ፊደል

ዲያቆን ዐቢይ ሙሉቀን

ፊደል፤ ፈደለ፤ ጻፈ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን፤ ትርጉሙም የጽሕፈት ሁሉ መጀመሪያ፤ ምልክት፤ የመጽሐፍ ሁሉ መነሻ ማለት ነው፡፡

ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ፊደል የሚለውን ቃል ሲተረጉሙ በቁሙ ልዩ፤ምርጥ ዘር፤ ቀለም፤ ምልክት፤ አምሳል፤ የድምጽና የቃል መልክ ሥዕል፤ መግለጫ፤ ማስታወቂያ፤ ዛቲ ፊደል፤ ሆህያተ ፊደል፤ ወዘተ በማለት ያብራሩታል፡፡

ካሕሳይ ገብረ እግዚአብሔር ሊቀ ሥልጣናት ሀብተ ማርያም ወርቅነህን ጠቅሰው፡-

፩.ፊደል ማለት መጽሔተ አእምሮ ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ያለ ፊደል ማንበብም መጻፍም አይቻልምና የአእምሮ መገመቻ፤ የምሥጢር መመልከቻ ማለት ነው፡፡

፪. ፊደል ማለት ነቅዐ ጥበብ ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የጥበብ ሁሉ መገኛ ፊደል ናትና፡፡

፫. ፊደል ማለት መራሔ ዕዉር ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የሰውን ልጅ ሁሉ ከድንቁርና ጨለማ አውጥቶ ወደ ብርሃን ዕውቀት ይመራልና፡፡

፬. ፊደል ማለት ጸያሔ ፍኖት ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ድንቁርናን ጠርጎ አጽድቶ ከፍጹም ዕውቀት ያደርሳልና፡፡

፭. ፊደል ማለት ርዕሰ መጻሕፍት ማለት ነው ምክንያቱም የመጽሐፍ ሁሉ ራስ ፊደል ነውና፡፡

፮. ፊደል ማለት ጽሑፍ ማለት ነው፣ ፊደል ማለት ፍጡር፣ ወይም መፈጠሪያ ማለት ነው ብለው አስረድተዋል፡፡

በአጠቃላይ ፊደል ማለት በዚህ መልክ የሚገለጽ ሲሆን፤ እያንዳንዱ ፊደል ሀልዎተ እግዚአብሔርን፤ የሥነ ፍጥረትን ነገር ወዘተ የሚገልጽ ትርጉም አለው፡፡

የግእዝ ፊደል ቅደም ተከተል በአበገደ ወይስ በሀለሐመ የሚለው ሐሳብ ላይ በርካታ ሊቃውንት ጠንከር ያለ ክርክር ያነሳሉ፡፡ ለምሳሌ ካሕሳይ ገብረ እግዚአብሔር በሁለቱም ጎራ ካሉት እየጠቀሱ የምሁራኑንም ሐሳብ ካቀረቡ በኋላ የእርሳቸውንም ያቀርባሉ፡፡ የተወሰኑትን እንመልከት፡-

አለቃ ኪዳነ ወልድን፤ ደስታ ተክለ ወልድን፤ መምህር ዘሚካኤል ገብረ ኢየሱስን ጠቅሰው በአበገደ እንደሚጀምር ያስረዳሉ፡፡ እንደነዚህ ሊቃውንት አባባል ሌላው ቀርቶ አብዛኞቹ የፈጣሪ መጠሪያ ስሞች በአልፋው አ ነው የሚጀምሩት ይላሉ፡፡

ለምሳሌ እግዚአብሔር፣ አኽያ (/ያ/ አይጠብቅም)፤ አዶናይ፤ ኤልሻዳይ፤ አብ፤ አውሎግዮስ፤ አማኑኤል፤ ኤሉሄ፤ ወዘተ የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊትም እግዚአብሔርን ባመሰገነበት መዝሙሩ ከአሌፍ እስከ ታው ሲደርስ የተጠቀመው በአበገደ ነው በማለት በአበገደ የሚጀምረው ትክክል እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ ስለዚህ ቀዳሚውና ትክክለኛው በአበገደ የሚነበብ ሲሆን፤ ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከአባ ፍሬምናጦስ ከሣቴ ብርሃን ጀምሮ ግን በሀለሐመ ቅደም ተከተል እያገለገለ ይገኛል፡፡

በሁለተኛው ጎራ ደግሞ የመጀመሪያውና ትክክለኛው በሀለሐመ የሚነበበው ነው ይላሉ፡፡ ከጥንት ከጥዋቱ ጀምሮ ፊደላችን የሚጀምረው በሀለሐመ ቅደም ተከተል ነው፡፡ በአበገደ ነበር የሚሉት በልማድ የመጣ ከጽርዕና እብራይስጥ በተውሶ የተገኘ ሐሳብ ነው፡፡ በዚህም ጎራ ካሕሳይ የጠቀሷቸው ዶክተር ፍሥሓ ጽዮን ካሳና አስረስ የኔሰው ግንባር ቀደምቶች ናቸው፡፡ የነሱንም መሟገቻ እንዲህ በማለት ጠቅሰውታል፡፡

‹‹…በመሠረቱ በሕገ ጠባይዕም ከአ ሀ ይቀድማል፤ አንድ ሰው ሀ ካላለ አ ማለት አይችልም፡፡ ሀ ማለት አፍ መክፈት ማለት ነው፡፡ ጥንት በሳባውያን ወይም በአግዓዝያን ቋንቋ ሀ አፍ መክፈት ማለት ሲሆን በትርጓሜም ቢሆን ሀ ትልቅ ምሥጢር ያለው ፊደል ነው፡፡ ሀ ሀገር፤ ሀ ሀብት ከማለት ጋር በግእዙ ግስ “ሀለወ” አለ፤ ኖረ፤ ነበረ ማለት ነው፡፡ ይህ የዶክተር ፍሥሐ ጽዮን ሲሆን፤ የአስረስ የኔሰውም እንዲህ ቀርቧል፡፡

ትክክለኛው የግእዝ ፊደል ቅደም ተከተል ሀለሐመ ለመሆኑ ከዕብራይስጥና ጽርዕ የማይገናኝ ለመሆኑ፡-

፩.የግእዝ ጽሑፍ ከግራ ወደ ቀኝ መሆኑ፤

፪.የዕብራውያን ፊደል ደረጃ አምስት ሲሆን የግእዝ ግን ሰባት መሆኑ፤

፫. የግእዝ ፊደሎች ተራ ቊጥር ፳፮  መሆናቸው ነው፡፡

በአጠቃላይ የፊደላቱ ቅደም ተከተል በሁለቱም ቢሆን እያንዳንዱ ፊደል ትርጉም አለው፡፡ ትርጉሙ ነገረ እግዚአብሔርን ማለትም ዘለዓለማዊነቱን፤ ፈጣሪነቱን በአጠቃላይ ትምህርተ ሃይማኖትን የሚያስረዳ ነው፡፡ በዚህ እትም የምንመለከተው ከሀ እስከ ፐ የፊደላትን ትርጉም ከትምህርተ ሃይማኖት አንጻር ይሆናል፡፡

ሀ፡- ሀልዎቱ ለአብ እምቅድመ ዓለም፤ የአብ አኗኗር ከዓለም በፊት ነው፡፡

ለ፡- ለብሰ ሥጋ እምድንግል፤ አካላዊ ቃል ከድንግል ሥጋን ተዋሐደ፡፡

ሐ፡- ሐመ ወሞተ እግዚእነ፤ ጌታችን መከራን ተቀብሎ ሞተ፡፡

መ፡- መንክር ግብሩ ለእግዚአብሔር፤ የእግዚአብሔር ሥራው ድንቅ ነው፡፡

ሠ፡- ሠረቀ በሥጋ አምላክ፤ አምላክ በሥጋ ተገለጠ

ረ፡- ረግዓት ምድር በቃሉ፤ ምድር በቃሉ ረጋች ፡፡

ሰ፡- ሰብአ ኮነ እግዚእነ፤ ጌታችን ሰው ሆነ፡፡

ቀ፡- ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ፤ በመጀመሪያ ቃል ነበረ፡፡

በ፡- በትሕትናሁ ወረደ እምሰማይ፤ ጌታችን በትሕትናው ከሰማይ ወረደ፡፡

ተ፡- ተሰብአ ወተሰገወ፤ ጌታችን ፈጽሞ ሰው ሆነ፡፡

ኀ፡- ኃያል እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር ኃያል ነው፡፡

ነ፡- ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ፤ ጌታችን ደዌያችንን ተቀበለ፣ ሕማማችንንም ተሸከመ፡፡

አ፡- አአኵቶ ወእሴብሖ ለእግዚአብሔር፤ እግዚአብሔርን ፈጽሜ አመሰግነዋለሁ፡፡

ከ፡- ከሃሊ እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር ቻይ ነው፡፡

ወ፡- ወረደ እምሰማይ እግዚእነ፤ ጌታችን ከሰማይ ወረደ፡፡

ዐ፡- ዐርገ ሰማያተ እግዚእነ፤ ጌታችን ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

ዘ፡- ዘኩሎ ይእኅዝ እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር ሁሉን የሚይዝ ነው፡፡

የ፡- የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ፤ የእግዚአብሔር ሥልጣን ኃይልን አደረገች፡፡

ደ፡- ደመረ ሥጋነ ምስለ መለኮቱ፤ ሥጋችንን ከመለኮቱ ጋር አንድ አደረገ፡፡

ገ፡- ገብረ ሰማያተ በጥበቡ፤ ጌታ በጥበቡ ሰማያትን ፈጠረ/አዘጋጀ/፡፡

ጠ፡- ጠዐሙ ወታእምሩ ከመኄር እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱና ዕወቁ፡፡

ጰ፡- ጰራቅሊጦስ መንፈሰ ጽድቅ፤ የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡

ጸ፡- ጸጋ ወክብር ተውህበ ለነ፤ ጸጋና ክብር ለእኛ ተሰጠን፡፡

ፀ፡- ፀሐየ ጽድቅ እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር የእውነት ፀሐይ ነው፡፡

ፈ፡- ፈጠረ ሰማየ ወምድረ፤ ሰማይና ምድርን ፈጠረ፡፡

ፐ፡- ፓፓኤል ስሙ ለአምላክ፤ ፓፓኤል የአምላክ ስም ነው፡፡

ከሀ እስከ ፐ ያሉት ፊደላት እንዲህ ያለ ትርጉም ሲኖራቸው በአበገደ ቅደም ተከተልም እንዲሁ የየራሳቸው ትርጉም አላቸው፡፡ በአበገደው ቅደም ተከተል መጠሪያም ስላላቸው ያን መሠረት አድርጎ ትርጉማቸውንም መመልከት ይቻላል፡፡ ለምሳሌ አ አሌፍ የሚል መጠሪያ አለው፡፡ በመሆኑም አሌፍ ማለት አብ ፈጣሬ ኵሉ ዓለም፤ ዓለምን ሁሉ የፈጠረ አብ ነው ማለት ነው፡፡ ሌሎቹም በዚህ መልክ የየራሳቸው ትርጉም ያላቸው ሲሆን፤ በዋናነት መመልከት የፈለግነው የግእዝ ፊደላት እያንዳንዳቸው ትርጉም ያላቸውና ነገረ እግዚአብሔርን መግለጽ የሚችሉ መሆናቸውን ነው፡፡

ፊደላት ነገረ እግዚአብሔርን የሚገልጹ እንደመሆናቸው ሁሉ የመጻሕፍት ራስ ናቸው፡፡ መንፈሳውያን መጻሕፍት ሁሉ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ናቸውና፡፡ እግዚአብሔር ለአበው ቃል በቃል፤ በራእይ እና በምሳሌ እየተገለጠ መልእክቱን እንዳስተላለፈ ሁሉ በመጽሐፍም ተናግሯል፡፡ «እስመ ይነግሮሙ ለሕዝቡ በመጽሐፍ፤ ለሕዝቡ በመጽሐፍ ይነግራቸዋልና» በማለት ልበ አምላክ ዳዊት እንደተናገረው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ለሕዝቡ መልእክቱን የሚናገርባቸው መጻሕፍት የሚጀምሩት ከፊደል ነው፡፡ በመሆኑም ፊደል የመጻሕፍት ሁሉ ራስም እግርም ናት፡፡ ከላይ ቢሉ ከግርጌ የምትገኝ እርሷ ናትና፡፡

