ሥረይ ግሦች

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የዚህን ዓመት የኅዳር የመጨረሻ ክፍለ ጊዜያችን የሆነውን ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ከባለፈው ትምህርታችን ቀጣይ ወይም ሦስተኛና የመጨረሻ የሆነውን ትምህርታችንን ከማቅረባችን በፊት በ ‹‹ሥረይ ግሥ›› ክፍል ሁለት ትምህርታችን ለማየት የሞከርነው  በግእዝ ቋንቋ ከግሥ ዓይነቶች አንዱ የሆነው ሥረይ ግሥን በግሥ አርእስት በቀተለ፣ በቀደሰ፣ በተንበለ፣ በባረከና በማህረከ ሥር መድበን ርባታቸውን እንደሆነ እያስታወስናችሁ በመቀጠል ደግሞ በዴገነ/ሴሰየ፣ በክህለ እና በጦመረ ሥር የሚመደቡ ሥረይ ግሦችን እናቀርብላችኋለን፡፡

ሥረይ ግሦች

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የጥቅምት ወር የመጨረሻ ክፍለ ጊዜያችን የሆነውን ትምህርት ለዛሬ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ከዚያ በፊት ግን የባለፈው ትምህርታችን ላይ ስላስተማርናችሁ ‹‹ረብሐ ግሥ›› ጥቂት እናስታውሳችሁ፡፡

ከግሥ ዓይነቶች አንዱ የሆነው ረብሐ ግሥ ዘማች ግሦችን ከቀዳማይ አንቀጽ ጀምሮ እስከ አርእስት እና ከዚያ በላይ ያሉትን ቅጽሎችን የሚያገሰግስ ማለት እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ በዚህ የግሥ ዓይነት ሥር የሚገኙት የዋህና መሠሪ ግሦች መሆናቸውንና እነርሱንም በግሥ አርእስት ማለትም በቀተለ፣ በቀደሰ፣ በተንበለ፣ በባረከ፣ በማህረከ፣ በሴሰየ፣ በክህለ እና በጦመረ ዘርዝረን ለማየት ሞክረናል፡፡ የዚህንም ግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳጠናችሁት ተስፋ እያደረግን ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናልፋለን፡፡ ከዚህ ቀጥሎ የምንመለከተው የግሥ ዓይነት ‹‹ሥረይ ግሥ›› ይባላል፡፡

ረብሐ ግሥ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የጥቅምት ወር የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜያችን ወደ ሆነው ትምህርት ከመግባታችን በፊት ስለ ባለፈው ጥቂት እናስታውሳችሁ፡፡ ከዘመን መለወጫ ጋር ተያይዞ ለንግግር የሚጠቅሙንን የመግባቢያ ዓረፍተ ነገሮችና የንግግር ስልቶች አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ ይህም ለእናንተ የንግግር ክህሎት በሚረዳ መልኩ አዘጋጅተን ያቀረብንላችሁ በ፳፻፲፬ ዓመተ ምሕረት በድረ ገጹ በቀረቡት ትምህርቶች የተማራችኋቸውን ቃላትም ሆነ ግሦች በመጠቀም እንድትለማመዷቸው በማሰብ ነው፤ ይህንን ተግባራዊ እንዳደረጋችሁትም ተስፋችን ነው፡፡

ታስታውሱ እንደሆነ ያለፈው ዓመት የመጨረሻ ትምህርታችን ስለ ነገረ ግሥና አገባብ ነበር፤ እንደሚታወቀው ዓረፍተ ነገሮችን ለመሥራት የሚጠቅሙን ከስሞች ቀጥሎ በዋነኛነት ግሦች በመሆናቸው በእነርሱ ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገን በዚህ ሳምንት ያቀረብንላችሁ ትምህርት ከግሥ ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው ‹ረብሐ› ግሥ ነው፡፡

ቃላተ አንጋር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በዘመነ ሉቃስ የመስከረም ወር ሁለተኛ ክፍለ ጊዜያችን የሆነውን ትምህርት ከማቅረባችን በፊት በባለፈው ትምህርታችን በግእዝ ቋንቋ የምንጠቀምባቸውን ዓረፍተ ነገሮች ከቤተሰቦቻችሁ፣ ከዘመዶቻችሁ፣ ከጓደኞቻችሁ እንዲሁም ከጎረቤቶቻችሁ ጋር እንድትለማመዷቸው አቅርበንላችሁ እንደነበር በማስታወስ በሚገባ ተረድታችሁ እንደተለማመዳችሁትና በቃላችሁ እንደያዛችኋቸውም ተስፋ እናደርጋለን!

የዚህ ሳምንት ትምህርታችን ደግሞ በግእዝ ቋንቋ ውስጥ የምንጠቀምባቸው የንግግር ስልቶች (ቃላተ አንጋር) ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ስለዚህም በመጀመሪያ በግእዝ ቀጥሎም በአማርኛ ስልቶቹን አከታትለን አቅርበንላችኋልና ተከታተሉን!

የግእዝ መግባቢያ ዓረፍተ ነገሮች

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! እንኳን ለዘመነ ሉቃስ አደረሳችሁ! እግዚአብሔር አምላክ አዲሱን ዓመት የሰላምና የደስታ እንዲያደርግላችሁ ከወዲሁ እንመኝላችኋለን!

አዲሱ ዓመት ቤተሰቦቻችንን፣ ዘመዶቻችንን፣ ጓደኞቻችንን እንዲሁም ጎረቤቶቻችንን የምንጠይቅበትና እንኳን አደረሳችሁ የምንልበት ጊዜ ነውና ከሰዎች ጋር ንግግር የምናደርግባቸው የመግባቢያ  ዓረፍተ ነገሮች በግእዝ ምን እንደሆኑ ታውቁ ዘንድ እንደ ዐውደ ዓመት ስጦታ እነሆ ብለናችኋል!

ነገረ ግሥ ወአገባብ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፉት ክፍሎች ዘመድ የሙሻ ዘርን የመጨረሻውን ክፍል አቅርበንላችኋል። በዚህ የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ደግሞ ስለ ‹‹የነገረ ግሥ ወአገባብ›› ይዘንላችሁ ቀርበናል። በጥሞና ተከታተሉን!

ሙሻ ዘር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፉት ክፍሎች ዘመድ ሙሻ ዘርን እና ባዕድ ሙሻ ዘርን ሰዋስውን ከሰዋስው ሳቢን ከተሳቢ እያናበቡ ዘጠኝ አገባባትን ሲያወጡ አይተናል። ከዚያ ቀጥለን ደግሞ ዛሬ የመጨረሻውን ክፍል እናያለን። መልካም ቆይታ!

ሙሻ ዘር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የሁለተኛውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹ሙሻ ዘር›› እናስተምራችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

እርባ ቅምር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የመጀመሪያውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ክፍል ሁለትን እናቀርብላችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

እርባ ቅምር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ላይ ‹‹ንዑስ አገባብ›› በሚል ርእስ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹እርባ ቅምር›› እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!