምህራን መፍለቂያዎች ስለ ሆኑ)፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች (ወጣቶ ችንና ምእመናንን ለማግኘት የተመቹ መድረኮች ናቸው ብለው ስላሰቡ) እና የቤተ ክርስቲያን መዋቅር (ድጋፍና ሽፋን ለማግኘት ይጠቅመናል ብለው ስላሰቡ) ናቸው፡፡
ቤተ ክርስቲያንም የተሐድሶ መና ፍቃንን እንቅስቃሴ ለመግታት በተለያዩ ጊዜያት ተኩላዎችን ከበጎች የመለየት ሥራ ሠርታለች፡፡ በተለይም ምእመናንን የመጠበቅ ሓላፊነት ያለበት ቅዱስ ሲኖ ዶስ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጋቸው ጉባ ኤያት ላይ የተሐድሶ መናፍቃንን መሰሪ አካሔድ ተረድተን እንድንጠነቀቅ ያላሳሰ በበት ጊዜ የለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ቅዱ ሳን ሐዋርያት በአመክንዮአቸው “እኛስ የሃይማኖት ለዋጮችን ግብር እንጸለየ ፋለን” ብለው ባስቀመጡት መመሪያ መሠረት የተሐድሶ መናፍቃንን ኑፋቄ ነቅሶ በማውጣትና የሃይማኖት ለዋጭ ነት ግብራቸውን በማውገዝ መመለስ የፈለጉትን ተመክረው፣ ቀኖና ተሰ ጥቷቸው፣ መምህራን ተመድበውላ ቸው እንዲማሩና ወደ ቤተ ክርስቲ ያን አንድነት እንዲጨመሩ፤ ቀኖናውን ለመቀበልና ለመማር ፈቃደኛ አንሆንም፣ ርትዕት ወደሆነችው ሃይማኖትም አንመለስም ያሉትን ደግሞ ከቤተ ክር ስቲያን አንድነት እንዲለዩ አድርጓል፡፡ በተለይም በ፲፱፻፺ ዓ.ም እና በ፳፻ወ፬ ዓ.ም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮን የሚጠብቁ ሳይሆኑ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ነን በማለት ሲያደናግሩ የነበሩ ተሐድሶ መናፍቃን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘዋል፡፡ የተሐድሶ መናፍቃን አቀንቃኞችን በማውገዝ ብቻ እንቅስቃሴውን መግታት እንደማይቻል የተረዳው ቅዱስ ሲኖዶስ የተሐድሶ መናፍ ቃን ምንጫቸው ምንድን ነው የሚለ ውን ለማወቅ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ባለሙያዎችን ያካተተ ሁሉን አቀፍ የሆነ ጥናት አጥንቶ የሚያቀርብ ኮሚቴ ሠይሞ ቅዱስ ሲኖዶስ በበላይ ነት እየመራና መመሪያ እየሰጠ ጉዳዩ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ክትትል እያደረገ ነው፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በተለይም ከ፳፻ወ፬ ዓ.ም ጀምሮ የተሐድሶ መናፍቃንን ጉዳይ ዋና አጀንዳ አድርጎ በየጉባኤው ሲወያ ይበት እንደነበር የቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤያት ያሳያሉ፡፡ ጉባኤው በመደበኛ ጉባኤያቱ ላይ ተሐድሶ መናፍቃን በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሠርገው በመግባት ጥፋት እያደረሱ እንደሆነና እንቅስቃሴው በሁሉም አህጉረ ስብከት የሚታይ መሆኑን አስቀምጧል፡፡ በዚህ መነሻነት የተሐድሶ መናፍቃን መገኛ ምንጫቸው ከየት እንደሆነ ለመለየት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡ በውይይቱም ተሐድሶ መናፍቃን ሠርገው በመግባት ብዙ ጥፋት እያደረሱባቸውና ኦርቶዶክሳ ውያን ልጆችን መናፍቅ ለማድረግ ትኩ ረት አድርገው ከሚሠሩባቸው የቤተ ክርስቲያን ተቋማት መካከል መንፈሳዊ ኮሌጆቻችንም የሚገኙበት በመሆናቸው በእነዚህ የቤተ ክርስቲያን የትምህ ርት ተቋማት ላይ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ በማለት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ስለዚህም የመንፈሳዊ ኮሌጆች የተማሪ አቀባበል፣ የትምህርት አሰጣጥ፣ የመም ህራን ማንነትና ምንነት እንዲሁም የማስተማሪያ መጻሕፍት ሊፈተሹና ሊመረመሩ እንደሚገባቸው በመግለጽ ጉዳዩን በጥልቀት አጥንቶ የሚያቀርብ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሠራ ይገኛል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ጉዳዮችን አስቀድሞ በማየትና ብፁዓን አባቶች በየአህጉረ ስብከታቸው እየተካሔዱ ያሉ እንቅስቃሴዎችን መነሻ በማድረግ በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ውሳኔዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ከምእመናን የሚ መጡ ጥቆማዎች በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ለሚሰጣቸው ውሳኔዎች ትልቅ ግብዓት ሆነው አገልግለዋል፡፡ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም በየአህጉረ ስብከታቸው እንዲሁ በተሐድሶ መናፍቃን ላይ እር ምጃዎችን ለመውሰድ በራሳቸው ክት ትል ከሚደርሱባቸው እውነታዎች በተ ጨማሪ ከሕዝበ ክርስቲያኑ የሚመጡ ጥቆማዎችን በግብዓትነት ይጠቀማሉ፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን ከጊዜ ወደ ጊዜ ሥውር ዓላማቸውን ዕውን ለማድረግ በቤተ ክርስቲያን ላይ እያካሔዱት ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ በሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ እየታወቀ መጥቷል ብለን እናምናለን፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በተሐ ድሶ መናፍቃን ላይ በየጊዜው የሰጣቸው ውሳኔዎች ምእመናን ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ከማድረጉም በላይ እንቅስቃሴ ውን ለመግታት የራሳቸውን ሓላፊነት እንዲወጡም አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ያለው ግንዛቤና በእንቅስቃሴው አደገኛነት ላይ ያለው መረዳት ማደጉ በጉዳዩ ላይ ያገባኛል የሚል ስሜት እንዲ ያሳድር አድርጓል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስና የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ውሳኔዎች ያበረ ታቷቸው ምእመናን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ እየተ ካሔደ ያለውን የውስጥም ሆነ የውጪ ሴራ የማክሸፍ እንቅስቃሴን የራሳቸው ጉዳይ አድርገው እንዲሠሩ እገዛ አድር ጎላቸዋል፡፡ የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስ ቃሴ ሥውር ዓላማና ቤተ ክርስቲያ ንን የማፍረስ ተልእኮ ጠንቅቀው የተረዱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ ማኅበራት፣ ምእመናን እና ወጣቶች መረጃዎችን ስለ እንቅስቃሴው በቂ ግንዛቤ ለሌላ ቸው ምእመናን ለማዳረስ ያደረጉት ጥረት ከፍተኛ ነው፡፡ እነዚህ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መከታተላቸው እና መረጃው የሌላቸውን ምእመናን ለማንቃት ሰፊ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው የተሐድሶ መናፍቃንን መሰሪ ተግባር በማጋለጥ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን በየቦታው የሚያ ደርጉትን ሥውር እንቅስቃሴ በማጋ ለጥ፣ መረጃዎችን በማሰባሰብ ለሚመለ ከታቸው አካላት በማቅረብ፣ ስለ እንቅስ ቃሴው አደገኛነት ግንዛቤ መፍጠሪያ መርሐ ግብራትን በማዘጋጀት እውነቱ ከሐሰቱ እንዲለይ በማድረግ ትልቅ ሥራ ሠርተዋል፡፡ ግንዛቤ መፍጠሪያ መርሐ ግብራቱ አብዛኛው ምእመናን የቤተ ክርስቲያንን መምህራን የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ነጣቂ ተኩላዎች ለይ ተው እንዲያውቁ አድርገዋል፡፡ በዚህ መነሻነት ብዙ ምእመናን የተሐድሶ መና ፍቃንን ሥውር ሴራ በመገንዘብ በግ ልም በማኅበርም በመደራጀት እንቅስቃ ሴውን ለመግታት እየተጉ ይገኛሉ፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በተለያዩ ጊዜያት የሰጣቸውን ውሳኔዎች እና አቅጣጫ ዎች መሠረት በማድረግ ብዙ አህጉረ ስብከት የተሐድሶ መናፍቃንን ዓላማ አንግበው በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሠርገው በመግባት ምእመንን የሚያደናግሩ ክፉዎች ሠራተኞችን ከአገልግሎታቸው አግደዋል፡፡ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በየአህጉረ ስብከታቸው ለተሐድሶ ዓላማ አስፈጻሚ የሆኑት ልብ ገዝተው መመለስ ለሚፈልጉት ቀኖና በመስጠት እንዲታረሙ፣ ለመመ ለስ ፈቃደኛ ላልሆኑት ደግሞ ተወግ ዘው እንዲለዩ በማድረግ የኖላዊነት ሓላፊነታቸውን በመወጣት አርአያና ተጠቃሽ የሚሆን ተግባር አከናውነ ዋል፡፡ ምእመናንን ከሐሰተኞች መምህ ራን የመጠበቅ ሓላፊነት ያለባቸው ብፁ ዓን ሊቃነ ጳጳሳትና የየሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች በተለይም ከ፳፻ወ፬ ዓ.ም ወዲህ በአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤያት ላይ በዚህ ዘርፍ የተሠሩ ሥራዎችን በሪፖርታቸው ያላቀረቡ በት አጋጣሚ የለም፡፡ በሪፖርታቸው በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሠር ገው በመግባት የቤተ ክርስቲያንን እን ጀራ እየበሉ የሉተርን ዓላማ ለማስፈ ጸም የሚሠሩ ተሐድሶ መናፍቃንን በማ ጋለጥና አንዳንዶችንም ከአገልግሎት በማገድ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን መፈ ጸም መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡ ሪፖርቱ በሚቀርብበት ወቅት ከተሰብሳቢዎች ይቀርብ የነበረው ድጋፍ የሚያሳየው ተሐድሶ መናፍቃን በሁሉም ቦታ የሚያ ካሒዱት ቅሰጣ ምን ያህል የሚያሳምም እንደሆነ እና እንቅስቃሴውን ለመግታት የሚሠሩ ሥራዎች ደግሞ በተሰብሳቢ ዎች ዘንድ ምን ያህል ተስፋ ሰጪ ዎችና አስደሳቾች እንደሆኑ ማሳያ ነው፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ኮሌጆችን የከፈተችው ሐዋርያዊ አገልግ ሎቷ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ ነው፡፡ በእነዚህ መንፈሳዊ ኮሌጆች ተም ረው እስከ ጵጵስና መዓርግ ደርሰው ቤተ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ የነበሩ፣ በማገልግል ላይ የሚገኙ አባቶች አሉ፡፡ ዛሬም ቢሆን በመናፍቃን ስውር ዘመቻ ከአማናዊቷ እምነት ፈቀቅ ያሉና በኑፋ ቄያቸው ከቤተ ክርስቲያን አንድነት የተለዩ አንዳንድ ግለሰቦች እና ጥቂት ደቀ መዛሙርት ቢኖሩም በርትዕት ሃይ ማኖት ጸንተው የተሐድሶን ስውር ደባ ሲታገሉ የነበሩና እየታገሉ የሚገኙ ጽኑዐን ደቀ መዛሙርት በመንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ መኖራቸው ልብ ሊባል ይገባል፡፡ ተሐድሶ መናፍቃኑ መንፈሳዊ ኮሌጆችን “የእኛ ዓላማ ማስፈጸሚያ ናቸው”፤ ከመንፈሳዊ ኮሌጆች ተመርቀው የሚወጡ ደቀ መዛሙርትን ደግሞ “በሙሉ ልባችን እንቀበላቸዋለን”፣ ወዘተ በማለት እነዚህን የቤተ ክርስቲያ ናችንን ተቋማት ምእመናን እንዲጠራጠ ሯቸውና እንዲሸሿቸው፣ ከፍሬያቸውም በንጹሕ ልብ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ የሚቻላቸውን ሁሉ ሲሠሩ እደኖሩ ይታወቃል፡፡ ተሐድሶ መናፍቃን ይህን እኩይ ተግባር ቢፈጽሙም መንፈሳዊ ኮሌጆች አሁንም የብዙ ሰባክያነ ወንጌል መፍለቂያዎች፣ የብዙ እውነተኛ መም ህራን መገኛዎች መሆናቸውን መረዳት ይገባል፡፡ ስለዚህ ምእመናንም ሁሉንም በጅምላ ከመጠራጠር ርቀን በፍሬያ ቸው ታውቋቸዋላችሁ እንደተባለ በትም ህርታቸው መለየት ይኖርብናል፡፡ ሁሉ ንም በጅምላ መጥላት ከጀመርን ግን ሳናውቀው የተሐድሶ መናፍቃንን ዓላማ እያስፈጸምንላቸው መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው፡፡
