የግእዝ ቁጥሮች አጻጻፍ

ሐምሌ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

የግእዝ ቋንቁ ጥንታዊያን ከተሰኙ ቋንቋዎች መካከል አንዱ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት በቀን አቆጣጠርና በሥነ ጽሑፎቻቸው ሲጠቀሙበት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ቆይቷል፡፡ ዛሬም የግእዝ ቁጥሮች በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሰፊ ሥፍራ አላቸው፡፡

በዚህ ዓምዳችን የግእዝ ቁጥሮችን አጻጻፍና የንባብ ስያሜአቸውን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡
የግእዝ ቋንቋ እንደ ማንኛውም ቋንቋ እራሱን የቻለ የቁጥር አጻጻፍ ስልቶች አሉት፡- እነዚህ ቁጥሮች እኛ በተለምዶ አጠራር የአማርኛ ቁጥሮች ብለን እንጠራቸዋለን፡፡ ይሁን እንጂ ትክክለኛውን አካሄድ ስንመለከት በአጠቃላይ የአማርኛ ብቻ ሳይሆኑ ልክ እንደ አማርኛ ፊደሎች ሁሉ ቁጥሮቹም መነሻቸው ግእዝ መሆኑን እንረዳለን፡፡

የግእዙም ሆነ አሁን እኛ የምንጠቀምበት ቁጥር ማለትም ከዐ/ዜሮ/ ጀምረን የምንጽፈው የአማርኛ ቁጥር ሳይሆን ስያሜው ከየት እንደመጣ ትክክለኛ መረጃዎች ባይኖሩም 0፣ 1፣ 2፣ 3….. እየተባሉ የሚዘረዘሩት ቁጥሮች የዐረብኛ ቁጥሮች ተብለው እንደሚጠሩ በተለያዩ መጻሕፍት ተጽፈው እናገኛለን፡፡

በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር /የቀን መቁጠሪያ/ ላይ የምናገኛቸውን በየወቅቱ የሚከበሩተን ሃይማኖታዊ በዓላትንና ብሔራዊ በዓላትን ለማክበር የምጠቀመው የቀን አቆጣጠር የግእዝ ቁጥር /ኢትዮጵያዊ/ ቁጥር እንደሆኑ በግልጹ ልንረዳውና ተገቢውን ስያሜ አውቀን በስሙ ልንጠራው ይገባናል፡፡

የግእዝ ቁጥሮችን በዝርዝር ጽፈን መጨረስ ባንችልም ከብዙ በጥቂቱ በመሠረታዊነት የምንጠቀምባቸውን ቁጥሮች ከዚህ በመቀጠል እንመለከታለን፡፡

 