እንግዲህ በዚህ እትም የሀለሐመ ፊደላትን ትርጉም ተመልክተናል በሚቀጥለው ደግሞ የአበገደን ፊደላት ትርጉም እንመለከታለን፡፡

ይቆየን

ምንጭ፤ ሐመር መጽሔት ፳፮ኛ ዓመት ቊጥር ፱

 

  የ፳፻፲፩ ዓ.ም የአጽዋማት ባሕረ ሐሳባዊ ቀመር

በዲ/ን ታደለ ሲሳይ

በዘመናት ሁሉ የነበረው ያለውና የሚኖረው፣ ሁሉን የፈጠረ በሁሉም ያለ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ በዚህን ጊዜ መኖር ጀመረ፣ በዚህን ጊዜ መኖር ያቆማል የማይባልለት የህልውናው መጀመሪያም ሆነ መጨረሻ የሌለው ዘለዓለማዊ ነው፡ “ተራሮች ሳይወለዱ ምድርም ዓለምም ሳይሠሩ ከዘላለም እስከ ዘለዓለም ድረስ አንተ ነህ”፡፡ “ኢየሱስም እውነት እውነት እላችኋለሁ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው፡፡”፣ ብሏል፡፡ በተጨማሪም፣ “ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትናና ዛሬ እስከ ዘለዓለም የሚኖር እርሱ ነውና” እንዲል /መዝ.89÷2፣ዮሐ. 8÷56-69 ዕብ.13÷8/፡፡

የሰው ልጅ ሐሳቡ፣ ንግግሩና ተግባሩ የሚከናወነው በጊዜ ነው፡፡ የጊዜያትና የዘመናት ቁጥርም ከሰው ልጅ ሕይወት ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ የጊዜያትና የዘመናት ቁጥርም ከሰው ልጅ ሕይወት ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ ዘመን ማለት በኅሊና ሲመረመር የጊዜና የዕድሜን መጠንና ልክ የሚወስን መሆኑን መጽሐፈአቡሻኸር ያስረዳል፡፡  ይህ ዘመን የሚባለው የጊዜ ዕድሜ በስያሜው አጠራር መሠረት ኃላፊ፣ የአሁንና የትንቢት/የወደፊት/  ጊዜ ተብሎ በሦስት ክፍላተ ጊዜ ይመደባል፡፡ «ወፉካሬሁሰ ለዘመን በውስተ ልብ አርአያ ወሰን ውእቱ ለጊዜ ዕድሜ ወዝንቱሰ ጊዜ ዕድሜ ዘስሙ ዘመን ይትከፈል እመንገለ ስሙ ኅበ ሠለስቱ ክፍል ኀበ ዘኅለፈ ዘመነ ወኀበ ዘይመጽእ ወኀበ ዘሀሎሂ እንዲል[1]፡፡

ከጥንተ ፍጥረት እስከ ዳግም ምጽአት ድረስ ያለው ዘመን ሁሉ በእነዚህ ሦስት ጊዜያት ሲሠፈርና ሲቆጠር ይኖራል፡፡ ያለፈውንና የሚመጣውን ዘመን ቆጥሮና ሠፍሮ መረዳትና ማስረዳት  እንደሚገባ ሲገልጽ ደግሞ፣  “ተሰአሉ  ዘቀደሙ መዋዕለ ዘኮነ እምቅድሜክሙ እምአመ ፈጠሮሙ እግዚአብሔር ለእጓለ እመሕያው ዲበ ምድር እም አጽናፈ ሰማይ እስከ አጽናፈ ሰማይ ለእመ ኮነ ዝንቱ ነገር፤ እግዚአብሔር  ሰውን በምድር ላይ ከፈጠረው ጀምሮ ከሰማይ ዳር እስከ ዳርቻዋ ድረስ ከቶ እንዲህ ያለ ታላቅ ነገር ወይም እንደ እርሱ ያለ ተሰምቶ እንደሆነ ከአንተ በፊት የነበረውን የቀድሞው ዘመን ጠይቅ”  ተብሎ ተጽፏል /ዘዳ.4÷32 ፡፡

ልበ አምላክ ዳዊትም ያለፈውን ዘመን በማስታወስ “የድሮውን ዘመን አሰብሁ፤ የዘለዓለሙን ዓመታት አሰብሁ፤ አጠነጠንሁም” በማለት ተናግሯል /መዝ.76÷51/፡፡

ዳግመኛም ይህ ዓመታትን ቆጥሮ ዘመኑን ያወቀው ልበ አምላክ ዳዊት ሲጸልይ፣ “ንግረኒ ውኅዶን ለመዋዕልየ፤ የዘመኔን አነስተኛነት ንገረኝ” ብሏል/መዝ.101÷23፡፡ ክቡር ዳዊት የዘመኑን ቁጥር ሲያሰላ እየቀነሰ እንደሚሔድ ገብቶታል፡፡ ይህ ግን ከኃጢአቱ የተነሣ አይደለም፡፡ ይልቁንም ስለ እርሱ የተጻፈው ምሥክርነት “ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ከገሰገሰ በኋላ አንቀላፋ”  ይላል/ሐዋ.13÷37/፡፡ ይህ ደግሞ ዘመንን ታረዝማለች፡፡ እንዲል /ምሳ.10÷27/

በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያን አባቶቻችንን ሥርዓት ጠብቀን፣ ሕገ እግዚአብሔርን አክብረን፣ እግዚአብሔር ሠፍሮ የሰጠንን ዘመን እርሱ በገለጸልን አቆጣጠር እየተጠቀምን በየዓመቱ አጽዋማትን እንጾማለን፣ በዓላትን እናከብራለን፡፡ በመሆኑም እንደእስካሁኑ ሁሉ ዛሬም የ2011 ዓ.ም አጽዋማትንና በዓላትን እንደሚከተለው እናወጣለን፡፡

                                                                  መባጃ ሐመር
ለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡

ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡

በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ [2]

ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡

በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡

ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ ይቆየን

ተውሳክ
ተውሳክ ማለት ለአንድ ጾም ወይም ለአንድ ዕለት የተሰጠ ልዩ ቁጥር (ኮድ) ማለት ነው፡፡ በዚህ ቁጥር መሠረትም አጽዋማትንና በዓላትን ማውጣት ይቻላል፡፡

ተውሳክ ማለት ጭማሪ፣ ተጨማሪ ማለት ሲሆን ለበዓላትና ለአጽዋማት ማውጫ ያገለግላል፡፡[3] እንዲል፡፡

መጥቅዕ ማለት ነጋሪት ወይም ደወል ማለት ነው፡፡ ነጋሪት ሲመታ፣ ደወል ሲደወል ሕዝብ ይሰበሰባል፤ መልእክትም ይተላለፋል፡፡ በዓላትና አጽዋማትም በመጥቅዕ ይሰበሰባሉ፤ መዋያቸውንም በዚህ ማወቅ ይቻላል፡፡ በዚህም መሠረት መጥቅዕ ከዕለታት ተውሳክ ጋር ተደምሮ መባጃ ሐመርን ያስገኛል፡፡

      መባጃ ሐመር = መጥቅዕ + በዓለ መጥቅዕ የዋለበት ዕለት ተውሳክ

መጥቅዕ= ያለፈው ዓመት መጥቅዕ + ጥንተ መጥቅዕ (ጥንተ መጥቅዕ በየዓመቱ የማይቀያየር ቁጥር ሲሆን ይኸውም 19 ነው፡፡)

መጥቅዕን በዚህ መንገድ ማግኘት ከቻልን፣ በዓለ መጥቅዕ እንዴት እንደሚገኝ አሁን እንመለከታለን፡፡

‹‹መጥቅዕ ሲበዛ ከመስከረም ንዛ፤ መጥቅዕ ሲያንስ ጥቅምትን ዳስ››

ይህ ታላቅ መልእክት ያለው የአባቶቻችን አባባል ሲሆን ለበዓለ መጥቅዕ ማውጫ የሚያገለግል ንግግራዊ ፎርሙላ ወይም ቀመር ነው፡፡ መጥቅዕ ሲበዛ ከመስከረም ንዛ ማለት በዓለ መጥቅዕን በጥቅምት አውል ማለት ሲሆን፣ መጥቅዕ ሲያንስ ጥቅምትን ዳስ ማለቱ መጥቅዕ ባነሰ ጊዜ በዓለ መጥቅዕን በጥቅምት አውለው ማለት ነው፡፡

መጥቅዕ በዛ የሚባለው ከዐሥራ አራት በላይ ሲሆን ነው፤ አነሰ የሚባለው ደግሞ ከዐሥራ አራት በታች ሲሆን ነው፡፡ በዚህም መሠረት መጥቅዕ ከዐሥራ አራት በላይ ከሆነ በዓለ መጥቅዕ በመስከረም ይውላል፤ መጥቅዕ ከዐሥራ አራት በታች ከሆነ ደግሞ በዓለ መጥቅዕ በጥቅምት ይውላል፡፡ ይህ ሁል ጊዜም ቢሆን የሚያገለግል ሕግ ነው፡፡ ለዚህም ነው አበው ‹‹መጥቅዕ ሲበዛ ከመስከረምንዛ፤ መጥቅዕ ሲያንስ ጥቅምትን ዳስ›› ያሉት፡፡

ለምሳሌ የ2011ን መባጃ ሐመር እንፈልግ፡፡

መባጃ ሐመርን ከመፈለጋችን በፊት ግን መጥቅዕን ማወቅ የግድ ነው፡፡ መጥቅዕን ለማወቅ ደግሞ የወንበርን ዓመታዊ ስሌት ማግኘት ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም፤

ወንበር = ቅልክ+ድልክ – 1

19

=5500+2011 -1

19

=395 ቀሪ 6-1

ወንበር =5

የ2011 ወንበር 5 ነው ማለት ነው፡፡

ከዚህ በመነሣት መጥቅዕን ለማግኘት፤

መጥቅዕ= ወንበር (ጥንተ መጥቅዕ)

= 5(19)

30

= 3 ቀሪ 5

መጥቅዕ = 5

መባጃ ሐመር = መጥቅዕ + በዓለ መጥቅዕ የዋለበት ዕለት ተውሳክ

መጥቅዕ = 5

በዓለ መጥቅዕን ለማግኘት፤ መጥቅዕ ከዐሥራ አራት በታች ስለሆነ ጥቅምት ላይ በዓለ መጥቅዕ ይውላል፡፡ ስለዚህ ጥቅምት 5 ሰኞ በዓለ መጥቅዕ ሲሆን፤ ይህ በዓለ መጥቅዕ የዋለበት ዕለት ሰኞ ተውሳኩ 6 ነው ማለት ነው፡፡

ስለዚህ፤

መባጃ ሐመር = መጥቅዕ + በዓለ መጥቅዕ የዋበት ዕለት ተውሳክ

መጥቅዕ = 5

በዓለ መጥቅዕ የዋለበት ዕለት = ሰኞ

የሰኞ ተውሳክ = 6

መባጃ ሐመር = 5 + 6 = 11

ስለዚህ የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር 11 ስለሆነ በዚህ መሠረት የ2011ን በዓላትና አጽዋማት ማውጣት ይቻላል፡፡

የመባጃ ሐመር ዋነኛ አገልግሎት ከአጽዋማት ተውሳክ ጋር እየተደመረ በዓላትንና አጽዋማትን ማስገኘት ነው፡፡ ስለዚህ የአጽዋማትንና የበዓላትን ተውሳክ ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡በመሆኑም መባጃ  ሐመሩንና የበዓላትና የአጽዋማትን ተውሳክ በመጠቀም የ2011ን የበዓላትና የአጽዋማትን መግቢያ እናገኛለን፡፡