ሆኖም ግን በእነዚህ ኮሌጆች ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን መስለው ገብተው ብዙ ጥፋት እያደረሱ ያሉ፣ መንፈ ሳዊ ኮሌጆች ውስጥ ተምረው ያለ ፉና በመማር ላይ ያሉ ኑፋቄ ያለባ ቸው ደቀ መዛሙርት እንዳሉ በተለያዩ ጊዜያት መናፍቅነታቸው ታውቆ ከመን ፈሳዊ ኮሌጆች የተባረሩና በቅዱስ ሲኖ ዶስ ምልዐተ ጉባኤም ተወግዘው የተ ለዩ ግለሰቦች ማስረጃዎች ናቸው፡፡ በመ ንፈሳዊ ኮሌጆቹ ውስጥ የመናፍቃን ተላላኪዎች መሆናቸው የተረጋገጠባ ቸው ተማሪዎች ከመንፈሳዊ ኮሌጆች ሲባረሩ ጉዳዩን ፖለቲካዊ መልክ በመስ ጠት ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመ ለስ ቢሞክሩም የየተቋሞቹ የቦርድ አመራሮች እስከ መጨረሻ ድረስ በመከ ታተል ውሳኔው እንዲጸና በማድረግ አኩሪ ተግባር ፈጽመዋል፡፡ ይህም ሊደ ገፍ፣ ሊበረታታና በአርአያነት ሊጠቀስ የሚገባው ተግባር ነው፡፡ ተሐድሶ መናፍ ቃን በመንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ ሊሠ ሩት ያቀዱትን ሴራ በማክሸፍ በኩል ከተሐድሶ መናፍቃን ጋር አንገት ለአን ገት ተናንቀው መረጃ በማሰባሰብ አደራ ጅተው ለየኮሌጆቹ አስተዳዳር በማቅረብ መንፈሳዊ ኮሌጆችን ከሠርጎ ገቦች ለመጠበቅ በአርአያነት የሚጠቀስ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙ ደቀ መዛሙርት አሉ፡፡ እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ልጆች መንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ የራሳቸውን ሥውር ዓላማ ለማሳካት የሚሠሩ ተሐ ድሶ መናፍቃንን በማጋለጥና ተገቢው ውሳኔ እንዲሰጣቸው ለማድረግ መረጃ ዎችን ከማሰባሰብ ጀምሮ ያደረጉት ተጋ ድሎ በጊዜው የሚገኝ ጥቅምን ንቆ ዘለዓ ለማዊ ርስትን በመናፈቅ ከመናፍቃን ጋር ብዙ ተጋድሎዎችን ፈጽመው ያለፉ ቅዱሳን አበውን አርአያነት የተከተለ ነው፡፡ መንፈሳዊ ኮሌጆችን የሚመሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና የተቋማቱ ሓላ ፊዎችም በኦርቶዶክሳዊ ተማሪዎች መካከል በተሐድሶ መናፍቃን አቀነባባ ሪነት ሠርገው የገቡ መናፍቃንን ለመለ የት በየጊዜው ብዙ ሥራዎችን ሠርተ ዋል፡፡ የመንፈሳዊ ኮሌጆች ቦርዶችም በተለያዩ ጊዜያት የመናፍቃን ዓላማ አስፈጻሚ የሆኑ ግለሰቦች ላይ የቀረቡ መረጃዎችን መርምረው ኑፋቄያቸው በመረጃ የተረጋገጠባቸውን ከመንፈሳዊ ኮሌጆች እንዲባረሩ አድርገዋል፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን እስካሁን ድረስ “ኦርቶዶክሳውያን ነን”፣ “የጥንታዊ አባቶች ልጆች ነን”፣ “ቤተ ክርስቲያንን ወደ ጥንታዊ አስተምህሮዋ እንመልሳ ለን”፣ ወዘተ የሚሉ የማደናገሪያ ቃላ ትን በመደርደር የዋሀንን ሲያታልሉ ቆይተዋል፤ አሁንም በማታለል ላይ ናቸው፡፡ “ወደ እግዚአብሔር መሔጃ መንገዱ ብዙ እንጂ አንድ ብቻ አይደ ለም”፣ “ሁላችንም የምናመልከው የተሰ ቀለውን አንድ ኢየሱስ ነው”፣ ወዘተ በማለት በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በፕሮቴስታንት መካከል የአስተምህሮ ልዩነት የሌለ ለማስመሰል ብዙ ጥረዋል፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋ ሕዶ ቤተ ክርስቲያንም እነዚህ አካላት “ቤተ ክርስቲያንን እናድሳለን” በሚል ሰበብ የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ሥርዓት እና ትውፊት በመቀየር ወይም በመቀየጥ ፕሮቴስታንታዊ ለማድ ረግ የሚሠሩ መሆናቸውን በመግለጽ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አሳውቃለች፤ እያሳ ወቀችም ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያንን አስ ተምህሮ ለመቀየር ደፋ ቀና ሲሉ የነ በሩ ተሐድሶ መናፍቃን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲ ያን አንድነት የተለዩ ቢሆንም አሁንም ራሳቸውን ቀሲስ፣ መምህር፣ ዲያቆን፣ ወዘተ እያሉ በመጥራት ስለሚያደናግሩና ከአንዱ ቦታ ሲነቃባቸው ወደ ሌላ ቦታ በመሔድ ስውር ተልእኳቸውን እየፈ ጸሙ ስለሆነ ቅዱስ ሶኖዶስ ከውሳኔው በተጨማሪ አፈጻጸሙን ሊያጤነው ይገ ባል እንላለን፡፡
የሁሉም አካላት መተባበር ዓላማ ቸውን እንደሚያከሽፍባቸው የተረዱት ተሐድሶ መናፍቃን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰ ጣቸውን ውሳኔዎች የማጣጣልና ቤተ ክርስቲያንን የማቃለል ሥራዎችን ለዚሁ ዓላማ ማስፈጸሚያ በከፈቷቸው ድረ ገጾች ሲያስተጋቡት እንደቆዩ በሁሉም ዘንድ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህ ደግሞ አቅ ጣጫ በማስቀየርና በማዘናጋት የፈለጉ ትን ጉዳይ ለመፈጸምና ለማስፈጸም የሚጠቀሙበት ስልት ነው፡፡ እነዚህ አካላት መናፍቅነታቸው ተረጋግጦ ተወ ግዘው ከቤተ ክርስቲያን መለየታቸው፣ ከአገልግሎት መታገዳቸው እና ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሴራቸው መገለጡ ተሳስተ ናል እንመለስ እንዲሉ አላደረጋቸውም፡፡ ይህን በማለት ፋንታ በተለያዩ ድረ ገጾቻ ቸው ላይ ውሳኔውን በሰጠው በቅዱስ ሲኖዶስ ሲሳለቁና ቤተ ክርስቲያንን ሲሳደቡ ቆይተዋል፡፡ በድርጊታቸው አፍ ረው ከመመለስና ከመጸጸት ይልቅ ቤተ ክርስቲያንና ቅዱስ ሲኖዶስን በማቃለል ምእመናን በብፁዓን አባቶች ላይ ያላ ቸው እምነት እንዲጠፋና ጥርጣሬ እንዲ ያድርባቸው ማድረግን እንደ ሥራ ተያ ይዘውታል፡፡ ይህ ድርጊታቸው ተሐ ድሶ መናፍቃን ምን ያህል ክፉ መንፈስ እንደተቆጣጠራቸውና እግዚአብሔርን እንደ አምላክነቱ ስላላከበሩት ለማይገባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው የሚለው የመጽሐፍ ቃል እየተፈጸመባቸው እን ደሆነ ማሳያ ነው፡፡ የድፍረታቸው ድፍ ረት በአሁኑ ወቅት ቤተ ክርስቲያንን የሚመራት መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን ግለሰ ቦች ናቸው በማለት ምእመናንን ከቤተ ክርስቲያን ለማስወጣትና የቅዱስ ሲኖ ዶስን ውሳኔ እንዳይቀበሉ ለማድረግ ብዙ ብለዋል፡፡ በተለይም አባ ሰላማ፣ ጮራና ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የሚባሉት ድረ ገጾቻቸው ቅዱስ ሲኖ ዶስ ያወገዛቸውን ተሐድሶ መናፍቃንን በመደገፍና ቅዱስ ሲኖዶስንና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን በማቃለል ድፍረት የተሞሉ ጽሑፎችን የሚያወጡባቸው የስድብ አፎቻቸው ናቸው፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን በ፳፻ወ፬ ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተላለፈ ውን ውሳኔ ተከትለተው አባ ሰላማ በሚ ባል ድረ ገጻቸው ላይ “ተወጋዦች አው ጋዦች፣ አውጋዦች ተወጋዦች የሆኑ ባት ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርእስ ባወ ጡት ጽሑፍ ላይ ቤተ ክርስቲያንን እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን እንዲህ በማ ለት ነበር የተሳደቡት፡-
ባለፉት ፳ ዓመታት ተወግዘው የተ ባረሩ ሁሉ በሕጋዊ አካል ተወግዘው የተባረሩ አይደሉም። በሕገ ወጦችና በማያስወግዝ ምክንያት በሕገ ወጥ መንገድ «የተወገዙ» ናቸው። የሕግ የበላይነት ባልሰፈነባትና ሁሉም አዛዥ በሆነባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መወገዝ የሚገባቸው ሰዎች መወገዝ የማይገባቸ ውን ሰዎች ሲያወግዙ ኖረዋል። ይኸው አሠራር አሁንም ቀጥሏል። ቤተ ክር ስቲያኗ ምን ያህል እንደዘቀጠች፣ ምን ያህል አንቱ የሚባል ሰው እንደታጣ ባት፣ ምን ያህል ከክርስቶስና ከሐዋር ያት፣ እንዲሁም ከሠለስቱ ምእት ትምህርት እንደራቀች ያሳያል።
“በረከታችሁም ሆነ ውግዘታችሁ ማንንም አያድንም፣ አይገድልምም” በሚል ርእስ በጻፉት ሌላኛው ጽሑፋ ቸው ደግሞ ከሐዋርያት ጀምሮ ባልተቋረጠ ሐዋርያዊ ክትትል ሥልጣነ ክህ ነት ያላቸውን ሊቃነ ጳጳሳት በማቃ ለልና ከተሐድሶ መናፍቃን በማሳነስ፡-
አንድ መንፈሳዊ ሥልጣን የሌለ ውና ለመንፈሳዊ ሥልጣንም የማይገዛ ስመ መንፈሳዊ የመናፍስትና የሙታን ጠሪ ስብስብ አንድ መንፈሳዊ የወን ጌል አገልጋይ የማውገዝም ሆነ የመለ የት ሥልጣን የለውም። አቅም ያንሰዋል! ኃይል ያለው ሥራ ለመሥራት በጥቂ ቱም ቢሆን ኃይል ያስፈልጋል። ይህ ማለት በሌላ አገላለጽ ሥጋ የሥጋን ሥራ ከመሥራት በዘለለ በመንፈሳዊ ዓለም ላይ አሁንም በድጋሜ እጽፈዋለሁ አንዳች ሥልጣን የለውም።
በማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንደማይገዙ ብቻ ሳይሆን ቅዱስ ሲኖ ዶስ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን ያለው አካል እንዳልሆነ አድርገው ጽፈዋል፡፡ በዚሁ ለጥፋት ዓላማ በከፈቱት አባ ሰላማ በሚባለው ድረ ገጻቸው ቋሚ ቅዱስ ሲኖዶሱ በ፳፻ወ፯ ዓ.ም በተሐድሶ መናፍቃን ላይ የወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ “ክርስቶስን የምታሳድድ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ቤተ ክርስቲያን ትሆና ለች?” በሚል ርእስ “ሲኖዶሱ በአንድ በኩል ፍልሰት በዝቶአል እያለ ሲናገር በሌላ በኩል ደግሞ ወንጌል እየሰበኩና ሕዝቡን ከፍልሰት እየገቱ ያሉ አገልጋዮ ችን ማሳደድ ሥራየ ተብሎ ተይዟል” በማለት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ አጣጥ ለውታል፡፡
ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በሚለው ድረ ገጻቸው ደግሞ ቅዱስ ሲኖዶስ ከሐዋርያት እውነት የራቀ ለቅዱሳን የጸጋ ስግደት ይገባል ብላ የምታስተምር ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን መና ፍቅ፣ ራሳቸውን ደግሞ ጻድቃን አድር ገው ቅዱስ ሲኖዶስም ቅዱሳን የሆኑ እነርሱን እያሳደደ መናፍቅ የተባሉ ኦርቶ ዶክሶችን እንደሚደግፍ በዚህ መልክ አቅርበዋል፡፡
ሲኖዶሳችን እውነትን እንደ ሐዋርያት ቢያውቅና ቢከተል ኖሮ እነዚህን ለማርያም፣ ለመስቀል፣ ለታቦት፣ ለሥ ዕል [የጸጋ ስግደት] መስገድ አይገባም ብለው የሚሟገቱ ሰዎችን ስም በማክ ፋት መናፍቅና ጸረ-ማርያም ብለው በሥ ቃይ እንዲሞቱ ያደረጉ ጸረ-ኦርቶዶክስ አቋም ይዘው ዘወትር በኦርቶዶክስ ተዋ ሕዶ ጥላ ሥር የሚነግዱ መናፍቃንን እሺ ቢሉ በትምህርት ይመልስልን፣ እንቢ ቢሉ ደግሞ በውግዘት ይለይልን ነበር፡፡ እንደ አለመታደል ሆኖ ሲኖዶሳ ችን መናፍቃንን በመደገፍ ጻድቃንን ያሳድዳል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምት ፳፻ወ፯ ዓ.ም መደበኛ ጉባኤው ላይ ስለ ተሐድሶ መናፍቃን በተያዘው አጀንዳ ላይ በተ ወያየበት ወቅት ከችግሩ አሳሳቢነት አንጻር ኮሚቴ ተቋቁሞ ሰፋ ያለ ጊዜ ተሰጥቶት ጥናቱን በጥልቀት አጥንቶ እንዲያቀርብ በወሰነበት ወቅት “ቤተ ክርስቲያን ተሐድሶን ከመቀበል ይልቅ ለማጥናት ኮሚቴ የማቋቋሟ አንድምታ” በሚል ጽሑፍ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያሰቡት ዓላማቸው እንዳይከሽፍባቸው ቅዱስ ሲኖዶስን በመቃወም እንዲህ ጽፈዋል፡፡
ከታሪክ መማር የተሳነው ቅዱስ የተባለው ሲኖዶስ ለአስፈላጊውና ለጠቃ ሚው የተሐድሶ እንቅስቃሴ ሌላ ስም በመስጠትና በቤተ ክርስቲያን ሌላ ትልቅ አደጋ ጋርጧል በሚል በማኅ በረ ቅዱሳን ከሳሽነት ሕጋዊም፣ መንፈ ሳዊም፣ ሞራላዊም፣ ሕሊናዊም አካሔድን ባልተከተለና ግብታዊነት በተሞላው መንገድ ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ውግዘት አስተላለፈ፡፡ … በዚህ ዘመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስ ቲያንንና ሃይማኖትን ከተሐድሶ አራማ ጆች ትምህርት ለመጠበቅ በሚል ተሐ ድሶ ሲል የፈረጃቸውን ወገኖች በማሳ ደድና በማውገዝ ተግባሩ ገፍቶበታል፡፡ ስለተሐድሶ እንዲያጠኑ በሚል ሰዎች ንም ጠቅላይ ቤተክህነት መድቧል፡፡ ጥናቱ አስፈላጊ ሊሆን ቢችልም ትኩ ረቱ ግን ተሐድሶን ለማጥፋት የሚል መሆኑ ቤተክህነቱ አሁንም በእንቅልፍ ላይ እንደሚገኝ የሚያሳይ ነው፤
በ፳፻ወ፬ ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ከተወገዙት ግለሰቦች መካከል አሸናፊ መኮንን፣ አግዛቸው ተፈራና ጽጌ ሥጦ ታው ውግዘቱን በመቃወም ስላስገቡት “የይግባኝ ደብዳቤ” ሲያትቱ ደግሞ፡-
የግንቦቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ቤተ ክርስ ቲያንን የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ በማድረግ ያዋረደበትን ውሳኔ ማሳ ለፉ ይታወሳል፡፡ ይህን የራሱን ክብር የቀነስበትን፣ በታሪክ ተወቃሽ የሚያደ ርገውንና ብዙዎችን ያሳዘነውን፣ የቤተ ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ባልተከ ተለና፣ በየትኛውም መስፈርት ሲመዘን ሕገ ወጥ ሆኖ የተገኘውን ውግዘት፣ «ተወጋዦቹ» እየተቃወሙት ነው፤ በማለት ጽፈዋል፡፡
