በጅማ ማእከል የጽ/ቤት ግንባታ ለማካሔድ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ

የማኅበረ ቅዱሳን በጅማ ማዕከል ለሚያስገነባው ባለ አራት ፎቅ ሕንፃ የመሠረት ድንጋይ ታህሳስ 24 ቀን 2008 ዓ.ም ተቀመጠ፡፡የጅማ፣ ኢሊባቦር እና ጋምቤላ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የመሠረት ድንጋዩን ካስቀመጡ በኋላ በሰጡት ትምህርት “€œበመከከላችን መደማመጡ፣ መተባበሩ፣ ሲኖር እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ይሆናልና ፤የሀገረ ስብከቱን ሁለገብ ሕንፃ ከእለት ጉርሳችሁ ቀንሳችሁ እንደገነባችሁ ይህንንም ሕንፃ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ አድባራት እና መላው ምእመናን ጥረት በማድረግ የቤተ-ክርስቲያኒቷን አገልግሎት እንድታፋጥኑ” በማለት መልእክትና መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

የጅማ ማዕከል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ማሞ መኮንን ባደረጉት ንግግር ቤዝመንቱን ጨምሮ ስድስት ወለል ያለው ሕንፃ እንደሚገነባ ገልጸው፤ “€œሕንፃው ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚከናወንባቸው የአገልግሎት ክፍሎች ፣የስብሰባና የስልጠና ይኖሩታል” ብለዋል፡፡
እንደ አቶ ማሞ ገለጻ ሕንፃው ከ12 ሺህ በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች ከሚማሩበት የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፊት ለፊት መገንባቱ ማኅበሩ በከፍተኛ ተቋም ውስጥ የሚማሩ ኦርቶደክሳዊያን ወጣቶች ከዘመናዊ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የቤተክርስቲያናቸውን ትምህርተ ሃይማኖት፣ታሪክ፣ሥርዓትና ትውፊት ተምረው የቤተ-ክርስቲያኒቷ ተረካቢ እንዲሆኑ ለማስቻል ማኅበሩ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንደሚያግዘው አስረድተዋል፡፡
ሕንፃውን ለማጠናቀቅ ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ የተናገሩት አቶ ማሞ ለግንባታው መጠናቀቅ መላው የቤተ-ክርስቲያኒቱ አባላት ሁሉ “€œየድርሻችንን እንወጣ”€ በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የሕንፃ ግንባታውን ሥራ በገንዘብ ለማገዝ የምትፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለE.0.T.C MAHIBERE KIDUSAN TS/BET BUILIDING. ሒሳብ አካውንት ቁጥር 1000143436989 ብሎ መላክ እንደሚቻል አስታውቀዋል፡፡