የግእዝ ቁጥሮች በአኀዝ

የግእዝ ቁጥሮች በፊደል

የዐረብኛ ቁጥር

አልቦ

0

አሐዱ

1

ክልኤቱ

2

ሠለስቱ

3

አርባዕቱ

4

ሐምስቱ

5

ስድስቱ

6

ስብዓቱ

7

ስመንቱ

8

ተሰዓቱ

9

አሠርቱ

10

፲፩

አሠርቱ ወአሐዱ

11

፲፪

አሠርቱ ወክልኤቱ

12

፲፫

አሠርቱ ወሠለስቱ

13

፲፬

አሠርቱ ወአርባዕቱ

14

፲፭

አሠርቱ ወሐምስቱ

15

፲፮

አሠርቱ ወስድስቱ

16

፲፯

አሠርቱ ወሰብዓቱ

17

፲፰

አሠርቱ ወስመንቱ

18

፲፱

አሠርቱ ወተሰዓቱ

19

እስራ

20

፳፩

እስራ ወአሐዱ

21

፳፪

እስራ ወክልኤቱ

22

፳፫

እስራ ወሠለስቱ

23

፳፬

እስራ ወአርባዕቱ

24

፳፭

እስራ ወሐምስቱ

25

፳፮

እስራ ወስድስቱ

26

፳፯

እስራ ወሰብዓቱ

27

፳፰

እስራ ወሰመንቱ

28

፳፱

እስራ ወተሰዓቱ

29

ሠላሳ

30

፴፩

ሠላሳ ወአሐዱ

31

፴፪

ሠላሳ ወክልኤቱ

32

፴፫

ሠላሳ ወሠለስቱ

33

፴፬

ሠላሳ ወአርባዕቱ

34

፴፭

ሠላሳ ወሐምስቱ

35

፴፮

ሠላሳ ወስድስቱ

36

፴፯

ሠላሳ ወሰብዓቱ

37

፴፰

ሠላሳ ወሰመንቱ

38

፴፱

ሠላሳ ወተሰዓቱ

39

አርብዓ

40

ሃምሳ

50

ስድሳ

60

ሰብዓ

70

ሰማንያ

80

ተሰዓ

90

ምዕት

100

፻፩

ምዕት ወአሐዱ

101

፻፪

ምዕት ወክልኤቱ

102

፻፫

ምዕት ወሠለስቱ

103

፻፬

ምዕት ወአርባዕቱ

104

፻፭

መዕት ወሐምስቱ

105

፻፮

ምዕት ወስድስቱ

106

፻፯

ምዕት ወሰብዓቱ

107

፻፰

ምዕት ወስመንቱ

108

፻፱

ምዕት ወተሰዓቱ

109

፻፲

ምዕት ወአሠርቱ

110

፻፲ወ፩

ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ

111

፻፲ወ፪

ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ

112

፻፲ወ፫

ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ

113

፻፲ወ፬

ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ

114

፻፲ወ፭

ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ

115

፻፲ወ፮

ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ

116

፻፲ወ፯

ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ

117

፻፲ወ፰

ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ

118

፻፲ወ፱

ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ

119

፻፳

ምዕት ወእስራ

120

፻፴

ምዕት ወሠላሳ

130

፻፵

ምዕት ወአርብዓ

140

፻፶

ምዕት ወሃምሳ

150

፻፷

ምዕት ወስድሳ

160

፻፸

ምዕት ወሰብዓ

170

፻፹

ምዕት ወሰማንያ

180

፻፺

ምዕት ወተሰዓ

190

፪፻

ክልኤቱ ምዕት

200

፪፻ወ፩

ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ

201

፪፻ወ፪

ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ

202

፪፻ወ፫

ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ

203

፪፻ወ፬

ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ

204

፪፻ወ፭

ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ

205

፪፻ወ፮

ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ

206

፪፻ወ፯

ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ

207

፪፻ወ፰

ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ

208

፪፻ወ፱

ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ

209

፪፻ወ፲

ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ

210

፪፻፲ወ፩

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ

211

፪፻፲ወ፪

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ

212

፪፻፲ወ፫

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ

213

፪፻፲ወ፬

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ

214

፪፻፲ወ፭

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ

215

፪፻፲ወ፮

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ

216

፪፻፲ወ፯

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ

217

፪፻፲ወ፰

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ

218

፪፻፲ወ፱

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ

219

፪፻፳

ክልኤቱ ምዕት ወእስራ

220

፪፻፴

ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ

230

፪፻፵

ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ

240

፪፻፶

ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ

250

፪፻፷

ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ

260

፪፻፸

ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ

270

፪፻፹

ክልኤቱ ምዕት ወሰማንያ

280

፪፻፺

ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓ

290

፫፻

ሠለስቱ ምዕት

300

፬፻

አርባዕቱ ምዕት

400

፭፻

ሐምስቱ ምዕት

500

፮፻

ስድስቱ ምዕት

600

፯፻

ስብዓቱ ምዕት

700

፰፻

ስመንቱ ምዕት

800

፱፻

ተሰዓቱ ምዕት

900

፲፻

አሠርቱ ምዕት

1000

፳፻

እስራ ምዕት

2000

፴፻

ሠላሳ ምዕት

3000

፵፻

አርብዓ ምዕት

4000

፶፻

ሃምሳ ምዕት

5000

፷፻

ሳድስ ምዕት

6000

፸፻

ሰብዓ ምዕት

7000

፹፻

ሰማንያ ምዕት

8000

፺፻

ተሰዓ ምዕት

9000

፻፻

እልፍ

10,000

፪፻፻

ክልኤቱ እልፍ

20,000

፫፻፻

ሠለስቱ እልፍ

30,000

፬፻፻

አርባዕቱ እልፍ

40,000

፭፻፻

ሐምስቱ እልፍ

50,000

፮፻፻

ስድስቱ እልፍ

60,000

፯፻፻

ሰብዓቱ እልፍ

70,000

፰፻፻

ስመንቱ እልፍ

80,000

፱፻፻

ተሰዓቱ እልፍ

90,000

፲፻፻

አሠርቱ እልፍ

100,000

፳፻፻

እስራ እልፍ

200,000

፴፻፻

ሠላሳ እልፍ

300,000

፵፻፻

አርብዓ እልፍ

400,000

፶፻፻

ሃምሳ እልፍ

500,000

፷፻፻

ስድሳ እልፍ

600,000

፸፻፻

ሰብዓ እልፍ

700,000

፹፻፻

ሰማንያ እልፍ

800,000

፺፻፻

ተሰዓ እልፍ

900,000

፻፻፻

አእላፋት

1,000,000

፲፻፻፻

ትእልፊት

10,000,000

፻፻፻፻

ትልፊታት

100,000,000

፲፻፻፻፻

ምእልፊት

1,000,000,000

 