ውሳኔውን የተሳሳተና ሕገ ወጥ በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስም ቤተ ክርስ ቲያንን የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ እንድትሆን ያደረጋት አስመስለው ጽፈ ዋል፡፡ በእርግጥ ይግባኝ አቅራቢ የተባ ሉት ተወጋዦችም ያስገቡት ደብዳቤ በአባ ሰላማ ድረ ገጽ እንደወጣው ይቅ ርታ ይደረግልን ወይም ተሳስተናልና እንታረም የሚል ሳይሆን በጽጌ ሥጦ ታው አገላለጽ “ያስተማርኩት፣ የጻፍኩ ትና የተናገርኩት ሁሉ ስሕተት መሆ ኑን ስላመንኩ ይህን ሁሉ ስሕተቴን ቅዱስ ሲኖዶስ ተረድቶልኝ ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ትምህርቱን እንድ ማር ይፈቀድልኝ ዘንድ በታላቅ ትሕ ትና አመለክታለሁ የሚል የይቅርታ [አሳብ] እንደሌለኝ በድጋሚ አረጋግጣለሁ” የሚል የትዕቢት ደብዳቤ ነው፡፡ ተሐድሶ መናፍቃን በተለያዩ ዘዴ ዎች ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያስተላልፋቸ ውን ውሳኔዎች ሲቃወሙና በቻሉት መጠን ለተቃውሟቸው ድጋፍ የሚሰጡ አካላትን በቤተ ክስቲያን መዋቅር ውስጥ አሥርገው ለማስገባት ሲሠሩ ቆይተዋል፡፡ ይኸው ዓላማቸው ተሳክቶ ላቸው በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ የቤተ ክርስቲያንን እንጀራ እየበሉ የቅ ዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በፊርማ ለማስ ቆም የሚሠሩ ጥቂት አካላትን ማግ ኘት ችለዋል፡፡ ለዚህም ነው ተሐድሶ መናፍቃን በተለያዩ ድረ ገጾቻቸው የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ አንቀበልም በማለት ከመጻፍ እና ከመሳደብ አል ፈው ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር አሥርገው ባስገቧቸው አንዳ ንድ ግለሰቦች በኩል የቅዱስ ሲኖዶ ስን ውሳኔዎች ለማስቀልበስ እየ ሠሩ ያሉት፡፡
ይህን ዓላማቸውን ዕውን ለማድ ረግ በተለይም በመንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ አሥርገው ባስገቧቸው አንዳንድ ተልእኮ አስፈጻሚ ግለሰቦች በኩል እነ ርሱ የማይፈልጉትን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ለመቃወም መምህራንን፣ ተመር ቀው የወጡና በመማር ላይ ያሉ የነ ገረ መለኮት ደቀ መዛሙርትን እና ጉዳዩ የማይመለከታቸው የዋሀን ምእመናንን ፊርማ እንዲያሰባስቡላቸው እየተጠቀሙባቸው ይገኛሉ፡፡ ይህም ድር ጊት ቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጣቸው መመ ሪያዎችና የሚወስናቸው ውሳኔዎች ተግባራዊ ቢደረጉ ለእንቅስቃሴያቸው እንቅፋት እንደሚሆንባቸው በማመን አቅጣጫ ለማስቀየርና ለማደናገር የሚ ጠቀሙበት ስውር ስልት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን፣ ቅዱስ ሲኖዶስን፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳ ሳትን እንደፈለጋቸው ሲሳደቡ የሚጠ ይቃቸው አካል ባለመኖሩ ምክንያት የልብ ልብ ተሰምቷቸው የሚፈጽሙት የዕብሪት ተግባር ነው፡፡ ተሐድሶ መና ፍቃን መናፍቅነታቸውን በራሳቸው ጽሑ ፎች አውጀው፣ የራሳቸውን የእምነት ድርጅት አቋቁመውና የራሳቸውን የእምነት መግለጫ አውጥተው ቤተ ክር ስቲያንን የማፍረስ ተልእኳቸውን ዕውን ለማድረግ እየሠሩ መሆናቸው እየታ ወቀ “ዐይናቸውን በጨው አጥበው” አሁንም ኦርቶዶክሳውያን ነን በማለት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሠርገው በመግ ባት ሁከት እየፈጠሩ ይገኛሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ሰላም የማይወዱት እነዚህ አካላት በአንጻራዊ መረጋጋት ላይ ይገኙ የነበሩትን መንፈሳዊ ኮሌጆችን አሥር ገው ባስገቧቸው ጥቂት ተላላኪዎች አማካኝነት በተለያዩ የስድብ አፎቻቸው ሲያጮኹት የኖሩትን ዓላማ ለማሳካት ሊጠቀሙባቸው በስውር በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጠቃ ላይ በቤተ ክርስቲያን ላይ በተለይ በመ ንፈሳዊ ኮሌጆች ላይ የተነጣጠረው የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ አሳሳ ቢና አስጊ መሆኑን ተረድቶ ኮሚቴ አቋ ቁሞ ሥራዎችን መሥራት በጀመረበት በዚህ ወቅት፣ መንፈሳዊ ኮሌጆችም ስንዴ ውን ከገለባው የማጥራት ሥራ ለመሥ ራት በጀመሩበት ጊዜ፣ ሰንበት ትምህ ርት ቤቶችና ወጣቶችም ተሐድሶ መና ፍቃንን በማጋለጥ መረጃዎችን በማሰባ ሰብ ለሚመለከተው አካል እያቀረቡ ባሉበት በዚህ ሰዓት “መናፍቅ የሚባል ነገር የለም” በማለት የቅዱስ ሲኖዶ ስን ውሳኔ ለማኮላሸት ፊርማ የሚያ ሰባስቡ አካላት መነሣታቸው እየተሰማ ነው፡፡ ይህ ድፍረት ከቤተ ክርስቲያን ዓላማ መውጣትና ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳ ኔም አለመታዘዝ ነው፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን ቤተ ክርስቲ ያን ውስጥ አንድ ችግር ፈጥረው መዋ ቅሩ ችግሩን ለመፍታት ደፋ ቀና በሚል በት ሰዓት እነርሱ የራሳቸውን ዓላማ ለማሳካት መሯሯጥን ልምድ አድርገው ሲሠሩበት የቆዩት ጉዳይ ነው፡፡ ቅድ ስት ቤተ ክርስቲያን የመልካም አስተዳ ደር እጦት መኖሩን አምና የመልካም አስተዳዳር ችግሮችን ለመቅረፍ መሥ ራት አለብን በሚል በሁሉም አህጉረ ስብከት በሚባል ደረጃ ውይይቶች እየተደረጉና ሥልጠናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም በጥቅምት ፳፻ወ፰ ዓ.ም መደበኛ ጉባኤ ባወጣው መግለጫ የመልካም አስተዳደር እጦትና የሙስና መስፋፋት ለቤተ ክርስቲያን ፈተና መሆ ኑን እና የችግሩ መነሻና ምንጭ ይታ ወቅ ዘንድ አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያ ኗን ሁለንተናዊ ችግር የሚያጠና ብፁ ዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ዐቢይ ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የመልካም አስተዳደር ችግር የአ ንድ ተቋም ችግር ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ መዋቅሮች ላይ የሚታይ አጠቃላይ ችግር መሆኑን ወስኖ እያለ ተሐድሶ መናፍቃን የአስተ ዳደር ችግር አለ ሲባል ለራሳቸው ዓላማ በሚጠቅማቸው መልኩ ሌላ ቅርጽ ሰጥተውና ስድብ አስመስለው ጉዳዩን ያስተጋቡልናል ብለው ለሚያስ ቧቸው አካላት ያቀርቡላቸዋል፡፡ ይህን የመናፍቃን ተንኮል ያልተረዱ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሓላፊነት ያላቸው አንዳንድ ግለሰቦችም የመልካም አስተዳዳር ችግር አለ መባሉን መናፍቅ ናችሁ የመባል ያህል ይፈሩታል፡፡ ይህ ግን በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ ታምኖበት ለውጥ ለማምጣት እየተሠራበት ያለ መሆኑን ማንም የማይስተው ሐቅ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያንን መልካም ነገር መስማት የማይፈልጉት ተሐድሶ መናፍቃን ግን በቤተ ክርስቲያን ደረጃ የታመነውን እውነት የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን ተቋማትን በመምራት ላይ ለሚገኙ አካላት “እንዲህ ተብላችሁ ተሰ ደባችሁ” በማለት የሐሰት ክስ በማቅረብ የቤተ ክርስቲያን ችግሮች ተፈተው ለውጥ እንዳይመጣ ይሠራሉ፡፡
በአጠቃላይ ተሐድሶ መናፍቃን በተለ ያዩ የስድብ አፎቻቸው የሚጮኹትን ጩኸት የሚሰማቸው አካል ባለማግኘታ ቸው ምክንያት ወደ ቤተ ክርስቲያን አሥርገው ባስገቧቸው አንዳንድ አካ ላት በኩል የራሳቸው ድብቅ ዓላማ ያላቸው ጥቂት ግለሰቦችን በማባበል ከውጪ ሆነው ሲጮኹለት የነበረውን ዓላማቸውን ለማስፈጸም ይጠቅመናል ብለው ያሰቡትን ማደናገሪያ ሁሉ ለመጠ ቀም እየሞከሩ ነው፡፡ ይህም ለቤተ ክርስቲያን ተቆርቋሪ በመምሰል በየጊ ዜው የሚፈጠሩ ወቅታዊ ጉዳዮችን ተጠ ቅመው አቅጣጫ በማስቀየር ለዓላማ ቸው ማስፈጸሚያነት የሚጠቀሙበት የተለመደ ስልት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የራሷ ሥርዓትና መዋቅር ያላት፣ ውሳኔ ዎችን የምትወስነው ከሐዋርያት ጀምሮ በተሠራ ሕግና ሥርዓት በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥንቃቄ እና በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ሆኖ ሳለ ተሐድሶ መናፍቃን የቅዱስ ሲኖዶ ስን ውሳኔ በግለሰ ባዊ ዓላማ ለማስቀ ልበስ እየተሯሯጡ መሆናቸው ጥፋታ ቸውን አምነው ከመመለስ ይልቅ ኑፋ ቄያቸው በቤተ ክርስቲያን ዕውቅና እን ዲሰጠው ለማድረግ መሞከር ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን የመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካል በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡ ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አለመታዘዝ ትዕቢትም ኑፋቄም ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ተሐድሶ መናፍቃን ብዙ የዋሀንን ለማደናገርና ተባባሪ ለማ ብዛት የሚጠቀሙበት ስልት እውነቱ ተደብቆ ሐሰቱ እውነት መስሎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሠርጎ እንዲገባ ማድረግ በመሆኑ ይህን የጥፋት ተልእኮ ለመግ ታት ሁሉም አካላት ሊተባበሩበት ይገ ባል፡፡ 

አምልኮተ ሰይጣን – ፍጻሜ “ተሐድሶ”?

ባለፉት ተከታታይ ዕትሞች ስለ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ አጠቃላይ ሁኔታ እና የትኩረት አቅጣጫዎች እንዳ ቀረብንላችሁ ይታወቃል፡፡ በዚህ ዕትም ደግሞ የተሐድሶ መናፍቃን ግብ ምን እንደሆነ እናስነብባችኋለን፤ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ፡፡
እሱባለው በለጠ የተባሉ ጸሐፊ “የገሃነም ደጆች ፕሮቴስታንታዊ ጅሃድ በኢትዮጵያዊነት – ተዋሕዶነት ላይ ሲፋ ፋም” በሚለው መጽሐፋቸው አውሮፓ ውያን፣ የካቶሊክና የፕሮቴስታንት እንዲሁም የተሐድሶ መናፍቃን የኢት ዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስ ቲያንን ለማጥቃት የፈለጉበትን ምክን ያት ሲገልጡ “ፈረንጆች ሃይማኖታ ችንን ከገደሉ፣ ቅድስት ኢትዮጵያን በባርነት ለመያዝ ቀላል መሆኑን ስለ ሚያውቁ ነው ቤተ ክርስቲያንን የጥ ቃት ዒላማቸው ያደረጓት” (ገጽ ፳፯) ብለዋል፡፡ በተጨማሪም “ሁሉም ወራሪ ዎች ከግራ ይምጡ ከቀኝ፣ በነጮችም ይፈጸሙ በዐረብ/ቱርክ፣ ወረራው በጦር ይሁን ወይም በሐሳብ፣ ሁሉም ወራሪዎች የጥቃታቸው ዋና ዒላማ የሚያደርጓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ነው፡፡ ግን ሁሉም ወራሪዎች ድል የተደረጉት የአንድነትና የነጻነት ምንጭ በሆነችው በዚች መከረኛ ቤተ ክርስቲያን ነው” (ገጽ ፳፫-፳፬) በማለት ጽፈዋል፡፡

ጸሓፊው ባለፉት አምስት መቶ ዓመታት በኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ የተቃጡት የውጪ ወረራዎች፣ በነጮች አማካኝነት የተቀሰቀሱ የእርስ በእርስ ጦርነቶች፣ የካቶሊክ ሚሲዮና ውያን ቅሰጣ፣ ኮሚኒስታዊ ርእዮተ ዓለምና ፕሮቴስታንታዊ ዘመቻዎች ሁሉ አንድ ዓይነት እና ጸረ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቋም ያላቸው ናቸው፡፡ ሁሉም የቅድስት ኢትዮጵያ ተዋሕዶ ሃይማኖትን “በደንቆሮነት”፣ “በጸረ ሕዝብነት”፣ በኋላ ቀርነት”፣ “በጣ ዖት አምላኪነት”፣ በ”ኦሪታዊነት”፣ አሁን አሁንማ የልብ ልብ አግኝተዋልና በይፋ በየቤተ አምልኮውና ማለቂያ በሌላቸው ዕለታዊ፣ ሳምንታዊ፣ â€Â¦ ልሳኖቻቸው “በሰይጣንነት” ይከሷታል ይላሉ (ገጽ ፳፬)፡፡
ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ ሊያ ሳኩት የፈለጉትን ግባቸውን ሲናገሩ ደግሞ እንዲህ ብለዋል፡፡ “በእምነታቸው ፍርድ ቤትም የሚጠይቁት አንድ ነገር ነው – የቅድስት ኢትዮጵያ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የስቅላት ሞት፡፡ ይህም ተፈርዶላቸው፣ የመስቀያ ገመዱን አዘ ጋጅተው፣ የመስቀያ ቦታውን መር ጠው፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን እግር ተወርች አስረው ዐይኖችዋን ሸፍ ነው፣ ከእስር ቤት አውጥተው ወደ መስ ቀያ ቦታ እየነዷት ይገኛሉ፡፡ በዚህ የቅድ ስት ኢትዮጵያ ተዋሕዶ ሃይማኖት ወደ ሞት መነዳት፣ አጃቢ ወታደር በመሆን ብዙ መቶ ሺ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ አስፈጻሚ፣ ካድሬ፣ ጽንፈኛ፣ ጅሀደኛ፣ ፕሮፖጋንዲስት በመሆን እርማቸውን ለመብላት እየተቅበዘበዙ ነው፡፡ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ የፕሮቴስታንት ርእዮተ ዓለም ሰለባ ኢትዮጵያውያን ጀሌዎችም â€Â¦ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስ ቲያንን ተዝካር ለመብላት ከወዲሁ እየጓጉ ነው” (ገጽ ፳፬-፳፭) በማለት አስቀምጠዋል፡፡