ጾመ ነነዌ
ጾመ ነነዌ የራሱ የሆነ ተውሳክ የለውም፡፡ የሚወጣውም ያለ ተውሳክ በመባጃ ሐመር ብቻ ነው፡፡

ሀ. በዓለ መጥቅዕ በመስከረም በሚውልበት ጊዜ ጾመ ነነዌ በጥር ይውላል፡፡

ለ. በዓለ መጥቅዕ በጥቅምት በሚሆንበት ጊዜ ጾመ ነነዌ በየካቲት ይውላል፡፡

ሐ. መጥቅዕ ከ፲፬(14) በላይ ሆኖ ከዕለት ተውሳክ ጋር ስንደምረው ከ፴(30) ከበለጠ ጾመ ነነዌ በየካቲት ይውላል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት አራት ነጥቦች መቼም ቢሆን የማይለወጡ ቋሚ ሕጎች ናቸው፡፡ በመሆኑም እነዚህን አራቱን በቃል አጥንቶ መያዝ ያስፈልጋል፡፡

ምሳሌ፡- ከላይ የተመለከትነውን የ2011 ዓ.ምን ጾመ ነነዌ እናውጣ፡፡

መጥቅዕ 5 ሲሆን በዓለ መጥቅዕ ጥቅምት ሰኞ ነው፡፡ መባጃ ሐመሩ ደግሞ 11 ነው፡፡ ከላይ በ‹‹ለ››እንደተመለከትነው በዓለ መጥቅዕ በጥቅምት በሚሆንበት ጊዜ ጾመ ነነዌ በየካቲት ይውላል ብለናል፡፡ በተጨማሪም ጾመ ነነዌ ተውሳክ ስለሌላት በመባጃ ሐመርብቻ ነው የምትወጣ ብለናል፡፡ ስለዚህ መባጃ ሐመሩ 11 ስለሆነ የካቲት 11 ቀን ጾመ ነነዌ ትገባለች ማለት ነው፡፡

ዐቢይ ጾም
የዐቢይ ጾምን ተውሳክ ለማግኘት ከጾመ ነነዌ ማግስት ጀምሮ እስከ ዐቢይ ጾም ያሉትን ቀናት መቁጠር ነው፡፡ እኒህም ቀናት ፲፬(14) ናቸው፡፡ በመሆኑም የዐቢይ ጾም ተውሳክ ፲፬(14) ነው ማለት ነው፡፡

ለምሳሌ በ2011 ዓ.ም ዐቢይ ጾም የገባው፤

የዐቢይ ጾም መግቢያ = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የዐቢይ ጾም ተውሳክ

መባጃ ሐመር = 11

የዐቢይ ጾም ተውሳክ = ፲፬(14)

የዐቢይ ጾም መግቢያ = 11 + 14 = 25

የካቲት 25 የዐቢይ ጾም መግቢያ ነው ማለት ነው፡፡

ደብረ ዘይት
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ዐቢይ ጾም ያሉትን ቀናት ቆጥረን የዐቢይ ጾም ተውሳክ ፲፬(14) ነው ብለናል፡፡ የደብረ ዘይትን ተውሳክ ለማግኘትም በተመሳሳይ መልኩ ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ደብረ ዘይት ያሉትን ቀናት ስንቆጥር ፵፩(41) ቀናትን እናገኛለን፡፡ ለ፴(30) ሲካፈል ቀሪ (፲፩)11ን እናገኛለን፡፡ ስለዚህ የደብረ ዘይት ተውሳክ ፲፩(11) ነው ማለት ነው፡፡

ደብረ ዘይት = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የደብረ ዘይት ተውሳክ

= 11 + 11

= 22

ከየካቲት ቀጥሎ ያለው ወር መጋቢት ስለሆነ መጋቢት 22 ደብረዘይት ነው ማለት ነው፡፡

ሆሣዕና
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ሆሣዕና ያሉት ቀናት ፷፪(62) ናቸው፡፡ እንደተለመደው ለ፴(30) ስናካፍለው ፪(2) ቀሪ እናገኛለን፡፡ በመሆኑም የሆሣዕና ተውሳክ (፪)2 ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ሆሣዕና መግቢያ = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የሆሣዕና ተውሳክ

= 11 + 2

= 13

ሚያዝያ 13 በዓለ ሆሣዕና ነበር ማለት ነው፡፡

ስቅለት
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ስቅለት ያሉት ቀናት ሥልሳ ሰባት ናቸው፡፡ ለሠላሳ ስናካፍለው ቀሪ ፯(7)ን እናገኛለን፡፡ በመሆኑም የስቅለት ተውሳክ ፯/7/ ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ስቅለት = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የስቅለት ተውሳክ

= 11 + 7

= 18

ሚያዝያ 18 ስቅለት ነው ማለት ነው፡፡

ትንሣኤ
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ትንሣኤ ያሉት ቀናት ሥልሳ ዘጠኝ ናቸው፡፡ ለሠላሳ ስናካፍለው ቀሪ ፱(9) እናገኛለን፡፡ በመሆኑም የትንሣኤ ተውሳክ ፱ (9) ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ትንሣኤ = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የትንሣኤ ተውሳክ

= 11 + 9

= 20

ሚያዝያ 20 ትንሣኤ ነው ማለት ነው፡፡

ርክበ ካህናት
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ርክበ ካህናት ያሉት ቀናት ፺፫(93) ናቸው፡፡ ለሠላሳ ስናካፍለውቀሪ ፫(3)ን እናገኛለን፡፡ በመሆኑም የርክበ ካህናት ተውሳክ ፫(3) ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ርክበ ካህናት = የ2011 መባጃ ሐመር + የርክበ ካህናት ተውሳክ

= 11 + 3

= 14

ግንቦት 14 ርክበ ካህናት ነው ማለት ነው፡፡

ዕርገት
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ በዓለ ዕርገት ያሉት ቀናት ፻፰(108) ናቸው፡፡ ፻፰(108)ን ለ፴(30) ስናካ ፍለው ፫(3) ጊዜ ደርሶ ፲፰(18) ይቀራል፡፡ በመሆኑም የዕርገት ተውሳክ ፲፰(18) ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ዕርገት = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የስቅለት ተውሳክ

= 11 + 18

= 29

ግንቦት 29 ዕርገት ነው ማለት ነው፡፡

ጰራቅሊጦስ
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ጰራቅሊጦስ ያሉት ቀናት ፻፲፰(118)ናቸው፡፡ ፻፲፰(118)ን ለ፴(30) ስናካፍለው ፫(3) ቀሪ ፳፰(28) ይሆናል፡፡

፳፰(28) የጰራቅሊጦስ ተውሳክ ይሆናል፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ጰራቅሊጦስ = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የጰራቅሊጦስ ተውሳክ

= 11 + 28

= 39

ለ፴(30) ሲካፈል 9 ቀሪ ይሆናል፡፡ ጰራቅሊጦስ ሰኔ 9 ነው ማለት ነው፡፡

ጾመ ሐዋርያት
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ጾመ ሐዋርያት ያሉት ቀናት ፻፲፱(119) ናቸው፡፡ ፻፲፱ (119)ን ለ፴(30) ስናካፍለው ፫(3) ጊዜ ደርሶ ፳፱ (29) ይቀራል፡፡

፳፱(29) የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ጾመ ሐዋርያት = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ

= 11 + 29

= 40

40 ለ30 ሲካፈል 1 ቀሪ 10 ይሆናል፡፡

ስለዚህ ሰኔ 10 የጾመ ሐዋርያት መግቢያ ነው ማለት ነው፡፡

ጾመ ድኅነት
ከጾመ ነነዌ ማግስት እስከ ጾመ ድኅነት ያሉት ቀናት ፻፳፩(121) ናቸው፡፡ ፻፳፩(121) ለ፴(30) ሲካፈል ፬(4) ጊዜ ደርሶ ፩(1) ይቀራል፡፡ የጾመ ድኅነት ተውሳክ ፩(1) ነው ማለት ነው፡፡

በ2011 ዓ.ም፤

ጾመ ድኅነት = የ2011 ዓ.ም መባጃ ሐመር + የጾመ ድኀነት ተውሳክ

= 11 + 1

= 12

ሰኔ 12 የጾመ ድኅነት መግቢያ ዕለት ነው ማለት ነው፡፡

በአጠቃላይ የአጽዋማቱ ተውሳክ እንደሚከተለው ነው፡፡

አጽዋማት       ተውሳክ           የመዋያ ዕለት

ጾመ ነነዌ        = አልቦ (0)         የካቲት 11

ዐቢይ ጾም        = ፲፬(14)           የካቲት 26

ደብረ ዘይት       = ፲፩(11)          መጋቢት 22

ሆሣዕና          = ፪(2)             ሚያዝያ 13

ስቅለት           = ፯(7)             ሚያዝያ 18

ትንሣኤ          = ፱(9)             ሚያዝያ 20

ርክበ ካህናት      = ፫(3)             ግንቦት 14

ዕርገት           = ፲፰(18)          ግንቦት 29

ጰራቅሊጦስ       = ፳፰(28)          ሰኔ 9

ጾመ ሐዋርያት    = ፳፱(29)          ሰኔ 10

ጾመ ድኅነት       = ፩(1)            ሰኔ 12

ኢየዐርግና ኢይወርድ
እነዚህ አጽዋማት ምንም እንኳን በየዓመቱ የየራሳቸው ቀመራዊ ማውጫ ቢኖራቸውም ገደብ ግን አላቸው፡፡ ገደባቸውም በግእዝ ኢይወርድና ኢየዐርግ ሲባል፣ ኢይወርድ የታችኛው እርከን፣ ኢየዐርግ ደግሞ የላይኛው እርከን ነው፡፡ በአማርኛው ገደብ ልንለው እንችላለን፡፡ በዚህም መሠረት የአጽዋማት ገደብ የሚከተለውን ይመስላል፡፡

አጽዋማትና በዓላት          ኢይወርድ    ኢየዐርግ

ጾመ ነነዌ             ጥር 17             የካቲት 21

ዐቢይ ጾም           የካቲት 1             መጋቢት 5

ደብረ ዘይት          የካቲት 28            ሚያዝያ 2

ሆሣዕና             መጋቢት 19           ሚያዝያ 23

ስቅለት          መጋቢት 24           ሚያዝያ 28

ትንሣኤ            መጋቢት 26           ሚያዝያ 30

ርክበ ካህናት        ሚያዝያ 20             ግንቦት 24

ዕርገት             ግንቦት 5                ሠኔ 9

ጰራቅሊጦስ         ግንቦት 15               ሠኔ 19

ጾመ ሐዋርያት      ግንቦት 16               ሠኔ 20

ጾመ ድኅነት        ግንቦት 18               ሠኔ 22

ቋሚ የመግቢያ ጊዜ ያላቸው አጽዋማት
                               ጾመ ነቢያት
ጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡

                                   ጾመ ገሀ  ድ
ጾመ ገሀድ የትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡

                                   ጾመ ፍልሰታ 
ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡

[1]  አቡሻኸር አንቀጽ 1 ገጽ 17 (የብራና ጽሑፍ)

[2] ዲ/ን ታደለ ሲሳይ ባሕረ ሐሳብ በቀላል አቀራረብ ገጽ 71

[3]  ዝኒ ከማሁ ገጽ 66

1ዐ.4 ቦ / አለ/ በመራሕያን ሲረባ/ Verb to have/

ግእዝን ይማሩ 

ታኅሣሥ 24 ቀን 2007 ዓ.