ሰዋሰወ ግእዝ ክፍል አራት

ሐምሌ 3 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

 

  •  ፊደል ብሂል – ርዕሰ መጻሕፍት -የመጻሕፍት (የጽሑፍ) መጀመሪያ
  • ፊደል ብሂል – ነቅዓ ጥበብ – የጥበብ ምንጭ /የእውቀት መፍለቂያ/
  • ፊደል ብሂል – መጽሔተ አእምሮ – የአእምሮ መስታወት
  • ፊደል ብሂል – ጸያሔ ፍኖት – መንገድ ጠራጊ /በር ከፋች/
  • ፊደል ብሂል – መራሔ እውራን ውእቱ – ፊደል ሰዎችን ካለአዋቂነት /ከድንቁርና እውርነት አውጠቶ ወደ ብርሃን የሚመራ ነው፡፡   

ባለፈው ሳምንት አምዳችን ስለ ግእዝ ፊደላትና ስለ ዝርዋን የግእዝ ፊደላት የአዘራዘር ሥልትና የፊደላት ትርጉም ተመልክተናል፡፡ በዛሬው አምዳችን ደግሞ ስለ አማርኛ ፊደላትና የአማርኛ ዝርዋን ፊደላትን እንመለከታለን፡፡

የአማርኛ ፊደላት የምንላቸው በቁጥር ፯/ሰባት/ ናቸው፡፡ የአማርኛ ፊደላት ከጊዜ በኋላ በዋንኞቹ የግእዝ ፊደላት ላይ የተወሰነ ቅጥያ በማድረግ የተመሠረቱ ፊደላት ናቸው፡፡ የአማርኛ ፊደላት የአዘራዘር ሥልት እንደ መነሻዎቹ የግእዝ ፊደላት ሲሆን በግእዝ በካዕብ በሣልስ በራብዕ በኀምስ፣ በሳድስና በሳብዕ የአዘራዘር ሥልት ይዘረዘራሉ፡፡ የአማርኛ ፊደላት የአማርኛ ፊደል የተባሉበት ዋናው ምክንያት በግእዝ ቋንቋ በሚዘረዘሩ ግሦችና የፊደላት ትርጉም አለመጠቀሳቸውና አብዛኛውን ጊዜ በግእዝ ቋንቋ በሚጻፉ ጽሑፎችና ሥነ ጽሑፍ ላይ አለመጠቀሳቸውም ነው፡፡ ለአማርኛ ፊደላት መነሻ የሆኑትን የግእዝ ፊደላትና የአማርኛ ፊደላትን ከነአዘራዘራቸው በቅደም ተከተል ከዚህ በመቀጠል እንመለከታለን፡፡

ከዚህ የምንረዳው በፊደል ገበታ ላይ የአማርኛ ፊደላት ተብለው ከሚጠሩት ፊደላት መካከል እነዚህ ፯/ሰባት/ ፊደላት ብቻ ሌሎቹ የግእዝ ፊደላት መሆናቸው ነው፡፡

መነሻ የግእዝ ፊደላት

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ኀምስ

ሳድስ

ሳብዕ

       ሰ

 

 

 

 

 

 

        ተ

 

 

 

 

 

 

        ነ

 

 

 

 

 

 

       ከ

 

 

 

 

 

 

        ዘ

 

 

 

 

 

 

        ደ

 

 

 

 

 

 

        ጠ

 

 

 

 

 

 

 

ከዚህ በመቀጠል ደግሞ የአማርኛ ፊደል ዲያሎችን /ዝርዋን የአማርኛ/ ፊደላትን እንመለከታለን፡፡

ዝርዋን የአማርኛ ፊደላት
ዝርዋን ማለት ብትን ሕግንና ቅደም ተከተልን ያልጠበቀ ማለት ነው፡፡ ዝርዋን የአማርኛ ፊደላት የምንላቸው በግእዝና በአማርኛ ፊደላት ላይ በተለየ መልኩ በራብዑ /በአራተኛው/ ፊደል ዝርዝር ላይ በስተመጨረሻ ወይም ከላይ ቅጥያ በማድረግ የተፈጠረ ፊደልና በአንድ ነጠላ ዝርዝር ብቻ የሚገለጽ በአማርኛ ጽሑፍ ላይ ብቻ የሚገኝ የፊደል ዝርዝር ነው፡፡ ዝርዋን የአማርኛ ፊደላት አብዛኛውን ጊዜ የሚያገለግሉት በአንስታይ /በሴት/ ጾታ ማለትም በሩቅ ድርጊት አመልካች በነጠላ የሴት ጾተ የሚገለጸውን ቃል የእራስነትዋን ለመግለጽ የምንጠቀምበትን ቃል ሁለት ተከታታይ ሳድስና ራብዕ ፊደላትን በመዋጥ በአንድ ፊደል በዝርው የአማርኛ ፊደል በመተካት የፊደላትን ቁጥር በመቀነስ ያገለግላል፡፡