የካቶሊክና የፕሮቴስታንት ሚሲዮ ናውያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ በየዘመናቱ ብዙ ደክመዋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ አስይ ዘው ወንጌል እንስበክላችሁ ያሉበት ጊዜ ነበር፡፡ በኀይል ለመደምሰስ መትረየስና ታንክ ባርከው የላኩበትም ጊዜ ነበር፡፡ በዘመናዊ ሥልጣኔ ወደ ፊት እናራምዳ ችሁ ብለው መጥተው በመርዝ ጋዝ እንድናልቅ ያደረጉበት ጊዜ ነበር፡፡ የሞ ከሩት ሁሉ አላዋጣ ብሏቸው ሌላ ዘዴ ሲፈልጉ የፕሮቴስታንት ድርጅቶችን ተገን አድርገው በመግባት ለሆዳቸው ያደሩ “መሪጌታ፣ መነኩሴ፣ ዲያቆን፣ ወዘተ” ነን ባዮችን መጠቀም ቤተ ክር ስቲያንን ለማፍረስ እንደሚጠቅማቸው ተረዱት፡፡ ስለዚህ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ በጦርና በሰይፍ ለማሳካት ያልተቻለውን የምዕራባውያንን ምኞት “በኢትዮጵያዊ ፈረንጆች” ለማሳካት ታልሞ የተነደፈ እንቅስቃሴ ነው፡፡ የመ ጨረሻ ዓላማው ምዕራባውያን የራሳቸ ውን አብያተ ክርስቲያናት” ጭፈራ ቤት እንዳደረጓቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ወደ ጭፈራ አዳራሽነት መቀየር፣ ምእመናንን ደግሞ ፍጹም ዓለማውያን (ሴኩላር) በማድረግ ለግብረ ሰዶማዊነትና ለአምልኮተ ሰይ ጣን ማዘጋጀት ነው፡፡ የተሐድሶ እንቅስቃ ሴው ግብ አንድና ብቸኛ ሳይሆን ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር መንግሥት በመለየት የሰይጣን ተገዢዎች በሚያ ደርጉ አስነዋሪ ድርጊቶች ውስጥ ማስገ ባት ነው፡፡ ክርስቶስን እንሰብካለን ብለው የተነሡት ፕሮቴስታንቶች፣ ሚሲዮኖቻ ቸውን እየላኩ እኛን “ወንጌል እናስተ ምራችሁ” የሚሉን የተሐድሶ መናፍቃን የጥፋት አባቶች እየደረሱባቸው ያሉትን እና ሊደርሱባቸው የሚፈልጓቸውን ግቦች እንመልከት፡፡
፩. ዓለማዊነት (Secularism)፡- የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የመጨ ረሻ ግብ “ክርስትና በልብ ነው” በሚል ፈሊጥ ልባቸው የፈቀደውን ሁሉ ማድ ረግ ነው፡፡ ሃይማኖት የሰው ልጅ አንዱ ማንነቱና ምንነቱ መገለጫ ነው፡፡ ነቢዩ ዮናስ ምንድን ነህ? ሥራህስ ምንድን ነው? ተብሎ ሲጠየቅ “ዕብራዊ ነኝ፤ ሥራዬም ሰማይና ምድርን የፈጠረ እግዚአብሔርን ማምለክ ነው” ብሎ የተናገረው ሃይማኖት የሰው ልጅ ማን ነት መገለጫ መሆኑን ማረጋገጫ ነው፡፡ ሰው ከቀለሙ፣ ከተወለደበት ዘር፣ ከተወለደበት ቦታ በላይ አምኖና ፈልጎ የተቀበለው ሃይማኖት እውነተኛ የማን ነቱ መገለጫ ነው፡፡ የሰው ልጅ ከፈለ ገው እናትና አባት፣ ከፈለገው ቦታ፣ ከፈለገው ዘር፣ የሚፈልገውን ቀለም ይዞ መወለድ አይችልም፡፡ ይህ በፈቃደ እግዚአብሔር የሚከናወን ስለሆነ ከሰው ልጆች ቁጥጥርና ከአቅማቸው በላይ የሆነ አምላካዊ ጥበብ ነው፡፡ ስለዚህ ሰው ስለ ማንነቱ ሲጠየቅ በትክክል የሚያውቀውና የሚያምንበት ማንነቱ ሃይማኖቱ ነው፡፡ የሰው ሰብእ ናም የሚወሰነው ሊገራው፣ ሊያሸንፈ ውና ሊያስተካክለው በሚችለው በውሳ ጣዊ ማንነቱ እንጂ በሥነ ፍጥረት በተለገሰው ውጫዊ ገጹ አይደለም፡፡
ይህን የሚያውቁ ምዕራባውያን ሰው ውስጣዊ ማንነቱን ረስቶ በውጫዊ ነገሮች ማለትም በአለባበሱ፣ በአመጋ ገቡ፣ በአነጋገሩ፣ ወዘተ ላይ ትኩረት እንዲያደርግ በመሥራት ላይ ናቸው፡፡ ሃይማኖት በእኛ በደካሞች እጅ ወድቆ የሆነውን ሳይሆን ዋኖቻችን ኖረው ባሳዩን መሠረት ለዓለም ሙት ሆኖ ለክርስቶስ ሕያው መሆን ነው፡፡ ለመጥፎ ነገር ሞቶ ለመልካም ነገር ሕያው መሆን ነው፡፡ ሰው ሁሉ በእግዚአብሔር ካመነና በእግዚአብሔር ከታመነ (ፍቅረ እግዚአብሔርን እና ፍቅረ ቢጽን ገንዘብ ካደረገ) የእርስ በእርስ ጦርነት፣ ክህ ደት፣ በሌሎች ጉዳት መደሰት፣ ግዴለ ሽነት፣ የሞራል ዝቅጠት፣ ዝሙት፣ ክፋት፣ ወዘተ አይኖርም፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን መብታችንን ለማስከበር ብለን ለምናቋቁማቸው የፍትሕ ተቋማት፣ ራሳችንን ለመከላለክል ብለን ለመሣሪያ መግዣ የምናወጣው ገንዘብ ለበጎ አድራ ጎት ይውል ነበር፡፡ ያደጉ አገራትም የድሀ አገራት ሕዝቦችን ከምድረ ገጽ ለማጥ ፋት የሚያግዙ የበሽታ መፈልፈያ ቤተ ሙከራዎችን ለመገንባት የሚያወጡት ወጪ ለበጎ ዓላማ ቢውል ስንት ድሆ ችን መመገብ በቻለ ነበር፡፡
የምዕራባውያን “ቸርቾች” ከላይ የጠቀስናቸው ችግሮች እንዲፈጠሩና እንዲባባሱ ታላቅ አስተዋጽኦ አድርገ ዋል፡፡ ሰው በጋራ የሚያምነው እውነት እንዳይኖር “ክርስቶስን በገባህ መልኩ ግለጠው/ አምልከው” እየተባለ ግለኝነት የተስፋፋው በፕሮቴስታንት ቸርቾች ነው፡፡ ቸርቾቻቸው የአምልኮ ቦታነታ ቸው ቀርቶ ቡና ቤት፣ ፊልም ቤት፣ ጭፈራ ቤት፣ ሙዚየም፣ የገበያ አዳራሽ ሆነዋል፡፡ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ በመቀበል ፈሊጥ የተጀመረው እምነት ቤተ ክርስቲያን ባለመሔድና እግዚአብሔር የለም በሚል ፍልስፍና ተደመደመ፡፡ ዛሬ ላይ የካቶሊክም ሆኑ “ካቶሊክ ኢየሱስን ጥላለች” ብሎ ሉተር የመሠረተው የፕሮቴስታንት እምነት ቸርቾች ወደ ፍጹም ዓለማዊነት (Secularism) “አድገዋል”፡፡ ፕሮቴስታን ቲዝም ከእምነት ደረጃ ወጥቶ ወደ ፖለቲካ ርእዮተ ዓለምነት ተሸጋግ ሯል፡፡
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት የካቶ ሊክና ፕሮቴስታንት እምነት ተስፋፍ ቶባቸው የነበሩ አገራት ዛሬ ላይ እግዚ አብሔር የለም የሚል ፍልስፍና የሚከ ተሉ ሆነዋል፡፡ ለምሳሌ፡- የራሷን ሕዝብ ኢ-አማኒ አድርጋ አሁንም ድረስ በተለ ያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ስም ወደ ድሀ አገራት በመግባት (በተለይም አፍሪካውያንን) ፕሮቴስታንት በማድረግ የምትታወቀው ስዊድን ከሕዝቧ ቁጥር ፴፬ በመቶ የሚሆነው እግዚአብሔር የለም የሚል ነው፡፡ ፴፱ በመቶው ስለ እምነት ግድ የሌለው ነው፡፡ በፈረንሳይም እንዲሁ ፵ በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የእግዚአብሔርን ህልውና የማይቀበል ነው፡፡ በስመ ክርስትና የሚኖሩትም ወደ ቤተ እምነታቸው አይሔዱም፡፡ ለምሳሌ፡- በታላቋ ብሪታንያ ክርስቲያን ነኝ ብሎ የሚያምነው ሕዝብ ፸፪ በመቶ ሲሆን “ቤተ ክርስቲያን” የሚሔደው ሕዝብ ግን 1.4 በመቶ ብቻ ነው፡፡ የሉተር “ሃይማኖት” በተፈጠረባት አገር በጀር መን ፸፪ በመቶ በተመሳሳይ ሁኔታ ክርስቲያን ነኝ ብሎ የሚያምን ሲሆን “ቤተ ክርስቲያን” የሚሔደው ግን 1.2 በመቶ ብቻ ነው፡፡
ዓለሙ በአሁኑ ሰዓት በዘመናዊ ነት ስም ግለኝነትን እያበረታታና ተደ ጋግፎና ተባብሮ የመኖርን መልካም እሴት እያጠፋ ነው፡፡ የሦስተኛው ዓለም አገራት በምግብ፣ በንጹሕ ውኃ አቅ ርቦት፣ በመጠለያ አቅርቦት፣ በመጀመ ሪያ ደረጃ የትምህርት አገልግሎት፣ በጤና አገልግሎት፣ በአጠቃላይ ለመ ኖር በመሠረታዊነት የሚያስፈልጉ ነገሮችን ማሟላት አቅቷቸው በሺ ዎች የሚቆጠሩ ነፍሳት በየቀኑ ይሞ ታሉ፡፡ ያደጉ አገራት ደግሞ እነዚ ህን መሠረታዊ የሥጋ ፍላጎቶች ለማ ሟላት ከሚያስፈልገው ወጪ በዐሥር እጥፍ የሚበልጥ ገንዘብ ለኮስሞቲክ ስና ለውሻ ምግብ ያወጣሉ፡፡ ዓለም አንዱን በቁንጣን ሌላውን በጠኔ መግደል ጠባይዋ መሆኑን ከዚህ ተግባር መረ ዳት ይቻላል፡፡
የሚቀነቀኑ ርእዮተ ዓለሞች (ፌሚ ኒዝም፣ ሊበራሊዝም፣ ሴኪዩላር ሂውማ ኒዝም፣ ወዘተ) እና የሚቀረፁ ሥር ዓተ ትምህርቶች መንፈሳዊነትና ሥነ ምግባራዊ እሴት እንዳይኖራቸው እየ ተደረጉ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- በአገራችን እግዚአብሔር የለም የሚል ርእዮተ ዓለም ነግሦ በነበረበት ጊዜ “ሳይማር ያስተማረንን ሕዝብ ማገልገል አለብን” የሚል አስተሳሰብ ነበር፡፡ ይህም የአብ ነት ትምህርቱን እንደ ትምህርት ላለ መቁጠር የምዕራቡን ትምህርት ባጠኑ ልሒቃን መነገር የጀመረ አስተሳሰብ ነበር፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሕፃናት የሚዘጋጁ የመዝናኛ ቁሳቁሶች፣ ለሴቶች የሚዘጋጁ አልባሳት፣ ለሕ ዝብ ዐይን የሚደርሱ ፊልሞችና ማስ ታወቂያዎች፣ ወዘተ በአጠቃላይ መል ካም ሥነ ምግባርን የሚያስረሱ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ድርጊቶች እስካሁን ድረስ በተወሰኑ ቡድኖች አነሣሽነት የሚቀነቀኑ ነበሩ፡፡ አሁን ግን “ሃይማኖታዊ መልክ” እየተሰጣቸው በእምነት ድርጅቶች በዓላማ እየተከናወኑ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- ተሐድሶ መናፍቃን የኢትዮጵያ ኦርቶዶ ክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማቃ ለልና አስተምህሮዋን ለመንቀፍ ሲፈ ልጉ፡-
ከወንጌል ተልእኮ አንጻር ፋይዳ ያላቸው ባይሆኑም በርካታ የሥነ ጽሑፍ ውጤቶች በኢትዮጵያ ኦርቶዶ ክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተከማችተው ይገኛሉ፡፡ የብዙዎች ዐይን ያላያቸውና ተነበው ያላለቁ ድርሳና ቶቿም ብዙ ናቸው፡፡ ከግዝፈታቸው የተነሣ ለዐራት ተይዘው የሚከፈቱ የአንድ ሰው ትክሻ ስለማይችላቸው በአህያ የሚጫኑ መጻሕፍቶች አሉ፡፡ አሳዛኙ ነገር ግን ከእነዚህ ሁሉ መጻ ሕፍት ዘጠና በመቶ የሚሆኑቱ ክር ስቶስ ኢየሱስን በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ የመረዳት ነጻነት የሚያደ ርሱ አይደሉም፡፡ (ከሣቴ ብርሃን ጋዜጣ መጋቢት ፳፻ወ፮ ዓ.ም) በማለት ይጽ ፋሉ፡፡
ይህ አሳብ ቤተ ክርስቲያንን በኢየ ሱስ ክርስቶስ የማታምን አድርጎ ከማቅረብ ያለፈ በምዕራባውያን እየተቀነ ቀነ ያለውን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲ ያንን በጎ እሴት፣ መልካም ሥነ ምግባ ርና ሰብአዊነት ለመናድ ምሰሶዋን ለመነቅነቅ ታልሞ የተጻፈ ነው፡፡ መጻ ሕፍቱ ጥቅም ስለሌላቸው አታንብቧ ቸው የሚል መልእክት ማስተላለፍ፣ ምግባር ትሩፋት አያስፈልግም ብሎ መስበክ ሳያስፈልግ ሰዎች በተለያዩ ሱሶች (ፊልም፣ ሙዚቃ፣ እግር ኳስ፣ ጫት፣ ወዘተ) ተጠምደው ከሥራ ውጪ እዲሆኑ ማድረግ ይቻላል የሚል ዓላማ ይዘው ለተነሡ አካላት ድጋፍ መስጠት ነው፡፡ ይህ ደግሞ በቀጥታ ዓለማዊነ ትን ማበረታታት ነው፡፡
፪. ሥርዓት አልበኝነት፡- ዓለምን ሁሉ ለዓለማዊነት እያዘጋጁ ያሉት ምዕራባውያን በመጀመሪያ ደረጃ የሚ ሠሩት ሥራ ለዶግማ፣ ለሥርዓት፣ ለቀኖና፣ ለትውፊትና ለታሪክ ትኩረት በመስጠት ትውልድን የሚያገለግለውንና የሚያስተካክለውን ሃይማኖት ማጥ ፋት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት የተሐድሶ መናፍቃን ሰይፍ ያነጣጠረው ለዶግማ፣ ለሥርዓት፣ ለቀኖና፣ ለትውፊትና ለታ ሪክ ዋጋ በምትሰጠው ኦርቶዶክሳዊነት ቤተ ክርስቲያን ላይ ነው፡፡ ተሐድሶ መናፍቃን ማመን ብቻ በቂ ነው፤ ስለሚሉ ቤተ ክርስቲያን መሔድ፣ ቅዳሴ ማስቀደስ፣ ቅዱስ ቁርባን መቀ በል፣ መጾም መጸለይ፣ መስገድ፣ መመ ጽወት፣ ምግባር ትሩፋት መሥራት አያስፈልግም፤ ባይ ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ የክህነት ደረጃ፣ ለሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መታዘዝ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም፤ በማለት ሰው ሕይወቱን በሥርዓት አልበኝነት እንዲመራ ያበረታታሉ፡፡
በተሐድሶ መናፍቃንን በመንገድ ጠራጊነት በሚያገለግሏቸው ሚዲያ ዎች የሚተላለፉ “ትምህርቶች” ሥር ዓት አልበኝነትን የሚያሰፍኑ መሆናቸ ውን የሚከተለው አባባላቸው ማሳያ ነው፡፡
ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል፣ በአፉ መስክሮ ይድናልና፣ መንገዱ ረጅም አይደለም ወገኖቼ፤ ውጣ ውረድ የለበትም፡፡ የምትከፍለው አይደለም፣ የተከፈለበት ነው፡፡ አንተ የምታደር ገው ነገር አይደለም፣ የተደረገልህ ነው፡፡ የምትሆነው አይደለም፣ የሆነልህ ነው፡፡ ይህንን ብታምን በአፍህ ብት መሰክር ትድናለህ፡፡ የእግዚአብሔር ቃል የሚነግረን መዳን ማለት በልብ ማመ ንና በአፍ መመስከር እንጂ እኛ በድ ካም የለመድነውን አይደለም፡፡ እየታገ ልን አንዴ ሲሳካ አንዴ ሳይሳካ እያለ ቃቀስን የምንኖረውን አይደለም፡፡
ይህ ንግግር መዳን በእምነት ብቻ ብሎ የተነሣው የሉተር ትምህ ርት እንጂ የቤተ ክርስቲያን አስተም ህሮ አይደለም፡፡ የቤተ ክርስቲያን አስተ ምህሮ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው “በብዙ ድካምና በብዙ መከራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንገባ ዘንድ ይገባናል” የሚል ነው፡፡ ሥርዓት አልበኝነትን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለማስገባት ቆርጠው የተነሡት የተሐድሶ መናፍቃን ግን ኦርቶዶክሳዊነትን እን ዲህ ያቃልሉታል፡፡