1ዐ.4 ቦ / አለ/ በመራሕያን ሲረባ/ Verb to have/

ብየ= አለኝ  ምሳሌ  ምንት ብየ ምስሌኪ    ካንቺ ጋር ምን አለኝ

ብከ= አለህ         ምንት ብከ ምስሌሃ   ከርሷ ጋር ምን አለህ

ብኪ = አለሽ       ምንት ብኪ ምስሌሃ   ከርሷ ጋር ምን አለሽ

ብነ = አለን        ምንት ብነ ምስሌክሙ  ከእናንተ ጋር ምን አለን

ብክሙ=አላችሁ     ምንት ብክሙ ምስሌሆሙ  ከእነርሱ/ ከወንዶች/

                                         ጋር ምን አላችሁ

ብክን= አላችሁ / ለሴት/  ምንት ብክን ምስሌየ  ከእኔ ጋር ምን አላቸው

ቦሙ= አላቸው         ምንት ቦሙ ምስሌየ   ከእኔ ጋር ምን አላቸው

ቦን = አላቸው / ለሴት/  ምንት ቦን ምስሌኪ  ከአንቺ ጋር ምን አላቸው

ከላይ ለጠቀስናቸው አፍራሻቸው አል ነው፡፡

 

 ለምሳሌ:-

አልብየ   =  የለኝም

አልብከ   =  የለህም

አልብኪ   =  የለሽም

አልብነ    =  የለንም

አልቦ     =  የለንም፣ የሉም፣ የለም

ቦ        =  አለ ፣አለው

ዘቦ       =  ያለው

 

1ዐ.5 ባለቤት ተውላጠ ስም (Subjective Pronoun)

እግዚአብሔር ለሊሁ ፈጠረ ዓለመ / እግዚአብሔር እርሱ ራሱ ዓለምን ፈጠረ/

ለሊሁ የአምር

ለሊከ እግዚኦ ተአምር እበድየ

ለሊከ እግዚኦ ተአምር ጽእለትየ

ለሊከሰ ሕይወተ ታሐዩ

ለሊኪ አውሰብኪ

ለሊሃ ትበልዕ ኩሎ ዘትረክብ

ትአምሩ ለሊክሙ ኩሎ ነገረ ዘኮነ በይሁዳ

ለሊሁሰ እግዚእ ኢየሱስ ኢያጥመቀ ዳእሙ አርዳኢሁ/ ዳእሙ — እንጂ/

 

       ነጠላ                                ብዙ

ለሊሁ   =  እርሱ እራሱ / Himself/  ለሊሆሙ = እነርሱ እራሳቸው

                                                                (Themselves)

ለሊሃ   =  እርሷ እራሷ (Herself)   ለሊሆን  = እነርሱ / ለሴቶች/

                                               (Themselves)

ለሊከ   =  አንተ እራስህ (Yourself)   ለሊክሙ = እናንተ እራሳችሁ 

                                                                 ( Yourselves)

ለሊኪ አንቺ እራስሽ (Yourself)   ለሊክን = እናንተ እራሳችሁ /ለሴቶች/  

                                                                 ( Yourselves)

ለሊየ /ለልየ = እኔ እራሴ/ ( My self)   ለሊነ   = እኛ እራሳችን

                                                               ( 0urselves)

 

1ዐ.6 ተሳቢ ተውላጠ ስሞች ( Objective Pronouns)

ነጠላ                                        ብዙ

ኪያየ = እኔን ( Me)        ኪያነ  =  እኛን (Us)

ኪያከ = አንተን ( You)      ኪያክሙ = እናንተን (You)

ኪያኪ = አንቺን ( You)        ኪያክን  እናንተን ( You) ለሴቶች

ኪያሁ = እሱን ( Him)         ኪያሆሙ = እነርሱን ( Them)

ኪያሃ = እሷን ( Her)         ኪያሆን  =  እነርሱን ( Them  ለሴቶች/

 

ምሳሌ

ዘርእየ ኪያየ ርእየ አቡየ

መኑ ይጼውእ ኪያከ

ኪያኪ ሰናይተ ዘፈጠረ እግዚአብሔር ይትባረክ

ቀድሱ ኪያሁ ወባርኩ ስሞ

አምላክነ አድኀነ ኪያነ እሞት

ዘተወክፈ ኪያክሙ ተወክፈ ኪያየ

ፈኑ ኪያሆሙ ኀበ አሕዛብ

ርእየ ኪያክን ወተፈስሐ ብክን

® ስለዚህ ተሳቢ ማለት “ን” የሚለውን ቃል ወይም ፊደል

የሚያመጣ ማለት ነው፡፡

 

የሚያበዙ ፊደላት    

አ፡-

    ነጠላ              ብዙ              የብዙ ብዙ

    ደብር             አድባር             አድባራት

    ርእስ             አርእስት

ከዚህ ላይ የቃላቱን መጨረሻ ሁለት ፊደላት ማስተዋል ነው፡፡

ብር፣ እስ / ሳድስ ናቸው፡፡/

 

ን፡- ሀ. ደራሲ + ያን = ደራስያን

       ሠዓሊ + ያን = ሠዓልያን

    ለ. ኢትዮጵያዊ +ያን =  ኢትዮጵያውያን

    ሐ. ቅዱስ = ቅዱሳን

        ብፁዕ =  ብፁዓን

        መዘምር = መዘምራን

ከዚህ ላይ የቃላቱ የመጨረሻው ሁለት ፊደላት ራብዕና ሣልስ ናቸው፡፡

ራሲ፣ ዓሊ፣ እንደገና የመጨረሻዎቹ ሁለት ፊደላት ፁዕና ዱስ ይላል፡፡

 

ት፡- ኢትዮጵያዊት+ ያት – ኢትዮጵያውያት

    ሰማይ  = ሰማያት

    ቅድስት = ቅዱሳት

    ሠናይት = ሠናያት

v  አሁንም ቢሆን የቃላቱን ሁኔታ ማስተዋል ነው፡፡

 

መ፡- ኩሉ — ኩሎሙ         ለሊሁ — ለሊሆሙ        

     አንተ —አንትሙ       ለሊከ —ለሊክሙ

 እ፡- ኃጢአት — ኃጣውእ

፡- መርዔት= መራዕይ             ፡- ኪሩብ = ኪሩቤል

     ሌሊት = ለያልይ                 ሱራፊ = ሱራፌል

 

፡- ዕፅ = ዕፀው                                 

    አብ = አበው                                 

    እድ = እደው                                   

 

የጸያፍ አበዛዝ ምሳሌ

መምህራን፡ መምህራኖች
ደራሲያን ፡ ደራስያኖች
ቅዱሳን ፡ ቅዱሳኖች

ማስታወሻ፡- የጸያፍ አበዛዝ ማለት ፈጽሞ
ግእዝም አማርኛም ያልሆነና ከሕግ
ውጭ የሆነ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ
ከላይ የተጠቀሱት ቃላት
አላዋቂነት ካልሆነ በቀር ፈጽሞ
አይባሉም፡፡                                                                                                                                 

1ዐ.2 የአንዳንድ አገናዛቢ አጸፋዎች ዝርዝር

 ዳር 12 ቀን 2007 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፊሎሎጂ መምህር

ካልእ = ሌላ፣ ካልእከ / ሌላህ/፤ ካልእኪ የሌላሽን
ቀደምት =/የቀድሞ ሰዎች/፤ ቀደምትክሙ / የቀድሞ ሰዎች የሆኗችሁ ለእናንተ/
ክልኤ = ሁለት፣ ክልኤሆሙ / ሁለታቸው/፤ ክልኤነ / ሁለታችን /፤ ክልኤክሙ / ሁለታችሁ/

በበይናት = በመካከል እርስ በርስ፤ በበይናቲነ/ እርስ በርሳችን /፤ በበይናቲሆሙ / እርስ በርሳቸው/፤ በበይናቲክሙ / እርስ በርሳችሁ/

ኩሎ = ሁሉ፣ ኩሎሙ / ሁላችው/፤ ኩልክሙ / ሁላችሁ/፤ ኩልነ / ሁላችን/
ባሕቲት = ብቻ፣ ባሕቲቶሙ / ብቻቸውን/፤ ባሕቲትየ / ብቻየን/፤ ባሐቲታ / ብቻዋን/
አመ = ጊዜ፣ አሜሃ / በዚህ ጊዜ፣ በዚያ፣ ጊዜ፣ ወዲያው/
ሶበ = ጊዜ፣ ሶቤሃ / በዚህ ጊዜ፣ በዚያ ጊዜ፣ ወዲያው/
ጊዜ =ጊዜ፣ ጊዜሃ / በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ ወዲያው/

 

ምሳሌ

ዘትፈቅድ ለርእስከ ግበር ለካልእከ = ለራስህ የምትፈልገውን ለሌላው አድርግ፡፡
ሰማእክሙ ዘተብህለ ለቀደምትክሙ / ተብህለ = ተባለ/
ቀደምትክሙ ሰገዱ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ
ክልኤሆሙ ሖሩ ወብልዑ ኅብስተክሙ
ተፋቀሩ በበይናቲክሙ
ተማከርነ በበይናቲነ
ተሰአሉ በበይናቲሆሙ / ተሰአለ፣ ተጠያየቀ/
ኩልነ አግብርተ እግዚአብሔር ንሕነ
መጽኡ ኩሎሙ ወሰአሉ በእንተ ንጉሦሙ
ሑሩ ኩልክሙ ኀበ ቤትክሙ ለክሙ
ኩሎሙ ነቢያት አስከ ዮሐንስ ተነበዩ
መጻእኩ እምብሔር ርኁቅ ባሕቲትየ
ዝንቱ ብእሲ ነበረ ውስተ ቤቱ ለባሕቲቱ
ዘበልዐ ባሕቲቶ ይመውት ባሕቲቶ

 

የንዑስ አንቀጽ ዝርዝር እንደ አገናዛቢ ሲያገለግል


ቀቲል/ ቀቲሎት/ –መግደል፤ ቀቲልየ = መግደሌ፤ ቀቲልክሙ = መግደላችሁ
ቀተለ = ገደለ፤ ቀቲሎትየ = መግደሌ፤ ቀቲሎትክሙ = መግደላችሁ
ቀደሰ = አመሰገነ፤ ቀድሶየ = ምስጋናየ፤ ቀደሶክሙ = ማመስገናችሁ
ቀድሶትየ = ምስጋናየ፤ ቀድሶትክሙ = ማመስገናችሁ
ገቢር/ ገቢሮት/ =መሥራት፤ ገቢርየ = ሥራየ፤ ገቢርክሙ = ሥራችሁ
ገብረ = ሥራ፤ ገቢሮትየ = ሥራየ፤ ገቢሮትክሙ = ሥራችሁ

1ዐ.3 ተጠቃሽ ተውላጠ ሥም


ነጠላ                                     ብዙ
ሊተ = የእኔ ፣ ለእኔ ፣ ልኝ          ለነ = ለእኛ
ለከ = ላንተ፣ ልህ                  ለክሙ = ለእናንተ ላቹሁ
ለኪ = ላንቺ፣ ልሽ                 ለክን = ለእናንተ / ለሴት/ ላቹሁ
ሎቱ/ሎ/ = ል፣እርሱ               ሎቶ/ሎቶሙ/ሎሙ = ለእነርሱ / ለወንድ/
ብየ = በኔ፣ ብኝ፣ አለኝ             ብነ = በእኛ ብን አለን
ብከ = በአንተ፣ አለህ               ብክሙ = በእናንተ፣ ባችሁ ፣አላችሁ
ብኪ = በአንቺ አለሽ               ብክን= በእናንተ፣ ባችሁ አላቹሁ/ለሴቶች/
ቦቱ/ ቦ/ = በት አለው ፣ በእርሱ    ቦኑ/ ቦቶሙ/ = አላቸው፣ አላችሁ ባቸው/ለወንዶች/
ባቲ/ ባ/ = ባት                   ቦን / ቦቶን/ = አላቸው፣ አላችሁ፣ ባቸው /ለሴቶች/
ላቲ= ለእርሷ                      ሎሙ = ለእነርሱ / ለወንዶች/ ፣ባቸው

 

ምሳሌ

ፍታህ ሊተ እግዚኦ ወተበቀል በቀልየ
ልበ ንፁሐ ፍጥር ሊተ
ሰላም ለከ ኦ ሚካኤል መልአከ አድኅኖ
ሰላም ለኪ እንዘ ንሰግድ ንብለኪ
ሎቱ ስብሐት
አምጽኡ ላቲ አምሐ ለድንግል
ብየ እግዚአብሔር ዘየዐቀበኒ
መጽአ ብየ ሞት አመ ነበርኩ በኃጢአት
ኦ ጎልያድ አይቴኑ ትበውእ እስመ በጽሐ ብከ ዳዊት
ብኪ ግርማ ራእይ ዘየዐቢ
ወተቀትለ ቦቱ ወልዱ ለአዳም
ወተሰቅለ ባቲ ወልዳ ለማርያም
ተአገሠ ለነ ኩሎ ኃጢአተነ
ሰአሊ ለነ ቅድስት
ሰላም ለክሙ

የንባብ ምልክቶች

ነሐሴ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.