ዝርዋን የአማርኛ ፊደላት የሚባሉት
           ሏ፣ ሟ፣ ሿ፣ ሯ፣ ቧ፣ ቷ፣ ዟ፣ ዧ፣……. ናቸው፡፡

ምሳሌ፡- ልብዋ …. ልቧ፣ ቤተሰብዋ…..ቤተሰቧ
           እርስዋ… እርሷ፣ እጅዋ….. እጇ ወዘተ…….

ለዛሬ ያለንን አምድ በዚህ እናበቃለን በቀጣይ ሳምንት የግእዝ አኀዝ ቁጥሮችን የአጻጻፍና የአነባበብ ሥልት እንመለከታለን እስከዚያው ቸር ይግጠመን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ሰዋሰወ ግእዝ ክፍል ሦስት

ሰኔ 26 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

ባለፈው ሳምንት አምዳችን ከ፳፮ (26)ቱ የግእዝ ፊደላት መካከል የ፲፫(13)ቱን የግእዝ ፊደላት ቅርጽ ከነትርጒማቸው መግለጻችን ይታወቃል፡፡

ዛሬ ደግሞ ተከታዮቹን አሥራ ሦስት (፲፫) ፊደላት እንመልከት

፲፬. ከ ብሂል- ከሃሊ እግዚአብሔር፡፡
      ከማለት – እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነው፡፡

፲፭. ወብሂል – ወረደ እም ሰማይ እግዚእነ
      ወ ማለት -ጌታችን ከሰማይ ወረደ፡፡

፲፮. ዐ ብሂል – ዐርገ ሰማያተ እግዚእነ፡፡
      ዐ ማለት – ጌታችን ወደሰማይ ወጣ /ዐረገ/፡፡

፲፯. ዘ ብሂል – ዘኲሎ ይእኅዝ እግዚአብሔር፡፡
      ዘ ማለት -እግዚአብሔር ይይዛል /ሁሉን የሚይዝ ነው/፡፡

፲፰. የ ብሂል – የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኀይለ፡፡
      የ ማለት – የእግዚአብሔር ቀኝ ኀይልን አደረገች፡፡

፲፱. ደ ብሂል – ደመረ ሥጋነ ምስለ መለኮቱ፡፡
      ደ ማለት – ሥጋችንን ከመለኮት ጋር አንድ አደረገልን፡፡

፳. ገ ብሂል – ገብረ ሰማያተ በጥበቡ፡፡
     ገ ማለት – ሰማያትን በጥበቡ ሠራ፡፡

፳፩. ጠ ብሂል – ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር፡፡
      ጠ ማለት – የእግዚአብሔርን ቸርነት ታውቁ ዘንድ ቅመሱ፡፡

፳፪. ጰ ብሂል – ጰራቅሊጦስ መንፈሰ ጽድቅ፡፡
      ጰ ማለት – ጰራቅሊጦስ የእውነት መንፈስ ነው፡፡

፳፫. ፀ ብሂል – ፀሐይ ጸልመ በጊዜ ስቅለቱ ለእግዚእነ፡፡
      ፀ ማለት – ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ፀሐይ ጨለመ፡፡

፳፬. ጸ ብሂል – ጸጋ ወክብር ተውህበ ለነ፡፡
      ጸ ማለት – ጸጋ እና ክብር ለእኛ ተሰጠን፡፡

፳፭. ፈ ብሂል – ፈጠረ ሰማየ ወምድረ፡፡
      ፈ ማለት እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ፡፡

፳፮. ፐ ብሂል – ፓፓኤል ሥሙ ለአምላክ፡፡
      ፐ ማለት – ፓፓኤል የአምላክ ስም ነው፡፡ 

ከዚህ በመቀጠል ዝርዋን የግእዝ ፊደላትን /የግእዝ ፊደል ዲቃሎች/ ተብለው የሚጠሩትን ፈደላትና በፊደል ገበታ ላይ በስተመጨረሻ ተጽፈው የምናገኛቸውን ፊደላት እንመለከታለን፡፡

  • በፊደል ገበታ ላይ በስተመጨረሻ ተጽፈው የምናገኛቸው ከዋናው የፊደል የአጻጻፍ ቅርጽ ወጣ ያሉ ሁለት ዓይነት ፊደላትን እናገኛለን፡፡