“ጌታን የምናመልከው የሃይማኖት ድርጅት በመቀያየር አይደለም፡፡ ጴን ጤም መሆን ኦርቶዶክስም መሆን አያጸድቅም፡፡ ሕይወት እና ጽድቅ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን ብቻ ነው የሚገኘው። ጴንጤም ሆነ ኦርቶ ዶክስ መሆን ለእውነተኛ ወንጌል መረ ዳት ዋስትና አይደለም፡፡ ክርስቶስ በመ ጨረሻ ለፍርድ ሲመጣ ጴንጤ በዚህ፣ ኦርቶዶክስ በዚህ፣ ተሐድሶ በዚያ በኩል ብሎ አያሰልፍም፡፡ ሃይማኖት ማለት በእግዚአብሔር ልጅ አምኖ መመስከር ነው እንጂ ድርጅት መከተል አይደለም” በማለት ሃይማኖት አን ዲት ናት ያለውን የቅዱስ ጳውሎስን ቃል ሽረው፣ ብዙ መንገድ እንዳለ አድ ርገው አልፎ ተርፎም ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትን ድርጅት ብለው አቃለው ይናገራሉ፡፡
የዚህ ሁሉ ዓላማ ሥርዓት አልበ ኝነት የነገሠበት ግላዊ ሕይወትን በም እመናን ላይ ለማንበር ነው፡፡ የጥ ፋት አባቶቻቸው ምዕራባውያን የሰው ልጆች የእግዚአብሔር አጋዥነት ሳያስ ፈልጋቸው ሓለፊነት ያለው “ሞራ ላዊ” ሕይወት በመምራት ለሰው ልጆች ፍጹም ጥቅምና ደህንነት የመብቃት ዐቅምና ሓላፊነት አላቸው፡፡ በምክንያታዊነት በመመራት፣ ጥልቅ በመሆነ መረዳትና በተግባራዊ የሕይወት ልምምድ ሕይወትን ፍጹምና ደስታ የሞላበት ለማድረግ ይችላሉ፡፡ ይህም አስተሳሰብ በየጊዜው በዝግመተ ለውጥ እያደገ የሚሔድ ነው፡፡ አስተሳሰቡ በእሴቶች መሠረት በሚቀመጡ ግቦች እንዲመራ በሚያደርጉ አስተዋይ ሰዎች መሪነት በጥንቃቄ ቅርፅ እያገኘና ከዕውቀታችን ማደግ ጋር እየተለወጠ የሚሔድ ነው፡፡ እሳቤውም እንደ ሰው ልጅ ሕይወት ያላማቋረጥ የሚሻሻ ልና የሚዘምን ነው፤ በማለት ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም የሚለ ውን የጌታ ቃል ለማፍረስ ይሠራሉ (ምንጭ፣ የ፲፱፻፺፫ /እ.ኤ.አ/ የሰብአ ዊነት መግለጫ) በማለት ጽፈዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ የሚ ለው “ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አት ችሉም” ነው፡፡ ሁሉ በእርሱ ሆነ፤ ከሆነ ውስ አንዳች እንኳን ያለ እርሱ የሆነ የለም፡፡ ምድርና ሞላዋ በእግዚአብሔር ተፈጠሩ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ይህን ወይም ያን እናደርጋለን በሉ፡፡ ሁሉ የእርሱ፣ በእርሱ፣ ለእርሱ የሆነ አም ላክ የተመሰገነ ይሁን፤ የሚል ነው፡፡ የመልእክቱ አስተላላፊዎች እነዚህን ጥቅሶች ውሸት ለማድረግ የሚሠሩ መሆናቸውን ድርጊታቸው ይመሰክ ራል፡፡
፫. አክራሪነት፡- አክራሪነት ማለት ከእኔ የተለየ አስተሳሰብ ያለው አካል በምድር ላይ ሊኖር አይገባም የሚል ጽንፈኝነት ነው፡፡ ምዕራባውያን አክራሪነ ትን በመዋጋት ስም እያስፋፉ የሚገ ኙት አክራሪነትን ነው፡፡ ልዩነቱ ምዕራ ባውያን አክራሪነትን የሚያስፋፉበት መንገድ እስልምናን ሽፋን አድር ገው አክራሪነትን እንደሚያራምዱ ወገ ኖች በጦር መሣሪያ ሳይሆን በኢኮ ኖሚ፣ በትምህርት፣ በሥልጠና፣ በል ማት፣ በባህልና ሃይማኖት ተሐድሶ፣ በሰብአዊ መብት ማስከበር፣ አክራሪነ ትን በመከላከል፣ ወዘተ ሽፋን መሆኑ ነው፡፡ ምዕራባውያን በዓለም ላይ ፕሮቴ ስታንት ብቸኛ እምነት እንዲሆን፣ ምዕራባዊ ባህልና አስተሳሰብ በዓ ለም ሁሉ እንዲንሰራፋ፣ “በነጻነት” ስም የሚሰበከው ዓለማዊነት እንዲስፋፋ፣ ወዘተ እየሠሩ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ተግ ባራት የመጨረሻ ዓላማቸው የሌሎ ችን አገራት እምነት፣ እሴት፣ አስተ ሳሰብ፣ ባህል፣ ወግ፣ ወዘተ በማፍረስ በፕሮቴስታንታዊ ባህል ለመተካት ከተቻለ ደግሞ ፈጽሞ ዓለማዊ ለማድ ረግ ነው፡፡
በዓለም ላይ ማንነታቸውን እንዲ ያጡ፣ ያላቸው የተፈጥሮ ሀብት በሌ ሎች እንዲወሰድባቸው የተደረጉ አገ ራት ዜጎች አሸባሪዎች ሆነዋል፡፡ አሸባ ሪዎች የሆኑት ግን ተፈጥሯቸው ለሽብር የሚስማማ ሆኖ ወይም አሸባ ሪነትን መርጠውት ሳይሆን አማራጭ ስለሌላቸው ነው፡፡ ጆን ፐርኪንስ በኢኳ ዶር የሆነውን ጠቅሶ ሲናገር እንዲህ ነበር ያለው፡-
â€Â¦ ነዳጅ ለማውጣት ሲባል ከቦ ታቸው ለተፈናቀሉትና ጫካቸው ተመን ጥሮ አካባቢያቸው ወድሞ በእጅጉ ለተጎዱት፣ ገንዘቡም ለዕለት ኑሯቸው እጅግ አስፈላጊያቸው ለሆነውና የሚበላ ምግብና የሚጠጣ ውኃ በማጣት ለሚሰቃዩት ነዋሪዎች የሚደርሳቸው ከአገሪቱ ከሚወጣው ነዳጅ ሽያጭ ከእያንዳንዱ መቶ ዶላር ውስጥ ከ2.5 ዶላር በታች ነው፡፡ እነዚህ ሕዝቦች በሙሉ – በኢኳዶር ያሉ ሚሊዮኖች እና በዓለም ዙሪያ ያሉ ቢሊዮኖች አንድ ቀን አሸባሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እንዲህ የሚሆኑት ግን በኮሚዩኒዝም ወይም በነውጠኛነት ስለሚያምኑ አይደ ለም፤ ወይም በተፈጥሯቸው ክፉዎች ስለሆነ አይደለም፤ የእኛ ድርጊት ተስፋ ስላስቆረጣቸው ብቻ ነው እንጂ፡፡ (የተሐ ድሶ መናፍቃን ዘመቻ ገጽ ፳፫)
የካቶሊክና የፕሮቴስታንት ሚሲዮ ናውያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ በእነርሱ ቋንቋ “ለማደስ” ብዙ ጊዜ ተመላልሰ ዋል፡፡ በዚህ ምልልሳቸው የመጨረሻ ግባቸው ተሳክቶ ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ፕሮቴስታንት ማድረግ ባይች ሉም ብዙ የፕሮቴስታንት ችርቾችን አቋቁመዋል፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመና ንን ዘርፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም የሚፈልጉት ልክ በምዕራቡ ዓለም እንዳደረጉት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስ ቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ትውፊት፣ ታሪክና ሥርዓት በማጥፋት ወጥ የሆነ ፕሮቴስታንታዊ አስተሳሰብን ማንበር ነው፡፡ ይህ በእነርሱ ቋንቋ “ሰዎች እጃቸውን ለጌታ እንዲሰጡ ማድረግ ነው” እየተደረገ ያለው ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ማንነት ማጥፋት ነው፡፡
ከዚህ በላይ አክራሪነት፣ አክራሪነ ትንም የሚያስፋፋ ተግባር የለም፡፡ ማንም ሰው የፈለገውን እምነት የመከ ተል፣ የፈለገውን አስተሳሰብ የመያዝ መብት አለው፡፡ ይህ ለሁሉም በሥነ ፍጥረት የታደለ መብት ነው፡፡ በተሐድሶ መናፍቃን ዘንድ ግን ይህ አይሠራም፡፡ የእምነቱ ተከታዮች ሳይሆኑ “ኦርቶዶክ ሳውያን ነን” በማለት ምእመናንን ከቤተ ክርስቲያን እያስወጡ ለሌሎች ቤተ እምነቶች ይገብራሉ፡፡ በገንዘብ በማታ ለል፣ በትውውቅ በመቀራረብ አልፎ ተርፎም በጉልበት በማስፈራራት ጭምር ምእመናንን ከበረታቸው የማስወጣት ሰፊ ዕቅድ ይዘው ይሠራሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቁጭ ብለው ቤተ ክርስቲያንን ይሳደባሉ፤ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትን የሚከተሉ ምእ መናንን ደግሞ ደንቆሮ፣ ያልበራላቸው፣ ኋላ ቀር፣ ጣዖት አምላኪ፣ ግብዝ፣ ወዘተ በማለት ሰው የፈለገውን እምነት የመከተል ሰብአዊ መብቱን ይጋፋሉ፡፡ እንግዲህ ከሰው ቤት ገብቶ አዛዥና ናዛዥ ለመሆን ከመፈለግ እና አልወ ጣም ብሎ ከመሟገት በላይ፣ “ኦርቶዶ ክሳዊ ነኝ” የሚል ጭንብል ለብሰው የማያምኑበትን እምነት ከመሳደብ በላይ፣ የራስን እውነት ከመናገር አልፎ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ትክክል አይደለችም እያሉ ከመሳደብ በላይ አክ ራሪነት ምንድን ነው?
፬. ግብረ ሰዶማዊነት፡- ግብረ ሰዶ ማዊነት ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ የሆነ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ነው፡፡ እግዚ አብሔር በዚህ ዐመጽ ውስጥ የነበሩ የሰዶምንና የገሞራን ሕዝቦች በእሳት ዲን አጥፍቷቸዋል፡፡ እግዚአብሔርን ከሚያስቆጡ የሥጋ ሥራዎች ውስጥ አንዱ ግብረ ሰዶም ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕራፍ ፩፣፳፬-፳፰ “â€Â¦ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸ ውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው” በማለት ግብረ ሰዶማዊ ነት ትልቅ ኀጢአት መሆኑን ነግሮናል፡፡ “ለባሕርያቸው የማይገባውን” የሚለው ግብረ ሰዶማዊነት የተፈጥሮን ሥርዐት የሚቃረን፣ የርኩሰት ሥራ፣ ጸያፍ፣ ሥጋን የሚያዋርድ፣ እግዚአብሔርን የሚያስቆጣና ቅጣትን የሚያስከትል መሆኑን ያስረዳናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ግብረ ሰዶማዊነት ከእግዚአብሔር መን ግሥት የሚያስወጣ መጥፎ ድርጊት መሆኑንም እንዲህ በማለት ነግሮ ናል፡፡ “ዐመጸኞች የእግዚአብሔርን መን ግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ፤ ሴሰኞች ቢሆን ወይም ጣዖ ትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝ ሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ â€Â¦ የእግዚአብ ሔርን መንግሥት አይወርሱም” (፩ኛ ቆሮ. ፮፣፱)፡፡
አማናዊውና ተፈጥሯዊው ትምህ ርት ይህ ሆኖ ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላትን እንደ ነጻነት የሚቆጥ ሩት ምዕራባውያን ግብረ ሰዶማዊ ነት በሰብአዊ መብት፣ በፍቅር፣ ወዘተ ስም ሕጋዊ እንዲሆን እየጣሩ ነው፡፡ በዓለም ታዋቂ የሚባሉ ሰዎችም ግብረ ሰዶማዊነትን አስመልክቶ በበጎ ጎን ጽፈዋል፡፡ ለምሳሌ፡- ሲግመንድ ፍሮ ይድ የሚባል የሥነ ልቡና ባለሙያ፡-
ግብረ ሰዶምን እንደ ወንጀል መቁ ጠር ትልቅ ኢፍትሐዊነት ነው፡፡ በጥን ቱም ሆነ በዘመናዊ ዓለም በጣም የሚ ከበሩ ግለሰቦች (ለምሳሌ፡- ፕላቶ፣ ሚካ ኤል አንጀሎ፣ ሊኦናርዶ ዳቪንቺ፣ ወዘተ) ግብረ ሰዶማውያን ነበሩ፡፡ ግብረ ሰዶም ጥቅም የለውም፤ ነገር ግን የሚ ያሳፍር፣ የሚያስጠላ፣ የሚያስቀጣና እንደ በሽታ የሚቆጠር ነገር ሳይሆን እንደ አንድ አማራጭ የሥራ ዘርፍ መታየት አለበት፤ ብሏል፡፡
ካረን ሁከር የምትባል ሴት በጥናት ደረስኩበት የምትለውን “ግብረ ሰዶማው ያን በሕይወታቸው የሥነ ልቡና ቀውስ አልደረሰ ባቸውም፡፡ ስለዚህ ግብረ ሰዶምና ሥነ ልቡናዊ ቀውስ ቀጥተኛ ግንኙነት የላቸውም” ብላ በመገለጽ ግብረ ሰዶማዊነትን ተፈጥ ሯዊ ለማስመሰል ሞክራለች፡፡ ሐቭሎክ ኢሊስ ደግሞ “አብዛኞቹ ግብረ ሰዶ ማውያን ለሚኖሩበት ማኅበረሰብ ከፍ ተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል”፤ ይላል፡፡ እነዚህ ሁሉ አስተሳሰቦች የእግዚአብ ሔርን መኖር በማያምኑ ወይም በሚጠ ራጠሩ አካላት የሚቀነቀኑ ስለሆነ ብዙ ላያስገርሙን ይችላሉ፡፡ የሚያሳዝነው ግን እግዚአብሔርን እናውቃለን፤ “ክርስ ቶስን እንሰብካለን” በሚሉ አካላት እነ ዚህ አስተሳሰቦች ትክክል ናቸው ተብ ለው መወሰዳቸው ነው፡፡
አብዛኛዎቹ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ግብረሰዶማዊነትን የሚደግፉ ናቸው፡፡ ስፔን፣ ጀርመን፣ ቼክ ሪፐብ ሊክ፣ ፈረንሣይ፣ እንግሊዝ፣ ኢጣሊያ፣ ግሪክ፣ ፖላንድ የመሳሰሉ አገራት ግብረ ሰዶማዊነትን የሚደግፉ ናቸው፡፡ በሌላው ዓለም ስናይ አሜሪካ፣ አርጀን ቲና፣ ቺሊ፣ ሜክሲኮ፣ ብራዚል፣ ቬንዙ ዌላ፣ አውስትራሊያ፣ ፊሊፒንስና ጃፓን ደጋፊ አገራት ናቸው፡፡ ግብረ ሰዶማ ዊነትን በሕግ ከፈቀዱ አገራት መካከል ደግሞ፡- አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላ ንድ፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ፣ ካናዳ፣ ቤልጂ የም፣ አውስትራሊያና ደቡብ አፍሪካ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ግብረ ሰዶማዊነትን በመቃወም ኢትዮጵያ ከናይጀሪያ ቀጥሎ ሁለተኛ ናት፡፡
በእነዚህ አገራት የሚገኙ እና ወን ጌልን እንስበክላችሁ የሚሉን የካቶሊ ክና የፕሮቴስታንት ቸርቾች ግብረ ሰዶማዊነት የሰውን ልጅ የሚያጠፋ መሆኑን የሚናገረውን የቅዱስ ጳውሎ ስን መልእክት እያስተማሩ ግብረ ሰዶ ማዊነትን በዐዋጅ ተቀብለዋል፡፡ በክር ስትና ስም የሚጠሩ “አብያተ ክርስቲ ያናት” የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ኀጢአት ወይም የሥነ ምግባር ግድ ፈት አድርገው አያዩትም፡፡ እንዲያ ውም ግንኙነቱን በመባረክ እንደ ጋብቻ እየቆጠሩት ነው፡፡ ግብረ ሰዶማዊነትን ፈቅደው በቸርቾቻቸው ወንድን ከወ ንድ፣ ሴትን ከሴት እያጋቡ ነው፡፡ ወን ጌል ገልጠው እያስተማሩ፣ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ነን እያሉ ግብረ ሰዶ ማውያንን በመቅደሳቸው አቁመው የሚያጋቡ የእምነት ድርጅቶች ስለ መኖራቸው ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ለም ሳሌ፡- ፈረንሳይ ውስጥ የሚገኙ የፕሮ ቴስታንት “አብያተ ክርስቲያናት” ጠቅ ላይ ሲኖዶስ ግብረ ሰዶማውያን ጋብ ቻቸውን “በቤተ ክርስቲያን” ውስጥ እንዲፈጽሙ ፺፬ በመቶ በሆነ ድምፅ አሳልፏል፡፡