መ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

  • የማንሳት ምልክት

  • የመጣል ምልክት

  • የማጥበቅ ምልክት

አንዳንድ የግእዝ ግሶች የሚጠብቅ ድምፅ ሲኖራቸው ግማሾቹ የላቸውም፡፡

ምሳሌ፣ ቀተለ — ገደለ፣ ቀደሰ — አመሰገነ

ትውውቅ

ሰላም ለከ አኁየ                     ወ ሰላም ለከ

(ሰላም ላንተ ይሁን ወንድሜ)       (ሰላም ላንተም ወንድሜ)

መኑ ስምከ እኁየ                    ወልደ ገብርኤል ውእቱ ስምየ

(ስምህ ማን ነው ወንድሜ)         (ስሜ ወልደ ገብርኤል ነው)

ወመኑ ስመ አቡከ                  ገ/ ማርያም ውእቱ ስመ አቡየ

(ያባትህ ስም ማን ነው)            (ያባቴ ስም ገ/ማርያም ነው)

እስፍንቱ አዝማኒከ                  እሥራ ወአሐዱ

(ዕድሜህ ስንት ነው)               (ሀያ አንድ)

እም አይቴ መጻእከ                      እም ጎጃም

(ከየት መጣህ)                        (ከጎጃም)

ግብር እፎ ውእቱ                      ሚመ ኢይብል

(ሥራ እንዴት ነው)                  (ምንም አይል)

እስኩ ነዓ ነሑር ኀበ ቤተ እግዚአብሔር    ትፍስሕትየ ውእቱ

እስኪ ና ወደ ቤተክርስቲያን እንሂድ       (ደስታዬ ነው)

ሕይወት እፎ ውእቱ                      ሠናይ ውእቱ

(ሕይወት እንዴት ነው)                  (ጥሩ ነው)

እሉ አብያፂከ ውእቶሙ                    እወ

(እነዚህ ጓደኞችህ ናቸው)                (አዎ)

አይቲ ብሔሮሙ                          (ዝ እም ሲዳሞ ወዝኩሰ እም ወሎ)

(የት ነው ሀገራቸው)                     (ይህ ከሲዳሞ ነው ያ ደግሞ ከወሎ)

ትትሜህርኑ ትምህርተ ዘመነዌ              እወ እትሜሀር አነ ትምህርተ ዘመነዌ

(የዘመናዊ ትምህርት ትማራለህ)            (አዎ የዘመናዊ ትምህርት እማራለሁ)

አይቴ ውእቱ ቤተ ትምህርትከ               6 ኪሎ ውእቱ ቤተ ትምህርትየ

(ትምህርት ቤትህ የት ነው)                (6 ኪሎ ነው ትምህርት ቤቴ)

ስፍነ አመተ በጻሕከ                        ሣልሳ ዓመተ በጻሕኩ

(ስንተኛ ዓመት ደረስክ)                    (3 ዓመት ሆኖኛል)

ተአምርኑ ትምህርተ ሃይማኖትከ ወ ሀገርከ      ምንት ውእቱ ትምህርተ ሀገርየ

(የሀይማኖትህ እና የሀገርህን ትምህርት ታውቃለህ)     (የሀገሬ ትምህርት ምንድን ነው)

ንባብ፣ ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ግእዝ፣ ቅኔ ይትበሀሉ       ለእሉሰ አኣምሮሙ ቀዲሙ

(ንባብ፣ ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ይባላሉ)                 እነሱን ቀድሞ አውቃቸዋለሁ

በል እግዚእ የሀብከ ጽንአቶ ወይክስት ለከ           አሜን

(በል ጌታ ፅናትን ይስጥህ ይግለፅልህም)           (ይሁን ይደረግልኝ)

 

ግሥ አርዕስት (Root Verbs)

 

የግሥ አርዕስት ማለት ለሌሎች ግሶች መሠረት በመሆን የሚከተሏቸው ግሶች የእነርሱን የአወራረድ ባህሪ የሚከተሉ እና በአቀማመጣቸው የሚመስሏቸው ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ግልፅ የሚሆኑት በዝርዝር ሥንመለከታቸው በመሆኑ በመጀመሪያ ግር ሊለን አይገባም፡፡ የሆነው ሆኖ ለግስ ርባታ መሠረት መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም፡፡ የታወቁት የግስ አርዕስታት ስምንት ናቸው፡፡ እያንዳንዳቸውም የየራሳቸው ሠራዊት አላቸው፡፡

1. ቀተለ    2. ቀደሰ    3. ገብረ    4. አእመረ   5. ባረከ   6. ሤመ    7. ብህለ         8. ቆመ
6.1 እርባ ግስ (Tense and Nouns formation, including Adjectives)

በመጀመሪያ ግን አንድ በአንድ የስምንቱን ግሶች ቀለማት ብዛትና ዓይነት አንባቢው ማስተዋል ይገባዋል፡፡

  1. ቀተለ ፍፁም ሁሉም ግእዝ ሆኖ የላላ

  2. ቀደሰ ፍፁም ግእዝ ሆኖ የጠበቀ

  3. ገብረ ግእዝ ሳድስ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  4. አእመረ ግእዝ ሳድስ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  5. ባረከ ራብዕ ግዕዝ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  6. ሤመ ኀምስ ግእዝ ሆኖ የላላ

  7. ብህለ ሳድስ ሳድስ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  8. ቆመ ሳብዕ ግእዝ ሆኖ የላላ

ማንኛውም የቀዳማይ አንቀፅ ግስ ሁሉ ተነሽ መሆኑን በሥርዓተ ንባብ ላይ አይተናል፡፡

1. ቀተለ —- ገደለ ( past tense – ሐላፊ) / ቀዳማይ አንቀፅ/

ይቀትል — ይገድላል (future- ካልአይ— ትንቢት ወይም Present Tense – ያሁን ጊዜ)

ይቅትል —- ይገድል ዘንድ / ዘንድ አንቀፅ/

  • ቀቲል / ቀቲሎት/ — መግደል/ to kill ( infinitive) ንዑስ አንቀፅ/

ቀታሊ — የገደለ / ቅጽል –Adjective

ቀታልያን— የገደሉ /ወንዶች/ / ቅጽል ሲበዛ/

ቀታሊተ — የገደለች / ለሴት ቅጽል ሲሆን

ቀታልያት — የገደሉ / ለብዙ ሴቶች ቅጽል ሲሆን/

ቅቱል —- የተገደለ / ቅጽል — Adjective/

ቀታሊ —-ገዳይ / ስም ሲሆን/

ቀትል — ውጊያ / ጥሬ ዘር/

ቅትለት — አገዳደል / ሳቢዘር/

በ ቀተለ ምሳሌ እንሰራና ሌሎችን እንዴት እንዳሚወርዱ ካየን በኋላ ሌሎችን በራሳችን መሥራት እንችላለን፡፡

ምሳሌ፡-

አነ ቀተልኩ — እኔ ገደልኩ

አነ እቀትል — እኔ እገድላለሁ

አነ እቅትል— እገድል ዘንድ/ ዘንድ አንቀፅ/

አነ እቅትል — ልግደል / ትዕዛዝ/

አንተ ቀተልከ — አንተ ገደልክ አንቲ ቀተልኪ—- ገደልሽ

አንተ ትቀትል — አንተ ትገድላለህ አንቲ ትቀትሊ— ትገድያለሽ

አንተ ቅትል—– አንተ ግደል አንቲ ትቅትሊ —- ትገድይ ዘንድ

ንህነ ቀተልነ — ገደልን አንቲ ቅትሊ — ግደዬ

ንህነ ንቀትል — እንገድላለን አንትን ቀተልክን — ገደላችሁ /ሴ/

ንህነ ንቅትል — እንገድል ዘንድ አንትን ትቀትል —- ትገድላላችሁ / ሴ/

ንህነ ንቅትል — እንግደል አንትን ትቅትል—- ትገድሉ ዘንድ /ሴ/

አንትሙ ቀተልክሙ —ገደላችሁ /ወ/ አንትን ቅትል —- ግደሉ /ሴ/

አንትሙ ትቀትሉ —-ትገድላላችሁ/ወ/ ውእቶሙ ቀተሉ — ገደሉ /ወ/

አንትሙ ትቅትሉ —ትገድሉ ዘንድ/ወ/ ውእቶሙ ይቀትሉ —-ይገድላሉ/ወ/

አንትሙ ቅትሉ —- ግደሉ/ወ/ ውእቶሙ ይቅትሉ — ይገዳሉ ዘንድ/ወ/

ውእቱ ቀተለ — ገደለ ውእቶሙ ይቅትሉ —- ይግደሉ/ወ/

ውእቱ ይቀትል —– ይገድላል ይእቲ ቀተለት —- ገደለች

ውእቱ ይቀትል —- ይገድል ዘንድ ይእቲ ትቀትል — ትገድላለች

ውእቱ ይቅትል —- ይግደል ይእቲ ትቅትል — ትግድል ዘንድ /ሴ/

ውእቶን ቀተላ — ገደሉ /ሴ/ ይእቲ ትቅትል— ትግደል

ውእቶን ይቅትላ —- ይገድላሉ /ሴ/

ውእቶን ይቅትላ — ይገድሉ ዘንድ /ሴ/

ውእቶን ይቅትላ — ይግደሉ /ሴ/

ማስታወሻ፣ ሀ. የትንቢት( future) እና የአሁን ጊዜ( Present) በግእዝ

አንድ ዓይነት የግሥ አወራረድ / አገባብ/ አላቸው፡፡

ለ. ዘንድ አንቀጽና ትዕዛዝ አንቀጽም እንዲሁ አንድ ዓይነት ናቸው፡፡

ሐ. የእግዝ ግሶች ርባታቸውን የሚጀምሩት በቀዳማይ አንቀጽ (past) ነው፡፡

ቀተለን የሚመስሉ ግሶች ነበረ፣ ወረደ፣ ወዘተ ናቸው፡፡ ነገር ግን አወራረዳቸው ከቀተለ ሊለዩ ስለሚችሉ ማስተዋል ያስፈልጋል ፡፡

ምሳሌ ወረደ፣ ይወርድ፣ ይረድ

የግእዝ ሥርዓተ ንባብ (pronounciation)

ነሐሴ 19 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

የግእዝ ሥርዓተ ንባብ ስምንት ናቸው፡፡ እነርሱም፡- 

  1. ማንሳት                       5. ማናበብ

  2. መጣል                       6. አለማናበብ

  3. ማጥበቅ                      7. መዋጥ

  4. ማላላት                      8. መቁጠር ናቸው፡፡

1. ማንሳት፡- ይህ ሥርዓተ ንባብ የቃሉ መጨረሻ ፊደል ሳድስ ከመሆን የተለየ ሆኖ ቃሉ በከፈተኛ ድምፅ የሚነገር ወይም የሚነበብ ማለት ነው፡፡ ለዚህም ነው ሁሉም የግስ ዓይነቶች በከፍተኛ ድምፅ የተነበቡ ተነሽ ናቸው የሚባሉት፡፡