  • ፩ ዲቃሎች /ዝርዋን/ የግእዝ ፊደላት ፪ ዲቃሎች /ዝርዋን/ የአማርኛ ፊደላት በመባል ይታወቃሉ፡፡

ከግእዝ ፊደላት ዝርዝር ጋር የሚሄዱትን የግእዝ ዝርዋን /ዲቃሎች/ ፊደላትን እንመለከታን፡፡

  • ዝርው ማለት ብትን /ቅደም ተከተልን ያልጠበቀ/ ማለት ነው፡፡

  • ዝርዋን የግእዝ ፊደላት ዝርዋን የሚል ስም የተሰጣቸው ከዋናዎቹ የግእዝ ፊደላት ላይ የተወሰነ ቅጥያ እየተጨመረ የተመሠረቱ ፊደላት በመሆናቸው ነው፡፡

  • ዝርዋን መባላቸው እንደ ዋንኞቹ የግእዝ ፊደላት ቅደም ተከተላቸውን ጠብቀው በሰባቱ የፊደላት ዝርዝር ባለመዘርዘራቸውና አብዛኛውን ጊዜ በግእዝ ፊደል በተጻፉ ጽሑፎች ላይ ብቻ መገኘታቸው ነው፡፡ እነዚህ ፊደላት የተመሠረቱት በዋንኞቹ የግእዝ ፊደላት ላይ የተወሰነ ቅጥያ በማድረግ ነው፡፡

  • ዋንኞቹ የግእዝ ፊደላት የአዘራዘር ሥልት በግእዝ ጀምረው በሳብዕ ቅደም ተከተላቸውን ጠብቀው ይዘረዘራሉ፡፡

ምሳሌ፡- ግእዝ      ካዕብ      ሣልስ         ራብዕ      ኀምስ    ሳድስ      ሳብዕ
       ሀ           ሁ          ሂ          ሃ          ሄ           ህ       ሆ    
       ለ           ሉ          ሊ         ላ          ሌ          ል       ሎ

 

የዝርዋን የግእዝ ፊደላት የአዘራዘር ሥልት ግን ከእነዚህ ይለያል

መነሻ ፊደላት

ግእዝ

ሳድስ

ሣልስ

ራብዕ

ኀምስ

 

የዛሬ አምዳችንን በዚህ እናጠናቅቃለን ሳምንት በአማርኛ ፊደላትና ዝርዋን የአማርኛ ፊደላትን የአጻጻፍና የአዘራዘር ሥልት ይዘንላችሁ እስከምንገናኝ ቸር ይግጠመን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 

ሰዋስወ ግእዝ (ክፍል ሁለት)

ሰኔ 19 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

 ፩.፪. የግእዝ ፊደላት አካፋፈል

መጀመሪያ ጊዜ ለሄኖስ በጸፍጸፈ ሰማይ (በሰማይ ገበታነት) የተገለጹለት ፊደላት አሁን በፊደል ገበታ ላይ በቅደም ተከተል እንደምናያቸው ሳይሆን ከዚህ በተለየ መልኩ ተዘበራርቀውና የእብራይስጡን የቋንቋ ስልት ይዘው ነው እነሱም አሌፋት በመባል የራሳቸው ስያሜ ነበራቸው

አ – አሌፍ                           ሐ – ሔት                            ሠ – ሣምኬት

በ – ቤት                            ጠ – ጤት                            ጸ – ጻዴ

ገ – ጋሜል                          የ – ዮድ                              ፈ – ፌ

ደ – ዳሌጥ                          ከ – ካፍ                              ዐ – ዔ

ሀ – ሄ                               ለ – ላሜድ                           ቀ – ቆፍ

ወ – ዋው                           መ – ሜም                           ተ – ታው

ዘ – ዛይ                             ነ – ኖን                                ረ – ሬስ

በማለት በእብራይስጡ አጠራር ይጠሯቸው ነበር፤ ነገር ግን እነዚህን የግእዝ ፊደላት በኢትዮጵያ ቀዳማዊ ጳጳስ በአቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን የግእዝ ፊደላትን አሻሽለው አሁን በፊደል ገበታ ላይ የምናያቸውን በቅደም ተከተል ከማስቀመጣቸው በፊት ያሉት ፊደላት፡-

 

ቀዳማዊ የግእዝ ፊደላት በሚል ስያሜ የሚጠሩ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ከሀ – ጀምሮ በዝርዝር በቀደም ተከተል የምናያቸው ፊደላት ደግሞ ደኀራዊ የግእዝ ፊደላት ብለን በሁለት እንመለከታቸዋለን፡፡

 