“የአብያተ ክርስቲያናቱ” መሪ ሲኖዶሳቸው ወደፊት እያንዳንዳንዱ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ይህን የግብረ ሰዶማውያን ጋብቻ በማጽደቅ ፍላጎታ ቸው ከሆነ ባርኮ ለማጋባት መንገዱ ተከፍቷል ብለዋል፡፡ የስኮትላንድ ሉተ ራን “ቤተ ክርስቲያን” ደግሞ ተመሳ ሳይ ጾታ ካላቸው ተጋቢዎች መካከል ዲያቆናትንና ካህናትን መሾም የሚቻል በትን ሕግ አጽድቃለች፡፡ በስዊድን የሚገ ኘው የፕሮቴስታንት “አብያተ ክርስቲ ያናት ሲኖዶስ” የግብረ ሰዶማውያንን ጋብቻ ለመባረክ በ፳፻፲፪ ውሳኔ ሲያስተላ ልፍ፣ የዴንማርክ “ሲኖዶስ” በበኩሉ እያንዳንዱ የፕሮቴስታንት “ቤተ ክርስቲ ያን” ይህን ጋብቻ መፈጸም ግዴታው እንደሆነ በመግለጽ ውሳኔውን በሥሩ ላሉ “አብያተ ክርስቲያናት” አስተላ ልፏል፡፡ የኖርዌይ ፕሮቴስታንት “ቤተ ክርስቲያንም” ከዴንማርክ ቀጥሎ ተመሳ ሳይ ውሳኔ አስተላልፋለች፡፡
በአጠቃላይ የካናዳ የተባበሩት “ቤተ ክርስቲያን” (the United Church of Canada)፣ የክርስቶስ የተባበሩት “ቤተ ክርስቲያን” (The United Church of Christ)፣ የጀርመን ሉተራን “አብ ያተ ክርስቲያናት” (all German Lutheran)፣ የኢኬዲ ተሐድሶና የተባ በሩት “አብያተ ክርስቲያናት” (refor med and united churches in EKD)፣ የስዊዘርላንድ ተሐድሶ “አብያተ ክርስቲያናት” (all Swiss reform ed churches)፣ የኔዘርላንድ ፕሮቴ ስታንት “ቤተ ክርስቲያን” (the Protestant Church in the Netherlands)፣ የቤልጂየም የተባበሩት ፕሮ ቴስታንት “ቤተ ክርስቲያን” (the Uni ted Protestant Church in Belgium)፣ የፈረንሣይ የተባበሩት ፕሮቴስታንት “ቤተ ክርስቲያን” (the Unit ed Protestant Church of France)፣ የዴንማርክ “ቤተ ክርስ ቲ,ያን” (the Church of Denmark)፣ የስዊድን “ቤተ ክር ስቲያን” (the Church of Sweden)፣ የአይስላንድ “ቤተ ክርስቲ ያን” (The Church of Iceland)፣ የኖርዌይ “ቤተ ክርስቲያን” (the Church of Norway)፣ የፊንላንድ ወንጌላ ዊት ሉተራን “ቤተ ክርስቲያን” (The Eva ngelical Lutheran Church of Finland)፣ የሜትሮፖሊታን ኅብረት “ቤተ ክር ስቲያን” (The Metropolitan Community Church)፣ የሐዋርያት ጴንጤ ቆስታል አጋዥ ዓለም አቀፋዊ ኅብ ረት (The Global Alliance of Affirming Apostolic Pentecostals (GAAAP)) ግብረ ሰዶማዊ ነትን ያጸደቁና ግብረ ሰዶማውያንን በጸሎት የሚያጋቡ “አብያተ ክርስቲ ያናት” ናቸው፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለወንድም ለሴትም ግብረ ሰዶማውያን ክህነት የሰጡ “አብያተ ክርስቲያናት” ደግሞ፡- የስኮትላንድ፣ የእንግሊዝ፣ የዌልስ፣ የስዊድን፣ የኖርዌይ፣ የዴንማርክና የአይስላንድ “አብያተ ክርስቲያናት”፣ የፊንላንድ ወንጌላዊት ሉተራን “ቤተ ክርስቲያን”፣ የጀርመን ወንጌላዊት ሉተ ራን “ቤተ ክርስቲያን”፣ የኔዘርላንድ ፕሮቴስታንት “ቤተ ክርስቲያን”፣ የቤል ጂየም የተባበሩት ፕሮቴስታንት “ቤተ ክርስቲያን”፣ የስዊዘርላንድ ተሐድሶ “ቤተ ክርስቲያን”፣ የፈረንሣይ የተባ በሩት ፕሮቴስታንት “ቤተ ክርስቲ ያን”፣ የካናዳ ወንጌላዊት ሉተራን “ቤተ ክርስቲያን”፣ የካናዳ አንግሊካን ቤተ ክርስቲያን፣ የጥንቷ ካቶሊክ “ቤተ ክርስቲያን” እና የጃፓን የተባበሩት የክርስቶስ “ቤተ ክርስቲያን” ናቸው፡፡
፭. አምልኮተ ሰይጣን፡- ምዕራባው ያን የሥልጣኔያቸው የመጨረሻ ጥግ “አምልኮተ ሰይጣን” ሆኗል፡፡ በተለያዩ አገራት የሚገኙ በተለይም በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በመላው ዓለም የሚታዩት ሙዚቀኞች፣ የእግር ኳስ ተጨዋቾች፣ ሞዴሊስቶች፣ የፊልም ተዋናዮች፣ ወዘተ ሰይጣንን ወደ ማም ለክ ደረጃ ደርሰዋል፡፡ እነዚህ አገራት ግን “የአፍሪካውያንን ዐይን ለማብራት በሚል” ብዙ ሚሲዮኖችን ወደ አፍሪካ ይልካሉ፡፡ አበው የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች እንዲሉ የራሳቸው ዜጎች በነጻነት፣ በዲሞክራሲያና ሰብአዊ መብት፣ በሥልጣኔ፣ በልማት፣ ወዘተ ስም ከአምልኮተ እግዚአብሔር ወጥ ተው ወደ አምልኮተ ሰይጣን እየገቡ፣ የእምነቱ ተከታይ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን መድረክ ላይ ቆመው የክርስቶስን ወን ጌል ገልጠው የሚያስተምሩ ፓስተሮ ቻቸው በአምልኮተ ሰይጣን እየታሙ በአርአያቸውና በአምሳላቸው የፈጠ ሯቸው ተሐድሶ መናፍቃን ለእኛ “ወንጌል ካልሰበክን” ይላሉ፡፡
የተሐድሶ መናፍቃን የመጨረሻ ግባቸው ይህ ነው፡፡ ምክንያቱም ገለጻ ሲያደርጉ በአምኮተ ሰይጣን የሚታ ሙትን ጆሹዋንና ፓስተር ክሪስን እንደ አርአያ ይጠቅሷቸዋልና፡፡ መጽ ሐፍ ቅዱስ የሚያዝዘው “የእግዚአ ብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻች ሁን አስቡ፣ የኑሯቸውንም ፍሬ እየ ተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው” በማለት ነው፡፡ የተሐድሶ መናፍቃን ዋኖቻችን ብለው የሚጠሯቸው ግን ምግባር የሌላቸው ብቻ ሳይሆኑ በእግ ዚአብሔር ማመናቸው እንኳን የማይ ታወቁ ሰዎችን ጭምር ነው፡፡ ጆሹዋና ፓስተር ክሪስ ርኩሳን መናፍስትን በመጥራት አጋንንትን እናወጣለን የሚሉ እንደሆኑ ብዙ ማስረጃዎች እየ ወጡ ነው፡፡ ስለዚህ የተሐድሶ መናፍ ቃን የመጨረሻ ግብ ዓለማዊነትን አልፎ ሰው በዘቀጠ የሕይወት ማንነት ውስጥ እንዲኖር የሚያደርጉ እኩይ ተግባራትን በውስጡ በማንገሥ ግብረ ሰዶማዊና ሰይጣን አምላኪ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡

መንክር ስብሐተ ልደቱ፤ የመወለዱ ምሥጢር ድንቅ ነው

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}ledete2004{/gallery}

«እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሴትን እናድርግ፤ በእርስዋም ደስ ይበለን፡፡» መዝ. 117·24 ይህች ዕለት ዕለተ ኃይል፣ ዕለተ አድኅኖ፣ ዕለተ ብሥራት፣ ዕለተ ቅዳሴ፣ ዕለተ ልደት፣ ዕለተ አስተርዕዮ ናትና ዓለም ሳይፈጠር አስቀድሞ ከአብ ባሕርይ ዘእምባሕርይ፣ አካል ዘእምአካል፣ የተወለደ ወልድ ዋሕድ ኋላም ከድንግል አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ በዚህች ዕለት በኅቱም ድንግልና ተወልዷልና ዕለተ ኃይል ትባላለች፡፡ መላእክት በጎል ተጥሎ፣ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተው ስብሐት ለእግዚአብሔር ብለው አመስግነውበታልና ዕለተ ቅዳሴ፣ መድኅነ ዓለም ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን በጎል ተገኝቶበታልና ዕለተ አድኅኖ፣ ቅዱስ ገብርኤል እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ብሎ ተናግሯባታልና ዕለተ ብሥራት ትባላለች፡፡ «እግዚአብሔርም አለኝ አንተ ልጄ ነህ እኔም ዛሬ ወለድሁህ» መዝ 2·7 በተዋሕዶ፣ በቃል ርስትነት ተብሎ የተነገረለት ቀድሞ ብቻውን እግዚአብሔር ከብቻው እግዚአብሔር እንደተወለደ፣ በኋለኛውም ዘመን ብቻውን የሚሆን የእግዚአብሔር ልጅ ብቻዋን ከምትሆን ከዳዊት ልጅ ተወለደ፡፡

በመጀመሪያ የማይታይ እሱ ከማይታየው ተወለደ፤ በኋላም የማይያዝ የሕይወት እስትንፋስ ከምትዳሰስ ሥጋ ተወለደ፡፡
በመጀመያ የአኗኗሩ መጀመሪያ ሳይታወቅ ተወለደ፤ በኋላም የዘመናት ፈጣሪ ዓመታትን የሚወስን እርሱ ዕድሜዋ ዐሥራ አምስት ከሆነ ከታናሽ ብላቴና ተወለደ፡፡
የመጀመሪያ ልደቱን ምሥጢር፣ የኋለኛ ልደቱንም ድንቅ በማድረግ ተወለደ፡፡
በቅድምና የነበረው የአብ አካላዊ ቃሉ በምልዓት ሳለ ተፀነሰ፤ በጌትነቱ በጽርሐ አርያም ሳለ ሰው ሆነ፤ ማኅተመ ድንግልናን ሳይለውጥ የእኛን ባሕርይ ተዋሕዶ ተወለደ፡፡
የሰውን ልጅ በጥንተ ተፈጥሮ የፈጠረ የእግዚአብሔር አብ ልጅ እግዚአብሔር ወልድ አሁን ደግሞ በሐዲስ ተፈጥሮ ለመፍጠር ሰው ሆኖ ተወለደ፡፡ «ሰው ሆይ አስተውል እሱን አስመስሎ ይወልድህ ዘንድ አንተን መስሎ ተወለደ ስለዚህ ነገር ቅዱስ ጳውሎስ መላእክትን የተቀበለ አይደለም፤ የአብርሃምን ዘር ከፍ ከፍ አደረገ እንጂ» እንዳለ ዕብ 2·16 የሰውን ልጅ ክብር ወደ ቀደመ ማንነቱ ለመመለስ እንዲህ ባለ ድንቅ ልደት ዛሬ ተወልዷልና ዕለተ ልደት ትባላለች፡፡
«በሀገራቸው ትንቢት የተነገረላቸው በዕብራይስጥ ልሳንም የተጻፈላቸው እስራኤል ምንም ባያውቁህ ከዓለም አስቀድሞ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንህ ደግሞ ከዳዊት ዘር ከምትሆን ቅድስት ድንግል ተወልደህ የሰው ልጅ መባልህን አወቅሁ» ማቴ 16·13-18
ትንቢቱስ ምን ነበር እግዚአብሔር፤ አዳምን ከአራቱ ባሕርያት ፈጥሮ ከእንስሳት ከአራዊት ለይቶ በነባቢት ነፍስ አክብሮ ልጅነትን ሰጥቶ ሥራ ሠርቶ ሊጠቀምበት መንፈሳዊ ዕውቀትን አድሎ በአርአያው በአምሳሉ የፈጠረው ነውና የባሕርዩን በጸጋ ሰጥቶ የሁሉ ገዥ አድርጎ በገነት ሹሞ አኖረው፡፡ ነገር ግን የገዥና የተገዥ ምልክት የምትሆን ዕፀ በለስን እንዳይበላ አዘዘው፡፡ ይኸውም የንፍገት አይደለም፤ ከሹመቱ እንዳይሻር፣ ከልዕልናው እንዳይዋረድ፣ ከልጅነት እንዳይወጣ፣ ክብርን እንዳያጣ ነው እንጂ፡፡ ሆኖም ግን የራሱን ክብር ልዕልና በራሱ ያጣ ዲያብሎስ በአዳም ክብርና ልዕልና ቀና፡፡ በሥጋ ከይሲ ተሠውሮ በሽንገላ መጣ፡፡ ክፋትን በተመላ ደስ የሚያሰኝ በሚመስል አነጋገር የሞት ሞት የምትሞቱ አይምሰላችሁ የዕፀ በለስ ፍሬ ብትበሉ የአምላክነት ዕውቀት ይሰጣችኋል፡፡ ክፉውንም ደጉንም ታውቃላችሁ፤ አሁን ካላችሁበት ክብርና መዓርግ ከፍ ትላላችሁ በማለት አታለላቸው፡፡ እነርሱም እውነት መሰላቸው፡፡ ከፈጣሪያቸው ትእዛዝ ወጡ፡፡ ራሳቸውን አጥፊ ሆኑ፤ የቀደመ ማንነታቸውን አጥተው ኃሣር፣ መርገም፣ ድንጋፄ፣ ረዓድ ወደሚበዛበት፣ ክፉና መልካም ወደሚሠራበት፣ ቢያገኙት ቁንጣን፣ ቢያጡት ቀጠና ወደ ሆነበት ዓለም ወረዱ፡፡ ቢሆንም ግን አዳም በፍታዊነቱ አንጻር መሐሪነቱን ተረድቶ በደሉን በማመን አዘነ፤ አለቀሰ፤ በልብ መታሰቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ይበልና ጸዋትወ መከራውን አይቶ አዘነለት፡፡ የሚድንበትን ተስፋ ትንቢት ሰጠው፡፡ አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ ከዚህም አያይዞ ከልጅ ልጁ ተወልዶ የሚያድነው ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል መሆኑን፣ እርሱን ለማዳን ስሙን ባሕርዩን ገንዘብ የሚያደርገው ወልድ ኢሳ 9·6 መሆኑንም ጨምሮ ነግሮታል፡፡ ዘፍ 3·22 ይህ የሚፈጸምበትን ቀጠሮም አስረድቶታል፡፡ ገላ 4·4 ከዚያ ቀጥሎ በየጊዜው ለተነሡ ልጆቹ ትንቢቱን በማስነገር፣ ምሳሌውን በማስመሰል፣ እስከ ጊዜው ደርሷል፡፡ ለዚህም ነው በዘመነ አበው የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ ተብሎ የሃይማኖት መሠረት ለሆነው ለአብርሃም የተነገረው ዘፍ 22·18
በዘመነ መሳፍንትም አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ መካከል ከወንድሞችህ እንደኔ ያለ ነቢይ ያስነሣልሃል፤ እርሱንም ታደምጣለህ ተብሎ በሙሴ ለእስራኤል ሕዝብ በሙሉ አዋጅ ታውጇል፡፡ ዘዳግ 18·15
በዘመነ ነገሥት ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ ብሎ ለዳዊት የገባው ልዩ ቃል ኪዳን አለ፡፡
ስለዚህ እወቅ አስተውልም ኢየሩሳሌምን መጠገንና መሥራት ትእዛዙ ከሚወጣበት ጀምሮ እስከ አለቃው እስከ መሢሕ ድረስ ተብሎ በነቢዩ ዳንኤል 9·25 ተነግሯል፡፡
ያዕቆብም በምርቃት የገለጸው ልጆቹን ለእያንዳንዳቸው እንደሚገባቸው የጸጋ ሀብት በረከታቸውን ባሳየ ጊዜ የይሁዳን መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም፤ ግዛትም ከወገኑ ገዥ የሆነው እስኪመጣ ድረስ እርሱም የአሕዛብ ተስፋቸው ነው፡፡ ዘፍ 49·10 ከይሁዳ ወደ ዳዊት እየቀረበ ሲመጣም እርሱም አባቴ አንተ ነህ ይለኛል እኔም በኩር አደርገዋለሁ፡፡ መዝ 88·20 1ሳሙ 16·1-13 በማለት ሥጋ (አካለ) ዳዊትን በተለየ መልኩ እንደመረጠው ፈጣሪው ሲሆን ልጁ ለመባል እንደወደደ እየገለጠው እያቀረበው መጣና ወደ ልጁ አለፈ፡፡
ዳዊትንም ልጁን ለዚህ ታላቅ ምሥጢር እንዲያዘጋጅ በትንቢት አነሣሣው፡፡ እርሱም ልጁን እንዲህ አላት፤ «ልጄ ሆይ የምልሽን ስሚ፤ እይ፤ ጆሮሽንም ወደ ምሥጢሩ ቃል አዘንብይ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ያለምንም የልብ መከፈል ራስሽን ለርሱ ስጪ፤ ንጉሥ ውበትሽን ይኸውም ንጽሕናሽን፣ መዓዛሽን፣ ቅድስናሽን ወዷልና፡፡ እርሱ ሌላ አይደለም፤ ለታላቁ ምሥጢር የመረጠሽ ጌታሽ ነውና፡፡» መዝ 44·10-12 አላት፡፡ ደስ በሚያሰኝ የተስፋ ቃል ትንቢቱን ተናገረ፡፡ እርሱም ይሁንልኝ ብላ የአባቷን ምክር ተቀብላ የአምላክ እናት ለመሆን በቃች፤ ትንቢቱም ደርሶ የገባውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ ወደደ፡፡