ምሳሌ፡- ነበረ = ተቀመጠ

ሐበነ = ስጠን

ተዘከረኒ = አስታውሰኝ

ውእቱ = ነው፣ ነበር፣ እሱ፣ ናቸው ወዘተርፈ፡፡

አንስት ሖራ = ሴቶች ሔዱ

ይግበሮ = ይሥራው

ያጥምቆ = ያጥምቀው

2. መጣል (ተጣይ)፡- ይህ ሥርዓተ ንባብ መጨረሻው ሳድስ ሆኖ የማይነሳ ማለት ነው፡፡

ምሳሌ፡- ማርያም፣ ሚካኤል፣ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ቤተ መንግሥት፣ ቅድስት፣ መቅደስ ወዘተርፈ፡፡

3. ማጥበቅ፡- ይህ ሥርዓተ ንባብ ከቃሉ ውስጥ የሚጠብቅ ፊደል ኖሮ ቃሉ ጠብቆ እንዲነበብ የሚያደርግ ነው፡፡

ምሳሌ፡- ቀደሰ = አመሰገነ

ሰብሐ = አመሠገነ

ተዘከሮ = አስታውሰው

ነጸረ = ተመለከተ

4. ማላላት፡- ይህ ሥርዐተ ንባብ በቃሉ ውስጥ የሚጠብቅ ፊደል ሳይኖርና ንባቡም ላልቶ ሲነበብ ነው፡፡

ምሳሌ፡- ቀተለ = ገደለ

ነበረ = ተቀመጠ (ኖረ)

አምለከ = አመለከ

ገብረ = ፈጠረ (ሠራ)

ፈጠረ = ፈጠረ (በአማርኛው ይጠብቃል)

5. ማናበብ፡- ይህ ሥርዓተ ንባብ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ቃላት እንደ አንድ ሆነው ሲናበቡና ን፣ በን ወይም የን ሲያመጡ ነው፡፡

ምሳሌ፡- ቤተ ክርስቲያን = የክርስቲያን ቤት

ቤተ መቅደስ = የማመስገኛ ቤት

ትምህርተ ሃይማኖት = የሃይማኖት ትምህርት

ድንግለ ሙሴ

ብሥራተ ገብርኤል

ዜና ሥላሴ

ውዳሴ ማርያም

ጥዑመ ልሳን

ወልደ ኢየሱስ

ተዋሕዶ ቃል

ዜና ቤተ ክርስቲያን

6. አለማናበብ፡- ይህ ሥርዓተ ንባብ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ቃላት ራሳቸውን ችለው ሲነበቡ ወይም አንዱ ላንዱ አጎላማሽ ሲሆን ነው፡፡

ምሳሌ፡- ቅዱስ አምላክ ይባላል እንጂ ቅዱስ አምላክ አይባልም፡፡

ድንግል ማርያም

መጽአ ወልድ – ወልድ መጣ

ጳውሎስ ሐዋርያ

7. መዋጥ፡- መዋጥ ማለት ከቃሉ ውስጥ ያለ ፊደል እንዲሁ ሳይጎላ በውስጠ ታዋቂነት የሚነበብ ነው፡፡ ከዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን ፊደሉ በጽሑፍ ጊዜ ግን ሥርዓቱን ጠብቆ ይጻፋል፡፡

ምሳሌ፡- ወይን (wan) ተብሎ እንጂ ወይን (wayyin) ተብሎ አይነበብም፡፡

ድንግል – ከዚህ ላይ ን ተውጣለች

ገብር – ከዚህ ላይ ደግሞ ብ ተውጣለች፡፡ ስለዚህ ገብር ባለሁለት ቀለም ነው፡፡

ኤልሳዕ ከዚህ ላይ ደግሞ ዕ ትዋጣለች፡፡

ርኩስ ኩ ተውጣለች፡፡

ከዚህ ላይ ብዙውን ጊዜ የሚዋጡት ቀለሞች ሲሆኑ መዋጥና አለመዋጣቸው ግን እንደ ንባቡና እንደትርጓመው ይለያያል፡፡

8. መቁጠር፡- ይህ ሥርዓተ ንባብ በአንድ ቃል ውስጥ የሚገኙ ፊደላትን ያለምንም መዋጥ ማንበብ ማለት ነው፡፡

ምሳሌ፡– ውእቱ ከሚለው ቃል ሁሉም ፊደላት ይነበባሉ እንጂ ሳድስ ስለሆነች ብቻ የምትዋጥ አይደለችሙ፡፡

ይእቲ፣ መላእክት፣ ማርያም፣ ማእከል፣ እኅት፣ ትማልም፣ ዮሐንስ፣ አጽፋር (ጥፍሮች) ስእርት (ፀጉር)፣ ኤልያስ፣ ብሔር (ሀገር) እሙንቱ፣ ስብሐት፣ ሐዋርያት፣ መጻሕፍት (ህ ትቆጠራለች)

ከእነዚህ ሥርዓተ ንባቦች በተጨማሪ ሌሎችም አሉ፡፡

 

ለምሳሌ፡- ወዳቂና ሰያፍ

ሀ. ወዳቂ፡- የምንለው ሥርዓተ ንባብ የቃሉ መጨረሻ ፊደል ካዕብ፣ ሳልስ፣ ራብዕ ኀምስና ሳብዕ ሆኖ የማይነሳ እና ቃሉ ሲነበብ የመጨረሻውን ፊደል በመያዝ እንዲወድቅ የሚያደርግ የሥርዓተ ንባብ ዓይነት ነው፡፡

ምሳሌ፡- ኀቤሁ ወደሱ የዚህ ቃል የመጨረሻ ፊደል ሁ ካዕብ ሲሆን ወዳቂ ነው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ልዩነቶች እንዳሉ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ ለምሳሌ ውእቱ የሚለው ነባር አንቀጽ ተነሽ እንጂ ወዳቂ አይደለም፡፡ እንዲሁም ግሶች በትዕዛዝም ሆነ በሓላፊ ሲመጡ ወዳቂ ናቸው ማለት አንችልም፡፡

 

ለምሳሌ፡- ሖሩ = ሔዱ ወይም ሑሩ = ሒዱ ብንልም ተነሽ እንጂ ወዳቂ አይደለም፡፡ ለሣልስ ምሳሌ ከይሲ ብእሲ መዋቲ መሃሪ ወዘተርፈ ሲሆኑ ግስ ከሆነ ግን አይወድቅም፡፡

 

ምሳሌ፡- ሰአሊ ለነ ቅድስት ከዚህ ላይ ሰአሊ የሚለው ቃል ወዳቂ አይደለም ለራብዕ ምሳሌ አንበሳ፣ ዜና፣ ወዘተረፈ ከዚህ ላይም በግስ የሚነገር ከሆነ አይወድቅም፡፡

 

ለምሳሌ፡- እላ አንስት ሖራ /እነዚያ ሴቶች ሔዱ/ ከዚህ ላይ « ሖራ » የሚለው ይነሳል እንጂ አይወድቅም፡፡

ለኀምስ ምሳሌ ውዳሴ፣ ቅዳሴ፣ ይባቤ፣ ወዘተረፈ

ለሳብዕ ምሳሌ ዶርሆ/ዶሮ/፣ መንበሮ፣ ቀቲሎት/

ንዑስ አንቀጽ የሆኑት ሁሉ ወዳቂ ናቸው፡፡ በተጨማሪ ቦዝ አንቀጽ የሆኑ ወዳቂዎች እንዳሉም ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን በግስ ትአዛዝ ወይም ዘንድ አንቀጽ የሆኑት ሊነሱ እንደሚችሉ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ 

አመልካች /Demonstratives/

 ነሐሴ 8 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

1. መራሕያን ያልናቸው ሁሉ አመልካቾች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የሚታወቁት ግን እንደሚከተለው በምሳሌ ቀርበዋል፤

ተክለ ማርያም ሖረ ኀበ ደብረ መንክራት

ውእቱ ሖረ ኀበ ደብረ ሊባኖስ

ውእቱ ብእሲ ሖረ ኀበ ደማስቆ

ይእቲ ወለት በልዐት ኅብስተ

ውእቶሙ ሙሉድ አእመሩ ትርጓሜ መጻሕፍት

ውእቶን አንስት ሰገዳ ለእግዚአብሔር አምላከ ኢትዮጵያ

ውእቶን አዋልድ በልዓ ኅብስተ

እሙንቱ ውሉድ አንበቡ ወንጌለ ዮሐንስ

እማንቱ አንስት ሰገዳ ለእግዚአብሔር አምላከ ኢትዮጵያ

ነጠላ                         ብዙ
ውእቱ ያ (that)          ውእቶሙ (ሙንቱ) እነዚያ (those)

ይእቲ ያቺ                  ውእቶን (ማንቱ)

  • እነዚህ ሁሉ የሩቅ ወይም በኅሊና ያለን ነገር ያመለክታሉ፡፡

2. ዝንቲ ብእሲ ሖረ ኀበ ኢየሩሳሌም፣ ይህ ሰው ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ፡፡

ዝ ብእሲ ሖረ ኀበ ኢየሩሳሌም፣
ዛቲ ብእሲት መጽአት እምደብረ ታቦር፣ የቺ ሴትዮ ከደብረ ታቦር መጣች፡፡
ዛቲ ብእሲት መጽአት እምደብረ ታቦር፣
እሉ ሰብዕ ሖሩ ኀበ ደብረ ከርቤ ግሸን፣ እነዚህ ሰዎች ወደ ደብረ ከርቤ ሔዱ
እላ ደናግል ቅዱሳት እማንቱ፣ እነዚህ ደናግል ቅዱሳት ናቸው

ነጠላ                            ብዙ
ዝ፣ ዝንቱ ይህ (This)        እሉ እነዚህ (These)

ዛ፣ ዛቲ ይች                   እላ እነዚህ

  • እነዚህ ሁሉ የቅርብን ነገር ያመለክታሉ፡፡

3. ዝኩ መምህረ ቅኔ ውእቱ = ያ ሰው የቅኔ መምህር ነው፡፡

እንትኩ ወለት እኀተ ሙሴ ይእቲ ያቺ ልጅ የሙሴ እኅት ናት

እንታክቲ አስካለ ማርያም ይእቲ

እልኩ ሰብእ ኢትዮጵያዊያን ውእቶሙ = እነዚያ ሰዎች ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡

እልክቱ

እልክቶን ደናግል መጽኣ እምገዳም = እነዚያ ደናግል ከገዳም መጡ፡፡

ነጠላ                                           ብዙ

ዝኩ፣ ዝክቱ (ዝለኩ) = ያ (that)        እልኩ፣ እልክቱ = እነዚያ (those)

እንትኩ፣ እንታክቲ = ያቺ                  እልኮን፣ እልክቶን = እነዚያ

  • እነዚህ ደግሞ እንደ ተራ ቁጥር አንድ የሩቅ ነገርን ያመለክታሉ፡፡

መልመጃ

አዛምድ (አስተፃምር፣ አስተዛምድ)

  1.  ዝኩ           አ. ሖረት

  2. ውእቱ          በ.ቀደስኪ

  3. አንታክቲ        ረ. መጽኣ

  4. እልክቱ         ደ. ነበሩ

  5. ይእቲ          ሀ. ሰገድኪ

  6. እሉ            ለ. ሖርነ

  7. እላ            ሐ. አንበብክሙ

  8. ዝክቱ          መ. ቀደሰ

  9. ዝንቱ          ሠ. ሐርክን

  10. እልኮን

  11. እልኩ

  12. እሙንቱ

የሚከተሉትን ወደ ግእዝ ተርጉም፤ ፈክር (ተርጉም) ኀበ ልሳነ ግእዝ

  1. ያች ልጅ ቆንጆ ናት፡፡

  2. እነዚያ ኤልሳቤጥና ማርያም ናቸው፡፡

  3. ያ የወንጌል ተማሪ ነው፡፡

  4. ይህ መጽሐፍ አዲስ ነው፡፡

  5. እነዚህ የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸው፡፡

              ሰላምታ

እፎ ኀደርከ ኁየ = እግዚአብሔር ይሰባሕ

(እንዴት አደርክ ወንድሜ) = (እግዚአብሔር ይመስገን)