፩.፫. ቀዳማዊና ደኀራዊ የግእዝ ፊደላት፣-

፩. ቀዳማዊ የግእዝ ፊደላት የምንላቸው በአሁኑ ጊዜ በፊደል ገበታ ላይ አ፣ በ፣ ገ፣ ደ…./አቡጊዳ/ በማለት የምንጠራው የፊደል አቀማመጥ ነው እነዚህ ፊደላት በመነሻ ፊደል ብቻ ነበር የተጻፉት፡፡

 

                                      ቀዳማዊ የግእዝ ፊደላት

                                      

                                     

                                       

                                     

                                      

                                     

                                      

                                     

                   

በዚህ ዓይነት አቀማመጥ በነጠላ በግእዝ ፊደሉ ብቻ ነበር የተቀመጡት ከዚህ በኋላ ግን በእነዚህ ፊደላት ላይ የተወሰኑ ቅጥያዎችን በመጨመር በመጀመሪያ ደረጃ እነዚህን ፊደላት ወደ ሰባት የፊደላት አዘራዘር በመለወጥ ለእያንዳንዱ ፊደል የተለያዩ ቅርጽና ድምጽን በመፍጠር ፊደላቱ ወደ ሰባት ድምጽ /ሥልት/ ተለውጠው እንዲጻፉ በወቅቱ ከነበሩት ሊቃውንት አባቶች ጋር በመነጋገር የፊደላቱን ቅርጽ አዘጋጅተውልናል፡፡


 

 

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ሐምስ

ሳድስ

ሳብዕ

፲፩

፲፪

፲፫

፲፬

፲፭

፲፮

፲፯

፲፰

 

 

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ሐምስ

ሳድስ

ሳብዕ

፲፱

፳፩

፳፪

፳፫

፳፬

፳፭

፳፮

 

ደሐራዊ የግእዝ (የኢትዮጵያ) ፊደላት አጻጻፍ

 

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ሐምስ

ሳድስ

ሳብዕ

፲፩

፲፪

፲፫

፲፬

፲፭

፲፮

፲፯

፲፰

፲፱

፳፩

፳፪

፳፫

፳፬

፳፭

፳፮

 

የግእዝ ቋንቋ እንደ ሌሎች ቋንቋዎች እራሱን የቻለ ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ የሚነገር ጥንታዊ ቋንቋ ነው፡፡ አንድን ቋንቋ እንደ ቋንቋ ከሚያስቆጥሩት መሠረታዊ ነገሮች አንዱ እና ዋንኛው የራሱ የሆኑ ፊደላት ሲኖሩት እና የራሱን የአነጋገር ሥርዓት ተከትሎ መሄድ ሲችል ነው፡፡ ይህም በመሆኑ በዛሬ አምዳችን ስለ ግእዝ ቋንቋ ፊደላት ብዛትና የፊደላቱንም ስያሜ ትርጒም እንመለከታለን፡፡

  1. የግእዝ ፊደላት አጠቃላይ ብዛት ፳፮ (26) ነው፡፡
  2. የግእዝ ፊደላት በሰባት የአዘራዘር ስልት ይዘረዘራሉ፡፡
  3. የግእዝ ፊደላት ብዛት ከነ አዘራዘራቸው ፻፹፪ (182) ናቸው፡፡
  4. ይህም ማለት እየአንዳንዱ ፊደል በሰባት ሥልት ስለሚዘረዘር ነው፡፡

ምሳሌ. ሀ. ግእዝ ሁ. ካዕብ ሂ. ሣልስ ሃ. ራብዕ ሄ.ሐምስ ህ.ሣድስ ሆ. ሣብእ ከፊደል ሀ እስከ ፐ ያሉት ፊደላት በዚህ ዓይነት መንገድ ይዘረዘራሉ፡፡

 

በፊደል ገበታ ላይ የምናገኛቸው የፊደላት ብዛት አጠቃላይ ፴፫ (33) ሲሆኑ ቀሪዎቹ ፯ (ሰባት) ፊደላት የአማርኛ ፊደላት በመባል ይጠራሉ፡፡ እነዚህን ፊደላት ከነ አዘራዘራቸው በሌላ ጊዜ እናያቸዋለን፡፡ ለዛሬ ፳፮ (26)ቱን የግእዝ ፊደላት በቅደም ተከተል ከነትርጒማቸው እንመለከታለን፡፡