ደም ግባቷን በወደደ ጊዜም በጽርሐ አርያም እናት ትሆነው ዘንድ ወደ ሰማይ አላሳረጋትም፤ እርሱ ራሱ ወደእርሷ ወረደ እንጂ፡፡ በዚያ ትፀንሰው ዘንድ በኪሩቤል ሠረገላ ላይ አላስቀምጣትም፤ ናዝሬት በተባለች በገሊላ ሀገር ሳለች እርሱ ራሱ በማሕፀኗ አደረ እንጂ፡፡ ገብርኤልንም ዘጠኝ ወር በማሕፀኗ እንድትሸከመኝ ወደዚህ አምጣት አላለም፤ እርሱ ራሱ ትሕትናዋን ተሳተፈ እንጂ፡፡ ይልቁንም መልክተኛውን በትንቢት ወደ መረጣት የዳዊት ልጅ ላከ፡፡ እርሱም ደስ ያለሽ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው፤ እነሆ ኢሳይያስ ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች እንዳለ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ፤ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከሥጋችን ሥጋን፣ ከነፍሳችን ነፍስ ነስቶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆነ፤ በተዋሕዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ የሆነውም ኢየሱስ ተባለ፤ ትርጓሜውም ወገኖቹን የሚያድናቸው ማለት ነው፡፡ ይህ እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ የሆነ ሳይሆን ከጥንቱ ሲነገር ሲያያዝ የመጣ ነው አላት፡፡ እርሷም እንዲህ ያለ ሰላምታ እንደምን ይቀበሏል አለች፡፡ በትሕትና መልአኩም በእግዚአብሔር ዘንድ የእናትነት ባለሟልነትን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ፤ የምትወልጅውም የልዑል እግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ይባላል፤ እግዚአብሔር የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ወገን ለዘለዓለም ነግሦ ይኖራል፡፡ ለጌትነቱ ፍጻሜ የለውም አላት፡፡ ነገሩስ መልካም ነበር፤ ነገር ግን ወንድ ሳላውቅ መፅነስ መውለድ እንደምን ይሆንልኛል? በውኑ ምድር ያለ ዘር ታፈራ ዘንድ ሴት ያለወንድ ትፀንስ ዘንድ ይቻላልን? ሴት ያለ ወንድ ዘር መውለድ ከዚህ በፊት አልሆነምና አለችው፡፡
እውነት ነው ከዚህ በኋላም አይሆንም ነገር ግን ያንች ፅንስ እንደ ሌሎች ፅንስ አይደለም፤ መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል፤ ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ይዋሓዳል፤ ለሱ የሚሳነው ነገር የለም፤ ሁሉን ማድረግ ይቻለዋል አላት፤ እርሷም ጊዜ በፍጹም እምነት ቃለ ብሥራቱን ተቀብላ አቤቱ እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋዩ ነኝ እንደ ቃልህ ይደረግልኝ ባለች ጊዜ ፈቃዷን ምክንያት አድርጎ የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት የሚሆን ዋሕድ ቃለ እግዚአብሔር በማሕፀኗ ተቀርፆ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የማይወስነው በማሕፀኗ ተወስኖ ሊወለድ የማይቻለው ተወለደ፡፡ በሰው ዘር ያልሆነ ነገር ግን እንደ ሰው የሆነውን ልደቱን እናምናለን፡፡
አምላክ ሲሆን መወለዱን፣ ወደዚህ ዓለም መምጣቱን፣ ከረቂቃን የረቀቀ ድንቅ ነው ከድንግል መወለዱ ፍጹም ሰው ቢሆንም ያለ ዘር በኅቱም ድንግልና ተጸንሶ በኅቱም ድንግልና መወለዱ ግን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በመሆኑ ፍጹም አምላክ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ይህ ልደት እጅግ አስደናቂ ልደት ነው፡፡ በኅቱም ድንግልና ተፀንሶ በኅቱም ድንግልና መወለድ ለዘለዓለም አዲስ ሥራ ቢሆንም በድንግልና መጸነሱም ሆነ መወለዱ በእርሱ ለእርሱ ብቻ እንጂ በማንም ሥልጣን ለማንም እስካልሆነ ድረስ ከማድነቅ ውጪ እንዴት ሊሆን ቻለ ማለት አይገባም፡፡ ይልቁንም ልደቱን በመመራመር ማወቅ አይቻልም በማመን እንጂ፤ እነዚህም ሁለት ልደታት ናቸው፡፡
1. ከዘመናት በፊት ዓለማት ሳይፈጠሩ ከእግዚአብሔር አብ ያለ እናት አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደው፡፡ መዝ 10·3 ይህ የመጀመሪያው ልደት ሲሆን፤
2. በኋላኛው ዘመን ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ በድንግልና የተወለደው ሁለተኛ ልደት ነው፡፡ ኢሳ 7·19 9·6 ማቴ 1·22-23 2·1 ገላ 4·4 ይህን ድንቅ ምሥጢር ሊቁ እንዲህ በማለት ይገልጠዋል፤ «አቤቱ ሆይ በአኗኗርህ የአብ ልጅ፣ በሰውነትህ የድንግል ልጅ፣ በመለኮትህ የአብ ልጅ፣ በትስብእትህ የሰው ልጅ፣ ለወለደህና ለወለደችህ አንድ ልጅ እንደሆንህ አመንሁብህ፡፡ አቤቱ ጌታዬ የላይኛው ቀዳማዊ ልደት ሌላ፣ የታችኛው ሁለተኛው ልደት ሌላ፣ ሰማያዊ ልደት ሌላ፣ ምድራዊ ልደት ሌላ፣ የልዕልና ልደት ሌላ፣ የትሕትና ልደትህ ሌላ፣ የፊተኛው ልደትህ ከሕይወት እሳት የተገኘ የሕይወት እሳት፣ የኋለኛው ልደት ከሴት የተወለደ አካላዊ ቃል የፊተኛውን ፈለግሁት አላገኘሁትም፤ የኋለኛውን አሰብሁት አደነቅሁት፤ የፊተኛውን ሳልደርስበት አመሰገንሁት፤ የኋለኛውን በአብራከ ልቡናዬ ሰግጄ እጅ ነሣሁት፡፡ የፊተኛው ልደት በኋለኛው ልደት ታወቀ ተረዳ፡፡ የመለኮት ወገን በድንግል ወገን ተመሰገነ፡፡ ከድንግል ከተወለድህ ወዲህ ከአብ የመወለድህ ሃይማኖት ተገልጸልን፤ ከድንግል መወለድህን በሚናገር ትንቢት ከአብ መወለድ ተረዳ፡፡ ስለዚህ ባለመጠራጠር አመንሁ» ይላል አባ ጊዮርጊስ፡፡
ምን ጊዜም የልደቱ ነገር ድንቅ ምሥጢር ነው፤ ቅዱስ ኤፍሬም እንደሚለው ሰው የሆነ እርሱን አምላክ እንደሆነ በተረዳ ነገር አውቀነዋልና ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይረቅ ረቂቅ ነው፤ ድንቅ ነው፡፡ ቃልን ወሰነችው፤ ልደቱንም ዘር አልቀደመውም፡፡ በመወለዱም ድንግልናዋን አለወጠም፤ ቃል ከአብ ያለ ድካም ወጣ፤ ከድንግልም ያለ ሕመም ተወለደ፡፡ ለዮሴፍ የታየው መልአክም ከእርሷ በመንፈስ ቅዱስ የሚወለደው ያለመለወጥ ሰው የሚሆነው የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ይኸውም ከባሕርያችን እርግማንን የሚያጠፋልን ያለወንድ ዘር የተወለደልን፣ አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ የተባለውም እነሆ ዛሬ ከቅድስት ድንግል ነፍስን ሥጋን ነሥቶ በተዋሕዶ በተገለጠ ጊዜ ተፈጸመ፡፡
አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ተመኘ፤ ቀኔንም /ልደቴን/ አይቶ ተደሰተ ተብሎ የተተነበየለት ዕለተ ምሥጢር ዕለተ ልደት ይህች ናት፡፡ እኛም ያየናት የድኅነት መጀመሪያ የዕለታት በኩር እንደሆነች ተረድተን የምናከብራት ደስታችንን የምንገልጽባት ይህች ዕለት ዕለተ አስተርዕዮ ናት፤ የማይታየው የታየባት፣ የማይዳሰሰው የተዳሰሰበት፣ የማይያዘው የተያዘባት፣ የማይታወቀው የታወቀባት፣ በትንቢት መነፅር አበው ያዩት ረቂት ብርሃን በአካል የተገለጠባት የአብንም ወላዲነት የተረዳንባት ዕለት ናት፡፡ በዚያ በአባቱ ቀኝ ሳለ በዚህ ከእናቱ ዕቅፍ ውስጥ ታየ፣ በዚያ ተሸካሚዎቹ እሳታውያን የሚሆኑ አራቱ እንስሳ ናቸው፡፡ በዚህም የተሸከመችው የፀሠራ አምስት ዓመት ብላቴና ድንግል ማርያም ናት፡፡ በዚያ ያለ እናት፣ አባት አለው፤ በዚህም ያለ ምድራዊ አባት፣ እናት አለችው፡፡
በዚያ በጽርሐ አርያም የሚደነቅ ከማይመረመር ከማይታይ አብ የመወለድ ምስጋና አለው፤ በዚህም በቤተ ልሔም የሚደነቅ ከድንግል የመለወድ ምስጋና አለው፡፡
በዚያ ኪሩቤልና ሱራፌል ከግርማው የተነሣ ይንቀጠቀጣሉ፤ በዚህ ግን ድንግል አቀፈችው፡፡ ሰሎሜም አገለገለችው፡፡ በዚያ የእሳት ዙፋን አለ፤ በዚህም የድንጋይ በረት አለው፤ በዚያ የትጉሃን ሥፍራ በሰማያት ያለች ኢየሩሳሌም አለችው፤ በዚህም የእንስሳት ጠባቂዎች ማደሪያ በዓት አለችው፡፡ በዚያ ገብርኤል በፍርሃት ይቆማል፤ በዚህም በሐሤት የምሥራች ይናገራል፡፡
በዚያ የእሳት ወላፈን ከአዳራሹ ይወጣል፤ በዚህም አህያና ላህም በእስትንፋሳቸው አሟሟቁት፡፡
እነሆ ከሰማይ ትጉሃን ይልቅ የሰው ልጅ ከበረ፤ እግዚአብሔር ከድንግል ማርያም ተወልዷልና፡፡ አንዱ የመወለዱ ምሥጢርም ይህ ነው፤ የሰውን ልጅ ከወደቀበት አንሥቶ በክብር ሰገነት ላይ ለማኖር የሰው ልጅም በጥንተ ተፈጥሮ ካገኘው ክብር የዛሬው በአዲስ ተፈጥሮ የሚያገኘው ክብር በልጧልና፡፡ የፊቱ በአምሳል በመፈጠር የተገኘ ነው፤ የአሁኑ ግን በተዋሕዶ በመወለድ የሚገኝ ነውና፡፡ የፊተኛው ሥጋ በጸጋ ከብሮ የተገኘ ነበር፤ አሁን ግን ሥጋ የባሕርይ አምላክ ሆኖ የተገኘ ከብር ነውና፡፡ የፊቱ ያለ ባሕርይ (በጸጋ) መከበር ነበር፤ ዛሬም በራስ ባሕርይ መከበር ነውና፡፡
ከአቂበ ሕግ በመውጣት ከወረደበት በታች የወረደበት ውርደት የለም፤ ዛሬም በተዋሕዶ በተደረገው ምሥጢር ከከበረበት በላይ ክብር የለም፤ በልዑል ዙፋን እስከመቀመጥ ደርሷልና፡፡
ትናንት ያልነበረ ሰውነት ከዘመን በኋላ የተገኘ ሲሆን፣ መለኮትን በመዋሓድ ሁሉን ግዙ ተብሎ ጥንት በጸጋ ከተሰጠው ግዛት በላይ ግዛቱ ድንበር የማይመልሰው ዘመን የማይለውጠው ከምድር እስከ ሰማይ የመላ ግዛት ሆነለት፡፡ መለኮት ወደሱ የመጣበት አመጣጥ ድንቅ የወደደበት ፍቅር ልዩ፣ በባሕርይ መወለዱም ዕፁብ ነውና ይህም ልደቱ ያለ ዘር የተደረገ ነው፡፡ ስለምን ቢሉ ቀዳማዊ ልደቱ የሚገለጥበት ነውና አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከእመቤታችን ያለአባት ያለዘር መወለዱ ቅድመ ዓለም ያለእናት ለመወለዱ ምሥክር መታወቂያ ነውና፡፡ ለዚህም ነው የመጀመሪያው ልደት በሁለተኛው ልደት ታወቀ የሚባለው፡፡ የሁለተኛው ልደት ክብርና ምሥጢርም ከአእምሮ በላይ በመሆኑ በመጀመሪያ ልደት ታወቀ ተረዳ፡፡ ድንቅ የሚሆን ልደቱም በምድር ላይ አባት ስለሌለው ሰው የመሆን መንገድ የጐደለው አይደለም፤ ብቻዋን ከምትሆን ከድንግል ፍጹም ሰው ሆኖ ተወለደ እንጂ ከአዳም ጐን እናት ሳይኖራት ፍጽምት ሴት እንደወጣች ፍጹም ሰው ሆነ፡፡ ማቴ 2·1-12 ሉቃ 2·8-16
የአብ ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው በሆነ ጊዜ የሕፃናትን ጠባይ ሳያስቀር የሰውነትን የጠባይ ሥርዓት እየፈጸመ ከዕለተ ፅንሰ ጀምሮ እስከ ዕለተ ልደት ድረስ በየጥቂቱ በማሕፀነ ማርያም ውስጥ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ቆይቶ ሕፃናት ሲወለዱ የሚሰማቸው ሳይሰማው ተወለደ፡፡ ሲወለድም በግብረ መንፈስ ቅዱስ በድንግልና እንደተፀነሰ በድንግልና ተወለደ እንጂ እናቱንም የድንግልና መለወጥ፣ በወሊድ ጊዜ ጭንቅና ምጥ አላገኛትም፡፡ ሕዝ 34·1 የመውለዷ ክብር ገናንነትም ከአእምሮ በላይ ነው፤ ይህ ተብሎ ሊነገር አይችልም፤ ያለ ምጥ ወልዳዋለችና፡፡