ትምህርት እፎ ውእቱ = ሠናይ ውእቱ

(ትምህርት እንዴት ነው) = (ጥሩ ነው)

ማእዜ ውእቱ ዘፈጸምክሙ ፈተናክሙ = ዘዮም ወርኅ

(መቼ ነው ፈተናችሁን የጨረሳችሁት) = (የዛሬ ወር)

በጽባሕ አይቴ ሐዊረከ ውእቱ ዘኢረክብኩከ =ኀበ ከኒሣ /ቤተክርስቲያን/

(በማለዳው ያላገኘሁህ የት ሄደህ ነው) =ወደ ቤተክርስቲያን

በየነ ምንት =በይነ ነገረ ማርያም

(ስለምን) = (ስለ ነገረ ማርያም)

ኩሉ ሰብአ ቤትከ፣ እምከ፣ አቡከ፣ አኁከ፣ ደኅና ወእቶሙ = ወሎቱ ስብሐት

(ሁሉም ቤተሰቦችህ ደህና ናቸው) = (አዎ ምስጋና ለሱ ይሁን)

በል ሠናይ ምሴት ጌሰም ንትራከብ = ኦሆ ለኩልነ

( በል መልካም ምሽት ነገ እንገናኝ) = (እሺ ለሁላችን) 

 

መራሕያን ምድብ ተውላጠ ስሞች /Pronoun/

 ሐሴ 1 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

መራሕያን ማለት “መሪዎች” ማለት ሲሆን በግእዝ ቋንቋ አስር /10/ የሚሆኑ ተውላጠ ስሞች /መራሕያን/ አሉ፡፡ እነርሱም፡-

  1. አነ …………………..እኔ

  2. አንተ…………………. አንተ

  3. አንቲ ………………… አንቺ

  4. ውእቱ ………………. እርሱ

  5. ይእቲ ……………….  እርሷ

  6. ንሕነ ………………… እኛ

  7. አንትሙ………………. እናንተ /ለቅርብ ወንዶች/

  8. አንትን ………………. እናንተ /ለቅርብ ሴቶች/

  9. ወእቶሙ ……………… እነዚያ /ለወንዶች/

  10. ውእቶን …………….. እነዚያ /ለሴቶች/

መራሕያን በዐረፍተ ነገር

ቀደሰ (ቀዳማይ አንቀጽ Past tense) = አመሰገነ

 

  1. አነ ቀደስኩ                     6. ንሕነ ቀደስነ

  2. አንተ ቀደስከ                    7. አንትሙ ቀደስክሙ

  3. አንቲ ቀደስኪ                    8. አንትን ቀደስክን

  4. ውእቱ ቀደሰ                     9. ወእቶሙ ቀደሱ

  5. ይእቲ ቀደሰት                   10. ወእቶን ቀደሳ

የግሱ የመጨረሻ ፊደል “ከ” ከሆነ ያንኑ መለየት አለብን፡፡ ምሳሌ ሰበከ ብሎ አነ ሰበኩ (“ኩ” ይጠብቃል) ይላል እንጂ ሰበክኩ አይልም ስለዚህ ማጥበቅ አለብን ማለት ነው፡፡

1.1. ነባር አንቀጽ (Verb to be)

ውእቱ , ነው፣ ነበር፣ ነሽ፣ ነህ፣ ናችሁ

ይእቲ , ናት፣ ነበረች

ውእቶሙ (ሙንቱ) , ናቸው፣ ነበሩ (ለወንዶች)

ወእቶን (እማንቱ), ናቸው፣ ነበሩ (ለሴቶች )

ምሳሌ፡- አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ

        አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም

        አንተ ውእቱ ቤዛ ኩሉ ዓለም

       ማርያም ይእቲ መሠረተ ሕይወት

       ጳውሎስ ወጴጥሮስ መምህራን ውእቶሙ

       ሰሎሜ ወኤልሳቤጥ ቅዱሳት ውእቶን

1.2. ሥርዓተ ዐረፍተ ነገር በምሳሌ

ሕዝቅኤል ነቢይ

  • ሕዝቅኤል ነቢይ ውእቱ

  • ነቢይ ውእቱ ሕዝቅኤል

  • አኮ /አይደለም/ ነቢይ ሕዝቅኤል

“ውእቱ” ለሚለው አዎን አለው “አኮ” ነው፡፡

የሚከተሉት ከመራሕያን ከግሶች ጋር አዛምድ/አስተፃምር/

 

  1. አንትን                         ሀ ነበርኩ
  2. ውእቱ                         ለ በላዕነ
  3. አነ                             ሐ ሖርኪ
  4. ውእቶን                       መ ጸለዩ
  5. ይእቲ                          ሠ ቀተልክን

ረ መጽአት

ሰ ኖምክሙ

ሸ ሖራ

ቀ በልዐ 

ወልጥ ኀበ ልሳነ አምሃራ (ወደ አማርኛ መልስ)

  1. ንሕነ ሖርነ ኀበ አክሱም ወላስታ

  2. አንቲ ውእቱ እመ ብርሃን

  3. ማርያም ወለደት ወልደ ዘበኩራ

  4. አንተ ወአነ ሰማእነ ቃለ እግዚአብሔር

  5. እለ መኑ /አነማን/ ውእቶሙ ዘሖሩ ኀበ ገዳመ ሲና

ወደ ግእዝ መልስ /ወልጥ ኀበ ልሳነ ግእዝ/

  1. ወደ ጸሎት ቤት ሄድን

  2. እኔ ነኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሄድኩ፡፡ (ዘ=የ)

  3. እነርሱ በኅብረት ተቀመጠ (ኅቡረ = በኅብረት)

  4. ቶማስ እና ጴጥሮስ መምህራን ናቸው፡፡

  5. ማርያም ድንግል የአሮን በትር (በትር = ብትር) ናት፡፡

  6. አንተ የክርስቶስ ወንጌል ሰበክህ፡፡

  7. አንተ ሰባኪ አይደለህም፡፡

አስተካክለህ ጻፍ (ጹሑፍ በሥርዓተ ሰዋሰው)

ምሳሌ /ሐዘነ/ ማርያም አመ ተሰቅለ ክርስቶስ/ ኀዘነት ማርያም /አመተሰቅለ ክርስቶስ/

  1. /ኖመ/ አንተ ላዕለ አራት /አልጋ/

  2. /ሖረ/ አንትን ኀበ ደብረ ጽጌ

  3. /ቆመ/ ማርያ ወማርያም ቅድመ ቤተ መቅደስ

  4. /ኀደረ/ ፍሬ ጽድቅ ውስተ ቤተ አርድእት /ተማሪዎች/

  5. /አርመመ/ ሚካኤል አመ ተሰቅለ አምላክ

  6. /ተፈሥሑ/ ጻድቃን በእግዚአብሔር

 

 

ልሳነ አርድእት

 ሰኔ 19 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

ክፍል ፩

የግእዝ ቋንቋ እድገት ከየት ወዴት?

አንዲት ሀገር የራሷ የሆነው ባህሏ /ሥርዓቷ/ የሚያኮራትና ማንነቷንም የሚያንጸባርቅ በመሆኑ ልትጠብቀውና ከትወልድ ወደ ትውልድ ልታስተላልፈው የባለቤትነት ግዴታዋ ነው፡፡ በመሆኑም ሀገራችን ኢትዮጵያን ለጥቁር ሕዝቦች መኩሪያ እንድትሆን ያደረጋት የልጆቿ ሀገር ወዳድነትና ጀግንነትን የተመላው ባህሏ ብቻ ሳይሆን የሃይማኖት፤ የሥነ ፊደል ሀገር መሆኗም መጻሕፍተ ታሪክን ባነበቡ ሊቃውንት አንደበት ብቻ ሳይሆን በማዳመጥ ትውፊት /ርክክብ/ ለኅብረተሰቡ ኀቡእ ያልሆነ ነገር መሆኑ ነው ፡፡

በተጨማሪም ሀገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት ዑደት ስፍር ቀምራ የራሷን አኀዝ ያደላደለች አፍሪካዊት እመቤት ናት ብንል ጽልመት ሊጋርደው የማይችለው ገሀድ ነው፡፡

ይሁን እንጂ እኛ ልጆቿ የትናንቱን ለዛሬ ማበርከት ያልቻልን ይመስላል፡፡ ለዚህም ነው ትናንት የኢትዮጵያ መሠረተ ቋንቋ የነበረው የግእዝ ቋንቋ ከነበረበት የብሔራዊና የውል ቋንቋነት ይቅርና ዛሬ ዛሬ የት ገባ ሊባል የሚያሳፍር ሆኗል፡፡ አበው ለብዙ ዘመናት ይህን ቋንቋ በዜማ ቤቱ፣ በቅኔ ቤቱና በመጻሕፍት ቤቱ እንዳልተጠቀሙበት ሁሉ ዛሬ ግን የአበው ያለህ ብንል፤ አይደለም መግባባት ይቅርና ገና ተማሪው እንኳን ከማለዳው “ኦኾ” /እሽ/ በማለት ፈንታ “ኦኬ” ቢል ይቀድመዋል ፡፡ ይህ ግን “የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች” ሳያሠኝ አይቀርም ፡፡

እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ታሪክ መረጃ ሥነ ሐውልቶች የተሸከሙት የግእዝ ቋንቋ ሥነ ጽሑፍ የሀገራችንን ጥንተ ታሪክ የሚያስረዳ መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል፡፡ የግእዝ ተፎካካሪ የነበረው የሳባዊያን ቋንቋም በግእዝ ተልቆ /ተበልጦ/ ግእዝ የኢትዮጵያ ነገሥታት ሊቃውንት ኅብረተሰብ መግባቢያ ከመሆኑም አልፎ ከሀገር ውጭም ኢትዮጵያ ሀገረ ፊደል፣ ሀገረ አሚን መሆኗን ያስመሰከረ ልሳን ነበር፡፡ የሆነው ሆኖ ቀድሞ ከ፯ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እየተጠናከረ መሄዱ በሚነገርለት በአማርኛ ቋንቋ መሆኑ ቀርቶ በቤተ ክርስቲያንና በተወሰነው የኅብረተሰብ ክፍል ዘንድ እየተገደበ መጣ፡፡ እንዲያውም በተለይ በዘመነ ዓምደጽዮን / ከ፲፫፻፯-፲፫፻፴፯ ዓ.ም./ የንጉሡ ገድል ሁሉ የሚጻፈው በተሰባበረ አማርኛ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ለአብነት ያህል የሚከተለውን ማየት ይቻላል፡፡ 

  • ሐርልኛ ዓመደ ጽዮን
  • መላለሸ የወሰን
  • ወሀ እንዳመሰን መላላሽ የወሰን
  • ከወጅ ዜብደናን ከገንዝጠጠን
  • ምንቀረህ በወሠን ከድያ አምኖን

በተጨማሪም በዐፄ ይስሐቅ /ከ፲፬፻፯-፲፬፻፳፪ ዓ.ም./ ጊዜ ለንጉሡ የሚቀርቡት መወድሶች ከአማርኛው ላይ ያተኮሩ ይምስላሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል፡-

  • ገጽዥን ይስሐቄ ገጽ
  • አርያም ይመስል አንቀጽ
  • እሳት ይመስል ብቁጽ
  • ከመ መደልው ልጽሉጽ
  • ገጹ እንዲያስደነግጽ
  • እስራኤላዊ መደንግጽ
  • ማን አየህ ገጽ በገጽ

 