 ፩.   ሀ- ብሂል ሀልዎቱ ለአብ እም ቅድመ ዓለም፡፡

   ሀ- ማለት የአብ አኗኗሩ ከዓለም በፊት ነው፡፡

  ፪.  ለ- ብሂል- ለብሰ ሥጋ እምድንግል፡፡

   ለ. ማለት- ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ሥጋን ለበሰ፡፡

  ፫. ሐ. ብሂል ሐመ ወሞተ ወተቀብረ፡፡

  ሐ.ማለት ክርስቶስ ታመመ፣ ሞተ፣ ተቀበረ፡፡

  ፬.  መ. ብሂል መንክር ግብሩ ለእግዚአብሔር፡፡

   መ-ማለት የእግዚአብሔር ሥራው ድንቅ ነው

  ፭. ሠ- ብሂል ሠረቀ በሥጋ፡፡

    ሠ- ማለት ጌታ በሥጋ ተወለደ (ተገለጠ)፡፡

  ፮.  ረ- ብሂል ረግዓት ምድር በቃሉ፡፡

   ረ- ማለት ምድር በቃሉ ረጋች (ጸናች)፡፡

  ፯.  ሰ- ብሂል ሰብአ ኮነ እግዚእነ፡፡

    ሰ- ማለት ጌታችን ሰው ሆነ፡፡

    ፰. ቀ- ብሂል ቀዳሚሁ ቃል፡፡

   ቀ- ማለት በመጀመሪያ ቃል ነበር፡፡

   ፱.…….    በ- ብሂል በትኅትናሁ ወረደ እግዚእነ፡፡

   በ- ማለት ጌታችን በትሕትናው ወደኛ ወረደ (ተወለደ)፡፡

        ፲.  ተ- ብሂል ተሰብአ ወተሰገወ፡፡

        ተ- ማለት ጌታችን ሰው ሆነ፡፡

        ፲፩ . ኀ- ብሂል ኀያል እግዚአብሔር፡፡

        ኀ- ማለት እግዚአብሔር ኀያል ነው፡፡

        ፲፪.  ነ- ብሂል ነሥአ ደዌነ ወፆረ ሕማመነ፡፡

 ነ- ማለት ጌታችን ደዌያችንን ያዘልን ሕመማችንን ተሸከመልን

        ፲፫.  አ- ብሂል አአኲቶ ወእሴብሖ ለእግዚአበሔር አቀድም (አእኲቶቶ ለእግዚአብሔር)

                    አ- ማለት እግዚአብሔርን በፍጹም ልቤ አመሰግነዋለሁ (እግዚአብሔርን ማመስገንን አስቀድማለሁ)፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 

ይቆየን

ሰዋስወ ግእዝ

ሰኔ 13 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በቅድሚያ በሕያውና ዘለዓለማዊ በሆነ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታዬን እያቀረብኩ ስለ ግእዝ ቋንቋ አጠር ባለ መልኩ እገልጻለሁ፡፡

የግእዝ ቋንቋ ቀዳማዊነት

ቋንቋ ማለት መግባቢያ መተዋወቂያ መነጋገሪያ አሳብ ለአሳብ መገላለጫ ወዘተ…… ማለት ነው፡፡ ሕዝብ ባለበት ቦታ ሁሉ ቋንቋ አለ፤ ቋንቋም ባለበት ቦታ ሕዝብ አለ፤ ያለ ሕዝብ ቋንቋ ያለ ቋንቋ ሕዝብ ሊኖር አይችልም፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ ስለ ግእዝ ቋንቋ አመጣጥ አጠር ባለ መልኩ ስንነጋገር፡-

ከአንዳንድ ቀደምት የታሪክ ጸሐፊዎችና የግእዝ ቋንቋ መጻሕፍትን ጽፈው ካስረከቡን ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶችና የቋንቋው ባለቤቶች እንደምንረዳው፡- የግእዝ ቋንቋ አመጣጥ በኢትዮጵያ መነሻ ሊሆነን የሚችለው ከስምንተኛው ምዕተ ዓመት ቅድመ ልደት ክርስቶስ ጀምሮ ነገደ ሴም /የሴም ዘሮች/ወገኖች/ ቋንቋቸውን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ሴማዊ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ቋንቋ ሆነ፡፡ ነገደ ሴም ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት ቋንቋቸውን በመግባቢያነት አሳድገው፣ ሥነ ጽሑፋቸውን አስፋፍተው፣ በባቢሎን በአካድና፣ በአሶር ይኖሩ ነበር፡፡ በኋላ ግን ለሁለት ተከፍለው ግማሾቹ ሴማውያን ሰሜንና ምስራቅ እስያን፣ ግማሾቹ ሴማውያን ደግሞ ደቡቡ እስያን ይዘው ይኖሩ ነበር፡፡