የዲያብሎስና የተከታቹን ሥነ ልቡና የሰበረ በፍርሃት እንዲዋጡ ማንነታቸውን እንዲያጡ ያደረገው አስደናቂው ልደት ጌታ በቤተ ልሔም ሲወለድ ቤተ ልሔም በብርሃን ተከባ፣ በመላእክት ምስጋና ደምቃ፣ በምሥራች ተመልታ ባየ ጊዜ የሰው ልጅ ጠላት ዲያብሎስ ይህን የልደት ምሥጢር ለማወቅ ለመመራመር ወደ ላይ ወደ ዐየር ወጣ፤ ከመሬት በታች ወደ አለው አዘቅት ወረደ፤ ዓለምን በሙሉ ዞረ፤ ግን ሊያውቅ አልቻለም፡፡ ባለማወቅ ሠወራቸው ተብሎአልና መርምሮ ማወቅ ባይቻለው የፍርሃት ጥርጥር መጠራጠር ጀምረ እንዲህ በማለት፤ የኢሳይያስ ድንግል የድንግልና ልጇን ወለደች፤ ተአምረኛው ሙሴ ሲወለድ እንዲህ ያለ ችግር አልገጠመኝም ብዙ ክብር ያላቸው ነቢያት ተወልደዋል፤ እንደዚህ ማንነቴን የሚያሳጣ ከዕውቀቴ በላይ የሆነ ችግር አልገጠመኝም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ዓለምን በሙሉ ዞርኳት፤ ይልቁንም ቤተ ልሔምን፡፡ ነገር ግን በእሷ የተደረገ የዚህን ልደት ምሥጢር ተመራምሬ ልደርስበት አልቻልኩም፡፡ ድካሜም ውጤት አልባ ሆኖአል ብሎ ወደ ወገኖቹ ቢመለስ በግምባራቸው ፍግም ብለው ወድቀው አገኛቸው፡፡ ለጊዜው እነሱን አይዟችሁ መንግሥቴ ከእኔ አታልፍም አላቸው፡፡ ከተደረገው ተአምራት ሁሉ በላይ ተአምር ቢደረግም አልፈራም ነበር፡፡ ትንቢቱ ቢደርስ ድንግል ልዑሉን ብትወልድ ይሆናል እንጂ እንዲህ ያለ ኃሣርና ውድቀት ያገኘን ምን አልባት ቤተ ልሔም አምላክ ተወልዶብሽ ይሆን ብሎ ተስፋ ባለመቁረጡ ተመልሶ ሄደ፡፡ መላእክት በአንድነት ሆነው በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እነሆ በምድር ላይ ለሰው የሰላም መሠረት ተጥሏልና እያሉ ሲያመሰግኑ፣ ደግሞ መልአኩ ለእረኞች እነሆ ለእናንተ ደስታ የሚሆን ምሥራች እነግራችኋለሁ፡፡ የዓለም መድኃኒት የሚሆን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በዳዊት ባሕርይ በዳዊት ሀገር ተወልዷልና፤ ምልክቱም አንዲት ድንግል ልጅ ሕፃኑን በክንዷ ታቅፋ ታገኛለችሁ ሲል ሰምቶ በሐዘን ላይ ሐዘን ተጨመረበት፡፡ ቢሆንም ግን እርግጡን ለማወቅ የልደት ዘመን መቼ እንደሆነ ለመረዳት የነቢያትን መጻሕፍት ትርጓሜ ወደሚያውቁ ወደ አይሁድ ሊቃውንት ዘንድ ፈጥኖ ሄዶ ስለ ክርስቶስ መወለድ አንሥቶ ያስረዱት ዘንድ አጥብቆ ጠየቃቸው፡፡ የጠየቃቸውን እንደማይሸሸጉት ተስፋ አድርጓልና እነሱም በይሁዳ አውራጃ በምትገኝ በቤተ ልሔም የዓለም መድኃኒት ይወለዳል ብለው ተናግረዋል ብለው መለሱለት፡፡ ሚክ 5·2 የዳንኤል ሱባዔስ ደርሷል? አላቸው፡፡ «አዎ» አሉት፡፡ «ይህ ሁሉ እንደደረሰ በምን አውቃለው?» አላቸው፡፡ የልደቱ መታወቂያ የጊዜው መድረስ የሚታወቅበት ከልደቱ ጋር ቀጠሮ ያለው ልደቱን የሚጠባበቅ ስምዖን የሚባል አለ፡፡ እሱን ጠይቀህ ተረዳ አሉት፡፡ ስምዖን ለልደቱ ምልክት የሆነበት ምክንያት ምንድ ነው? አላቸው፡፡ ለንጉሡ በጥሊሞስ መጻሕፍት ከእብራይስጥ ወደ ፅርዕ ሲተረጉም ኢሳይያስ እነሆ ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች ባለው የትንቢት ቃል በተሰነካከለ ጊዜ የእግዚአብሔርም መልአክ ሕፃኑን ሳታይ አትሞትም ብሎታልና ሉቃ 2·26 አሉት፡፡ ሒዶ አንተ የተባረክህ ሽማግሌ ተስፋ የምታደርገው መድኅን ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መምጫው ደርሷልን? አለው፡፡ አዎ መጥቷል፤ አለው፡፡ በምን አወቅህ? አለው፡፡ በኢሳይያስ ትንቢት በተሰነካከልኩ ጊዜ በሕማም ታሥሮ የነበረው እጄ ተፈትቷልና በዚህ አወቅሁ አለው፡፡ በመልክተኞቹ ይህን ከሰማ በኋላ እውነትም ዛሬ ገና የእኔ ክብር የሚዋረድበት፤ ያዋረድሁት አዳም ከእኔ ባርነት ነጻ የሚወጣበት ቀን ደርሰ አለ፡፡ የአዳም ልጅ ሆይ ጠላት ዲያብሎስ ላይጠቅመው ላይረባው ይህን ያህል ስለ ልደቱ ምሥጢር ለማወቅ አቀበቱን ከወጣ ቁልቁለቱን ከወረደ፣ ዓለምን በመዞር ከተንከራተተ፣ አንተማ ምን ያህል ልትደክም አይገባህ? የማንነትህ ህልውና ነውና የልደቱን ነገር ልታውቅ ይገባሀል፡፡ ግን በምርምር አይደለም፤ እንደ እረኞች በእምነት ነው እንጂ፡፡ እረኞች በምርምር ሳይሆን በምልክት ተረድተው ልደቱን አወቁ፤ አገኙትም፡፡ አንተም ከመጻሕፍት አንብበህ ከመምህራን ተረድተህ የእረኞች ምሥራች የእኔ ነው ብለህ ነው እንጂ በልደት የሠለጠነ አምላክ በጎል ተጥሎ፣ በጨርቅ ተጠቅልሎ፣ በግርግም ተኝቶ አይቶ ዲያብሎስ ፈራ፡፡ አዳም ግን የልዑልን ትሕትና አይቶ ኦ ወዮ ለዚህ ምሥጢራዊ ልደት አንክሮ ይገባል፤ መርምረው ሊያውቁት አይቻልምና፡፡ አምላኬ ለእኔ ሲል የተወለደው ይህ ልደት ብቸኛ ነው ብሎ አመሰገነ፡፡ ብቸኛ ያሰኘውም በዚህ ዓለም እናት አባት አንድ ካልሆኑ ልጅ አይወለድም፤ እሱ ግን ከአባት ያለ እናት ከእናት ያለ አባት ተወልዷልና፤ የዚህ ዓለም ልጅ በዘር በሩካቤ ይወለዳል፤ እሱ ግን ያለ ዘር ያለ ሩካቤ ተወልዷልና፡፡
የዚህ ዓለም ልጅ ልጅ ተብሎ ኑሮ የወለደ ጊዜ አባት ይባላል፤ እሱ ግን ለዘለዓለም ወልድ እየተባለ ይኖራልና፡፡
ይህች ዕለት ለፍጡራን የሚሆን ሁሉ ዕረፍት የሚሆን ወልድ ሰውነቱን በልደት የገለጠበት ዕለት ስለሆነች ፍጡራን ሁሉ መልካም ዜና ሰሙ፤ ደስም አላቸው፡፡ ደስታቸውንም ገለጡ፡፡ ሊቁ እንዳለው ሰው በመሆንህ ሥጋን በመዋሓድህ ወደዚህ ዓለም በመምጣትህ ፍጥረት ሁሉ ደስ አላቸው እንዳለ፡፡
መላእክት ባጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በድንግል እቅፍ አይተው ወሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ አሉ፡፡
ሰዎችም የፍጥረት ባለቤት እነሱን ለማዳን ልዑል ሲሆን በራሳቸው ባሕርይ በትሕትና ተወልዶ አይተው ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት አሉ፤ እንሰሳት አራዊት ለሰው በተደረገው ይቅርታና ክብር እስትንፋሳቸውን አምኀ አቀረቡ፡፡ ስሙን እየጠሩ ለዓለም መሰከሩ፡፡ ለምሳሌ ያህል ሚዳቋን ብንወስድ እንኳ ዮም ተወልደ መድኅነ ዓለም፤ ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን፤ ዮም ተወልደ ቤዛ ኵሉ ዓለም የዓለም መድኃኒት ዛሬ ተወለደ እያለች ስትዘምር ታይታለች፡፡ አስተዋይ አዕምሮ ካለ ይህ ድንቅ ምሥጢር ነው
ፊተኛ ልደቱ ፍጡራን የማያውቁት፣ በምሥጢር መሠወሪያ የተሠወረ ነው፡፡ ኋለኛ ልደቱ ግን ለእረኞች ተገለጠ፡፡ ለጥበብ ሰዎችም ታየ፡፡ በዓለምም ተሰማ፡፡ ልጄ ወንድሜ ሆይ ቃል /ወልድ/ በምድራችን ተሰማ፤ መታየቱም የታመነ ሆነ፡፡ በአባቱ መልክ /በአምላክነት ባሕርይ/ ተመላለሰ እንዳለ፡፡ መኃ 2·12-13 ጌትነቱን ለሚያምን ሁሉ አባቶቻችን በእሳት አምሳል ያዩትን እኛ ተገልጦ አየነው፤ ቃሉንም ሰማነው እያልን እንመሰክራለን፡፡ ከዚህ ሁሉ ጋር ሰው ሆነም ስንል በፍጹም ተወሕዶ ነው፤ ተዋሕዶ ማለት አንድ መሆን መዋሐድ አለመለያየት፣ የማይታየው ከሚታየው፣ የማይወስነው ከሚወሰነው፣ ጋር አንድ ሆኖ ለዘለዓለም ለመኖር አካላዊ ቃል እግዚአብጠር ወልድ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በማሕፀነ ማርያም አድሮ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መወለዱን ነው፤ ወንጌላዊው ዮሐንስም ቃል ሥጋ ሆነ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ ያለው ይህን ፍጹም ተዋሕዶ ነው፡፡ ይህም ተዋሕዶ አካላዊ መሆኑን ይገልጻል፤ ሰው ሆኖ ተወልዷልና፡፡
ስለዚህ በተዋሕዶ ለተፈጸመው ለልደት ምሥጢር አንክሮ ይገባል፡፡ ያለዘርዓ ብእሲ መፀነስ፣ ያለ ተፈትሖ መወለድ፣ ዘመን በማይቆጠርለት ሕፃን አፍ ከድንግል ጡት ወተት መፍሰስ፣ እግዚአብሔር ለመረጣቸው ለመቅደስ ካህናት ያልተደረገ ለከብት እረኞች ሰማያዊ ምሥጢር መገለጥ፣ ከሩቅ ምሥራቅ ተነሥተው የጥበበኞች በኮከብ እየተመሩ ወደ ቤተልሔም መሔድ፣ አንክሮ ይገባል፤ ከነገሥታት እጂ ወርቅ፣ ዕጣንና ከርቤ መቀበልም ድንቅ ያሰኛል፡፡ በዚያ ሰማያውያን ካህናት በወርቅ ማዕጠንት ያቀረቡትን የዕጣን መዓዛ ይቀበላል፡፡ በዚህም ዛሬ ከሰብአ ሰገል ይህን ተቀበለ፤ መላእክትና እረኞች ዝማሬን፣ እንስሳት እስትንፋሳቸውን፣ ኮከብ ብርሃኑን አቀረቡ፡፡ እኛም ይህን ተረድተን አሕዛብ ሁላችሁ በእጃችሁ አጨብጭቡ፤ በደስታም ቃል ለእግዚአብሔር እልል በሉ፤ ስሙንም አመስግኑ፤ ለጌትነቱም ምስጋና አቅርቡ እንላለን፡፡ መዝ 65·1
በአዳም በደል ያልተጸጸተ በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ያልተደሰተ የለምና የዚህ ልደት ዓላማም ሰውን ከስሕተቱ መልሶ የእግዚአብጠር ለማድረግ ነው ዮሐ 1·12-14 ይህንም ሲያደርግ አስደናቂውን ምሥጢር እያደረገ ነው፡፡ በተወለደ ጊዜ በቤተልሔም ወተትን ከድንግልና አምላክነትን ከሰውነት፣ ሕቱም ማሕፀን ከእናትነት ጋር አንድ አድርጎ አሳይቷናል፡፡ በአምላክነት ሥራ ካልሆነ በስተቀር ወተትና ድንግልና፣ እናትነትና አገልጋይነት፣ አምላክነት እና ሰውነት፣ በአንድነት ሊገኙ አይችሉምና እግዚአብሔርን አመስግኑት ሥራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት እንላለን፡፡ መዝ 65·3 በሥጋዊ ጥበብ ተራቀው ሥጋዊውን ዓለም ያወቁ የአግዚአብሔርንም ሕልውና በእምነት ሳይሆን በጥበባቸው እናውቃለን ለሚሉ ሁሉ ከሰብአ ሰገል ተምረው በእምነት ሊያውቁት ይገባል፤ የተወለደው ለእነሱም ነውና፡፡
ሆኖም ግን መምጣቱን በተስፋ ለሚጠባበቁ የልደቱን ነገር በፍጹም እምነት ለተቀበሉ ሁሉ እነሆ ያማረ የምሥራች በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ሁሉ የሕይወት ብርሃን ተወልዷልና ደስ ይበላችሁ፡፡ በብርሃኑ ጨለማ ተወግዷልና እግዚአብሔር በይሁዳ ታወቀ፡፡ ስሙም በእስራኤል ታላቅ ነው ተብሎ እንደተነገረ የእስራኤል ንጉሥ በእስራኤል ልጅ አድሮ የዳዊት አምላክ ከዳዊት ልጅ ሥጋን ተዋሕዶ ከቀድሞ ጀምሮ ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ተልከው መንፈስ ቅዱስ እንዳናገራቸው ዓለምን ለማዳን ከጽዮን የሚወጣ ከያዕቆብ በደልን የሚያርቅ ጌታ ይወርዳል፤ ይወለዳል በማለት በየወገናቸው በየዘመናቸው የተናገሩት ትንቢት እነሆ ዛሬ ተፈጸመ፡፡ እሱም እናንተን ከመውደዴ የተነሣ ሰው ለመሆን ወደናንተ መጣሁ፡፡ በሕፃንም መጠን ተወለድኩ፤ በጨርቅም ተጠቀለልኩ፤ ፍቅሬንም ገለጥኩላችሁ ብሏልና፣ እርስ በርሳችሁ የምትፋቀሩ የወንጌል ልጆች ወንድሞች ሆይ ይህን ትሕትናና ፍቅር አይተን እርስ በርሳችን እንፋቀር፡፡ ዮም ተወልደ ፍቅር ወሰላም ዮም ተወልደ ቤዛ ኵሉ ዓለም እግዚእ ወመድኅን ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን እያልንም እንዘምር፡፡

– ስብሐት ለእግዚአብሔር አብ
– ልጁን ውረድ ተወለድ ብሎ ለሰደደው ለአብ ወላዲ አሥራፂ ተብሎ መመስገን ይገባዋል፡፡
– ለወልድም ተወለደ ተብሎ መመስገን ይገባዋል፡፡
– ማሕየዊ ለሚሆን ለመንፈስ ቅዱስም ሠራፂ ተብሎ መመስገን ይገባዋል
– ሥጋን ላጸናው ለአብ ለተዋሓደ ለወልድ ላዋሓደ ለመንፈስ ቅዱስ ዛሬም ዘወትር በእውነት ምሥጋና ይገባዋል፡፡
– ለዓለሙ ሁሉ ሕይወትን ለወለደች ለድንግል ማርያም ምስጋና ይገባል፤ የድኅነታችን መመኪያ ናትና

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 ከደቀ መዝሙር አባ ሳሙኤል ንጉሤ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም አዳሪ ት/ቤት የሊቅ ተማሪ

ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች መድረስ እንደሚገባ ቅዱስ ፓትርያርኩ አሳሰቡ

የልደት ክርስቶስ በዓል የሰላምና የደስታ፣ የአንድነትና የፍቅር፣ የነፃነትና የእኩልነት በዓል ሊሆን እንደሚገባ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ አስታወቁ፡፡

ማንም ይሁን ማን፣ በየትኛውም ደረጃ ወይም አካባቢ ይኑር፣ ከሰላም ወጭ ጥቅሙን ማረጋገጥ የሚችል የለም፤ ሊኖርም አይችልም፤ በሰላም ውስጥ ሆኖ ግን ሁሉንም ማግኘት እንደሚቻል ላለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት አየታየው ውጤት ምስክር ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችንም ሆነ አገራችን ከሰው ሠራሽና ከተፈጥሮ አደጋዋች በቀላሉ ማምለጥ የሚቻለው ከሁሉ በፊት ሰላምን በአስተማማኝ ሁኔታ ይዘው ሲጓዙ እንደሆነ ቅዱስ ፓትርያርኩ ገልፀዋል፡፡
ቅዱስነታቸው አያይዘውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ተመልሶ ሰውን ከሞት ያዳነው ማንንም ሳይጎዳ በሰላም ጎዳና ብቻ ተጉዞ ነው፡፡ ጥላቻና ራስ ወዳድነት ሲያፈርሱ ሲያጠፉ እንጅ ሲያለሙ እና ሲገነቡ በየትኛውም የዓለማችን ክፍል ታይተውም፤ ተስምተውም፣ በታሪክ ሲደገፍም አይተን አናውቀም ብለዋል፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በልማትና በዕድገት እየገሠገሰች ያለች፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነገ ብሩህ ተስፋ ትሆናለች ተብላ ተስፋ የተጣለባት ሀገር ነች፡፡ ይህ ተስፋ እግዚአብሔር ባርኮልን በሃይማኖት፣ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቀለም ሳንለያይ መላ ኢትዮጵያዊያን አንድ ሆነን ያስገኘነው የልማት ፍሬ ነው በማለት ገልፀዋል፡፡ የተገኘው የልማት ፍሬ እየበረከተና እየደለበ ወደፊት እንዲቀጥልና እንዲያድግ እንጂ በማናቸውም ምክንያት ወደ ኋላ እንዲመለስና ህዝባችን መፍቀድ እንደሌለበት አያይዘው አስገንዝበዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ መላው ህዝባችን በሚገባ ማጤን ያለበት ነገር ቢኖር ምንጊዜም የችግር መፍትሔ ሰላምና ልማት እንጅ ሌላ አማራጭ መፍትሔ የሌለ መሆኑ ነው፡፡ ስለሆነም ሁሉም የአገራችን ህዝቦች የገናን የሰላም መዝሙር እየዘመሩ ለጋራ ዕድገትና ለእኩልነት፤ ለህዝቦች አንድነትና ለዘላቂ ልማት በፅናት መቆም እንደሚገባ ገለጡ፡፡
በመጨረሻም በዚህ ዓመት በሀገራችን በተከሠተው የዝናም እጥረት ምክንያት ለምግብ እጦት የተጋለጡ በርካታ ወገኖቻችን የወገንን እጅ በተስፋ እየጠበቁ ይገኛሉ፤ እነዚህ ወገኖች ግማሽ አካላችን መሆናቸውን ተገንዝበንና ጌታችን እኛን ለመፈለግ ወዳለበት የመጣበትን ፍቅር አብነት አድርገን፤ እኛም ወዳለበት በፍቅር በመሔድ በሁሉም ነገር ልንረዳቸውና አለን ከጎናችሁ ልንላቸው ይገባናል፡፡ አነሰ ሳንል በወቅቱ ፈጥነን እጃችንን ልንዘርጋላቸውና በአጠገባቸው ሆነን ልናበረታታቸው ይገባል፤ እግዚአብሔር ሁላችንን እንደወደደን እኛም ወንድሞቻችንን በመመገብ፤ በማልበስና ችግራቸውን ሁሉ በመጋራት ለእግዚአብሔርና ለወንድሞቻችን ያለንን ፍቅር ዛሬውኑ በተግባር እንድናሳይ በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