1ዐ.2 የአንዳንድ አገናዛቢ አጸፋዎች ዝርዝር

 ዳር 12 ቀን 2007 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፊሎሎጂ መምህር

ካልእ = ሌላ፣ ካልእከ / ሌላህ/፤ ካልእኪ የሌላሽን
ቀደምት =/የቀድሞ ሰዎች/፤ ቀደምትክሙ / የቀድሞ ሰዎች የሆኗችሁ ለእናንተ/
ክልኤ = ሁለት፣ ክልኤሆሙ / ሁለታቸው/፤ ክልኤነ / ሁለታችን /፤ ክልኤክሙ / ሁለታችሁ/

በበይናት = በመካከል እርስ በርስ፤ በበይናቲነ/ እርስ በርሳችን /፤ በበይናቲሆሙ / እርስ በርሳቸው/፤ በበይናቲክሙ / እርስ በርሳችሁ/

ኩሎ = ሁሉ፣ ኩሎሙ / ሁላችው/፤ ኩልክሙ / ሁላችሁ/፤ ኩልነ / ሁላችን/
ባሕቲት = ብቻ፣ ባሕቲቶሙ / ብቻቸውን/፤ ባሕቲትየ / ብቻየን/፤ ባሐቲታ / ብቻዋን/
አመ = ጊዜ፣ አሜሃ / በዚህ ጊዜ፣ በዚያ፣ ጊዜ፣ ወዲያው/
ሶበ = ጊዜ፣ ሶቤሃ / በዚህ ጊዜ፣ በዚያ ጊዜ፣ ወዲያው/
ጊዜ =ጊዜ፣ ጊዜሃ / በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ ወዲያው/

 

ምሳሌ

ዘትፈቅድ ለርእስከ ግበር ለካልእከ = ለራስህ የምትፈልገውን ለሌላው አድርግ፡፡
ሰማእክሙ ዘተብህለ ለቀደምትክሙ / ተብህለ = ተባለ/
ቀደምትክሙ ሰገዱ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ
ክልኤሆሙ ሖሩ ወብልዑ ኅብስተክሙ
ተፋቀሩ በበይናቲክሙ
ተማከርነ በበይናቲነ
ተሰአሉ በበይናቲሆሙ / ተሰአለ፣ ተጠያየቀ/
ኩልነ አግብርተ እግዚአብሔር ንሕነ
መጽኡ ኩሎሙ ወሰአሉ በእንተ ንጉሦሙ
ሑሩ ኩልክሙ ኀበ ቤትክሙ ለክሙ
ኩሎሙ ነቢያት አስከ ዮሐንስ ተነበዩ
መጻእኩ እምብሔር ርኁቅ ባሕቲትየ
ዝንቱ ብእሲ ነበረ ውስተ ቤቱ ለባሕቲቱ
ዘበልዐ ባሕቲቶ ይመውት ባሕቲቶ

 

የንዑስ አንቀጽ ዝርዝር እንደ አገናዛቢ ሲያገለግል


ቀቲል/ ቀቲሎት/ –መግደል፤ ቀቲልየ = መግደሌ፤ ቀቲልክሙ = መግደላችሁ
ቀተለ = ገደለ፤ ቀቲሎትየ = መግደሌ፤ ቀቲሎትክሙ = መግደላችሁ
ቀደሰ = አመሰገነ፤ ቀድሶየ = ምስጋናየ፤ ቀደሶክሙ = ማመስገናችሁ
ቀድሶትየ = ምስጋናየ፤ ቀድሶትክሙ = ማመስገናችሁ
ገቢር/ ገቢሮት/ =መሥራት፤ ገቢርየ = ሥራየ፤ ገቢርክሙ = ሥራችሁ
ገብረ = ሥራ፤ ገቢሮትየ = ሥራየ፤ ገቢሮትክሙ = ሥራችሁ

1ዐ.3 ተጠቃሽ ተውላጠ ሥም


ነጠላ                                     ብዙ
ሊተ = የእኔ ፣ ለእኔ ፣ ልኝ          ለነ = ለእኛ
ለከ = ላንተ፣ ልህ                  ለክሙ = ለእናንተ ላቹሁ
ለኪ = ላንቺ፣ ልሽ                 ለክን = ለእናንተ / ለሴት/ ላቹሁ
ሎቱ/ሎ/ = ል፣እርሱ               ሎቶ/ሎቶሙ/ሎሙ = ለእነርሱ / ለወንድ/
ብየ = በኔ፣ ብኝ፣ አለኝ             ብነ = በእኛ ብን አለን
ብከ = በአንተ፣ አለህ               ብክሙ = በእናንተ፣ ባችሁ ፣አላችሁ
ብኪ = በአንቺ አለሽ               ብክን= በእናንተ፣ ባችሁ አላቹሁ/ለሴቶች/
ቦቱ/ ቦ/ = በት አለው ፣ በእርሱ    ቦኑ/ ቦቶሙ/ = አላቸው፣ አላችሁ ባቸው/ለወንዶች/
ባቲ/ ባ/ = ባት                   ቦን / ቦቶን/ = አላቸው፣ አላችሁ፣ ባቸው /ለሴቶች/
ላቲ= ለእርሷ                      ሎሙ = ለእነርሱ / ለወንዶች/ ፣ባቸው

 

ምሳሌ

ፍታህ ሊተ እግዚኦ ወተበቀል በቀልየ
ልበ ንፁሐ ፍጥር ሊተ
ሰላም ለከ ኦ ሚካኤል መልአከ አድኅኖ
ሰላም ለኪ እንዘ ንሰግድ ንብለኪ
ሎቱ ስብሐት
አምጽኡ ላቲ አምሐ ለድንግል
ብየ እግዚአብሔር ዘየዐቀበኒ
መጽአ ብየ ሞት አመ ነበርኩ በኃጢአት
ኦ ጎልያድ አይቴኑ ትበውእ እስመ በጽሐ ብከ ዳዊት
ብኪ ግርማ ራእይ ዘየዐቢ
ወተቀትለ ቦቱ ወልዱ ለአዳም
ወተሰቅለ ባቲ ወልዳ ለማርያም
ተአገሠ ለነ ኩሎ ኃጢአተነ
ሰአሊ ለነ ቅድስት
ሰላም ለክሙ