እነዚህ ግጥሞች ግን እንደምናያቸው ሙሉ በሙሉ አማርኛ አልነበሩም፡፡ ለዚህም ነው ግዊዲ የተባለው የታሪክ ተመራማሪ “ግእዝ -አማርኛ” ጽሑፎች ብሎ የሚጠራቸው፡፡ በእርግጥ ከአማርኛው ላይ ግእዝ መደመር ለአሁኑ ትውልድም የቋንቋ ጣዕም የሥነ ጽሑፍ ቃና መሆኑ አወንታዊ ምላሽ አለው፡፡

ያም ሆኖ ግን ብዙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የጽሕፈት ሥራቸውን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው ይጠቀሙበት የነበረው በዚህ ቋንቋ መሆኑን አላገደውም፡፡ እንዲያውም በዘመነ ዘርዓያዕቆብ /፲፬፻፳፮-፲፬፻፷ ዓ.ም./ መስፋፋት የነበረበት የሥነ ጽሑፍ እድገት ግእዙን የሙጥኝ ያለ ነበር፡፡ በኋላም ቢሆን በዐፄ ሱስንዮስ / ከ፲፭፻፱፱-፲፮፻፳፬ ዓ.ም./ የሃይማኖት መለወጥ ምክንያት ጋር ተያይዞ ኢየሱሳውያን (Jesuites) ጉልህ ችግር ደርሶባት የነበረችውን የሮማ (ስፔን) ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮችን ቁጥር ለማበርከት ሲሉ በአማርኛ በመጻፍ ወረቀቶችን ለመበተን ቢሞክሩም የአንድ ባሕርይ አማኝ የሆነው ዐፄ ፋሲል / ከ፲፮፻፳፬ -፲፮፻፸፬ ዓ.ም/ በመንገሥ የምእመናኑን ፍጹም ቀናዒነት ብሎም የኢየሱሳውያን ከኢትዮጵያ ምድር መውጣት ለልሳነ ግእዝ እንደገና መወለድ መስፋፋት ሆነለት፡፡ ብዙም መጻሕፍተ ግእዝ ተደረሱ፡፡ የቅኔ እድገትም ታየ፡፡ ከዐፄ ፋሲል በኋላም ነገሥታቱ ታላቅ ተሳትፎአቸውን አበርክተዋል፡፡ ስለሆነም ዐፄ ኢያሱ አድያም ሰገድ /ከ፲፮፻፸፬ -፲፮፻፱፱ ዓ.ም./ እና ሌሎችም ነገሥታት የማይጠፋ ስማቸውን በልቡናችን ቀረጸው አልፈዋል፡፡

ዳግመኛ የ፲፮ኛው እና የ፲፯ኛው ክፍለ ዘመናት ቁስር አልሽር ብሎ እንደገና በመሳፍንቱ ዘመን /ከ፲፯፻፸፯-፲፰፻፵፭ ዓ.ም/ ሀገሪቱ እርስ በርሷ በፖለቲካና በሃይማኖት ድልቅልቅ ስትዋጥ ሀገርን አንድ ማድረግ ይችል የነበረውን ነገረ-ሃይማኖት ለመረዳትና ለመወሠን ሊቃውንቱ የግእዝን መጻሕፍት ማገላበጥ ግድ ሆነባቸው፡፡ የመነጋገሪያ /የመከራከሪያ/ ምሥጢራቸው የሆነው ቅኔም ለልሳነ ግእዝ መስፋፋት ጠቀመ፡፡ የአብነት ትምህርት ቤቶችም ተስፋፉ፡፡ ፍጹም የሆነ አንድነትም ታዬ፡፡ ዛሬስ የሃይማኖት ውዝግቡን የሚፈቱት የትኞቹ እውን መጻሕፍት ይሆኑ? በእርግጥ ዛሬ ግእዝ ያወቀው ሁሉ ነገረ ሃይማኖትን ተረዳ ማለት አይደለም፡፡ የሚማረውም ለሕይወት /ለፍቅር/ ወይም ታሪክን ለማወቅ ላይሆን ይችላል፡፡ ነበርኩ ለማለትና ክዶ ለማስካድ እንዲመቸው የሚያስብም አይጠፋምና፡፡ በየዋህነት መማር ግን በአማናውያኑ አበው ቀርቷል፡፡

እንግዲህ ለግእዝ ቋንቋ መዳከም ዐቢይ ምክንያት የአማርኛ መተካት ብቻ ሳይሆን ለቋንቋው የሚሰጠው ትኩረት መላላቱ የማያወላውል ምክንያት መሆኑ ነው፡፡ ዝም ብሎ ግን ቅርስ ቅርስ ማለት ብቻ ዋጋ የለውም፡፡ “ባዶ ብራና” ካልተነበበ ምን ሊሠራልን፡፡ በተጨማሪም መንግሥትም ሆነ ማንኛውም አካል ግእዝ የቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ቅርስ መሆኑን ሊገነዘበው ይገባል፡፡ ቤተ ክህነትም ብትሆን የእነ ቅዱስ ያሬድ የዜማ መጻሕፍት እነ ድጓ፣ የዚቅ ቀለማት፤ የእነ አባ ጊዮርጊስ መጻሕፍት ፣ እነ ሰዓታት በሌላ ቋንቋ ሊዜሙ “ይቻል” ይመስል ለግእዝ የሚሰጠው እንክብካቤ ያሳዝናል፡፡

ድሮ ድሮ የቆሎ ተማሪ ለምኖ አኮፈዳውን፤ ዳዊቱን አንግቦ የሚነጋገረው በዚህ ቋንቋ ነበር፡፡ እንደዛሬው ግን ለወደፊቱ አይደለም የሚነጋገር አባባሉን የሚያጠና /የሚቀጽል/፣ በደንብ ቅኔ የሚቀኝ ይቅርና ዳዊቱን አጣርቶ መድገሙም ራሱ ያጠራጥራል፡፡ በእርግጥ በአንዳንድ የገጠር ቦታዎች የሚያስተምሩ ብዙ የሊቃውንት በረከቶች ቢኖሩም፤ ነገ የሚተካው ግን ከግእዝ ይልቅ ጣሊያንኛ፣ እንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛ ብቻ ቢማር የሚያተርፈው ይመስለዋል፡፡ ይህ ግን “አባቱን አያውቅ አያቱን ይናፍቅ” ያሠኛል፡፡

ምንጭ መጻሕፍቱ በግእዝ የሆነው የሀገራችን ታሪክንስ አንባቢና ተርጓሚ ማን ይሆን? በዚህ እኮ ነው የሀገራችንን ታሪክ ለማወቅ የውጭ መጻሕፍት ላይ ጥገኛ የምንሆነው፡፡ አንባቢውና ተርጓሚው አላዋቂ ከሆነ ደግሞ ታሪከ ሀገር ቅድምና ሀገር በምልዑ ልብ የማይመሰከርበት ይመስላል፡፡ የሚገርመው ግን ብዙዎቹ የግእዝ መጽሐፎቻችን በፈርንጆቹ ላይ የማያልቅ ፍቅርን አሳድረውባቸው ቋንቋውን እስከ ሃምሳ ዓመት ድረስ ሲያጠኑ እኛ ግን “የሞተ ቋንቋ” እንለዋለን፡፡ ቋንቋው ሞተ ከማለት ግን ታሪከ ሀገር ቅድምና ሀገር ሞተ ብንል ሳይሻል አይቀርም፡፡ ቢያንስ ቢያንስ በቤተ ክርስቲያን ለካህናቱ የምስጋናቸው አንደበት ግእዙ ነውና፡፡

እንግዲህ እናጠቃለውና ማንኛውም ክፍል /አካል/ ይህ ቋንቋ በጥንቱም ሆነ በአዲስ መልክ እንዲያድግ ጥረት ቢያደረግ፤ የቅኔ መምህራኑም የግእዝ መምህራኑም ምንም እንኳን የኑሮ ችግር ቢኖርም ለራስ የሚስማማ ቦታን ከመምረጥ ለተማሪዎች የሚስማማ ቦታን መርጦ በገጠርም ቢሆን ማስተማር ይኖርባቸዋል፡፡ የቋንቋ ምሁራንም ለዚህ እድገት አስተዋጽዖ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በመካከለኛው ክፍለ ዘመን ላይ የጥንቱ ሰዋስው (Classical Grammar) ይምጣልን፣ ይመለስልን፤ መካከለኛው ክፍለ ዘመን የጨለማ ዘመን ነው እያሉ እንዳማረሩት ሮማውያንና ግሪካውያን እንዳንሆን ያስፈራል፡፡ ስለሆነም ሥርወ ቃላትን ለመመርመር ሰዋስውን ለመለየት ግእዝ ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ ለዚህም ታላላቅ ደራሲያን ምስክሮች ናቸው፡፡ በተረፈ ግን ሁላችንም የታሪክ፣ የሀገር፣ የወገን፣ የቅርስ ባለአደራዎች መሆናችንን አንዘንጋ፤ እንቅልፉም ይብቃን፡፡

ይቆየን

 

የሰው ሰውነት ክፍሎች

ሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም. 

በመ/ርት ኖኀሚን ዋቅጅራ

ባለፈው ግእዝን ይማሩ አምዳችን ላይ የግእዝ ቁጥሮችን አጻጻፍና የንባብ ስያሜአቸውን ማቅረባችን የሚታወስ ነው፡፡ ዛሬ ደግሞ የሰውነት ክፍሎችን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡

የሰውነት ክፍሎች፣ ከአንገት በላይ የአካል ክፍሎች፣ /ክፍላተ አካላት ዘላዕለ ክሳድ/

የአንገት በላይ የአካል ክፍሎች ማለት ከእራስ ፀጉራችን ጀምሮ እስከ አንገታችን ድረስ ያሉትን የአካል ክፍሎች ያካተተ /የያዘ/ ክፍል ማለት ነው፡፡ እነዚህንም የአካል ክፍሎች ከዚህ በመቀጠል እንመለከታለን፡፡
ሰብእ – ሰው

– ሰብእ ዘተፈጥረ እምነ ሠለስቱ ባሕርየተ ነፍስ ምስለ አርባዕቱ ባሕርያተ ሥጋ ውእቱ
    ሰው የተፈጠረው ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ እና ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ ነው፡፡

– ሠለስቱ ባሕርያተ ነፍስ ብሂል
    ሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ ማለት

፩. ሕያዊት – ሕዋሳትን የምታንቀሳቅስ ሕይወት ያላት
፪. ለባዊት – ልብ የምታደርግ /የምታስብ/
፫. ነባቢት – የምትናገር

አርባዕቱ ባሕርያተ ሥጋ ብሂል
 አራቱ የሥጋ ባሕርያት ማለት 

  • ነፋስ –  የነፋስነት ባሕርይ           – አፍ – አፍ
  •   እሳት – የእሳትነት ባሕርይ          – ስን – ጥርስ
  • ማይ – የውኃነት ባሕርይ            – ልሳን – ምላስ
  •   መሬት – የመሬትነት ባሕርይ        – ቃል – ቃል
  •   ድማሕ /ናላ/ – መሀል ራስ /አናት/  – ዕዝን – ጆሮ
  • ናላ – አናት                          – መልታህ – ጉንጭ
  •  ስእርት – የራስ ፀጉር                – አንፍ – አፍንጫ  
  • ጽፍሮ – ሹርባ                       – ከንፈር – ከንፈር
  • ድንጉዝ – ጥቅል ሥራ               – ሕልቅ – አገጭ
  • ድምድማ – የተበጠረ ጎፈሬ          – ጽሕም – ጢም
  • ሲበት – ሽበት                       – ክሳድ – አንገት
  •  ገጽ – ፊት                           – ምጉንጳ – የዐይን ሽፋን
  • ፍጽም – ግንባር                     – ዓይን – ዐይን
  • ከዋላ – ኋላ                                     የድምጽ ክፍላት
  • ቅርንብ – ቅንድብ                   – ፋጻ – ፍጨት            
  • ዕዝን – ጆሮ                         – ጒሕና – ጎርናና /ወፍራም/ ድምጽ   
  •  መልታህ – ጉንጭ                  – ቃና – የዜማ ድምጽ,  እስትንፋስ – ትንፋሽ