የሰሜን እስያ ሴማውያን ቋንቋ /የአካድ ቋንቋ/ አማራይክ፣ ዕብራይስጥንና ፊንቄን ሲያስገኝ የደቡብ እስያ ሴማውያን ቋንቋም /አካድ ቋንቋ/ ሳባን ግእዝንና የተለያዩ በኢትዮጵያ ውስጥ በመግባቢያነት የምንጠቀምባቸውን ሴማውያን ቋንቋዎች አስግኝቷል፡፡ በደቡብ እስያ ይኖሩ የነበሩ ነገደ ሴም በተለያየ ምክንያት እየፈለሱ ወደ ደቡብ ዐረብ፣ ወደ የመንና ወደ አካባቢዋ መጥተዋል ከዝያም ፈልሰው ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በአክሱምና በአካባቢዋ ሰፍረው ይዘዋቸው ከመጡት ቋንቋዎቻቸው መካከል በታሪክ ጎልተው የሚታወቁና አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩትና በአሁኑ ሰዓትም በአገልግሎት ላይ የሚገኙት ቋንቋዎች የሳባ እና የግእዝ ቋንቋዎች ናቸው፡፡

ነገደ ሴም /ሴማውያን/ ቋንቋዎቻቸውን /ሳባና ግእዝን/ ከነገደ ካም ቋንቋ ጋር አስማምተው በመያዝ ሁሉንም ቋንቋዎች ሲናገሩዋቸው ኖረው ነበር፡፡ በኋላ ግን ሳባና ግእዝ እየተለመዱና እየተስፋፉ እየዳበሩም ከመሄዳቸው የተነሣ የነገደ ካምን ቋንቋ እየዋጡት መጥተው ሁለቱ ሳባ እና ግእዝ ቋንቋዎች ብቻ ሀገራዊ ቋንቋዎች ይሆኑ ጀመር እየቆዩ ግን ሁለቱ /ሳባና ግእዝ/ በጣም ተመሳሳይና ተቀራራቢ በመሆናቸው እንደ አንድ ቋንቋ ሆነው ይነገሩ ጀመር፡፡ ይኸም ጽሑፉ /ፊደሉ/ በሳባ እንዲጻፍ እና መነጋገሪያ ቋንቋውን ደግሞ በግእዝ እንዲሆን በመደረጉ ነው፡፡ ነገደ ሴም በሳባ ቋንቋቸው ሳባውያን፣ በግእዝ ቋንቋቸው ደግሞ አግአዝያን ተብለው የሚጠሩት ከዚህ መነሻነት ነበር፡፡

ለዚህም መረጃ የሚሆኑን ሳባና ግእዝ ቋንቋዎች ተጽፈውባቸው የሚገኙት ጥንታውያን የኢትዮጵያ ቅርሶች እንደ የአክሱምና የላሊበላ ሐውልቶች በየሐ እና በአዱልስ ወዘተ….. የተለያዩ በድንጋይ ላይ የተቀረጹ ጽሑፎችና ቅርጻ ቅርጾች እስከ አሁን ቆመው የሚገኙ የዚህ ቋሚና ግልጽ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ የሳባና የግእዝ ቋንቋዎች በዚህ ሁኔታ እስከ 324 /፫፻፳ወ፬/ዓ.ም. አካባቢ ድረስ አብረው ሲነገሩ ቆይተዋል በኋላ ግን የሳባ ንቋ እየተዳከመና በግእዝ ቋንቋ እየተዋጠ ይሄድ ጀመር እንደ ምንም እየተንገዳገደ እስከ 350 /፫፻፶/ ዓ.ም. ቆይቶ ከዚህ በኋላ ከሥነ – ጽሑፍ ከመነጋገሪያነትም ፈጽሞ ቀረ የግእዝ ቋንቋ ግን ከ324 /፫፻፳ወ፬/ዓ.ም. ጀምሮ ብቸኛ ሀገራዊ ቋንቋ በመሆን እስከ ፲፪ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም የአማርኛ ቋንቋ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ ሲያገለግል እንደ ነበር የታሪክ ጸሐፊዎች በግልጽ አስቀምጠውታል፡፡
፩.፪. የግእዝ ፊደላት አመጣጥ

ስለ ግእዝ ቋንቋ ስንነጋገር በመጀመሪያ ለማንኛውም ቋንቋ መሠረት ስለሚሆነው ስለ ፊደል አመጣጥ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ ስለ ፊደል አመጣጥ ሊቃውንት ብዙ ትንታኔ ይሰጡበታል ይኸውም ፊደል ማለት ጽሑፍ ነው ምክንያቱም “ፈደለ” ጻፈ ከሚለው ከግእዝ ቃል የወጣ ነው ይላሉ፡፡ ይሁን እንጂ “ፈደለ” የሚለውም ቃል የሦስት ፊደላት ጥምረት በመሆኑ እነዚህ ፊደላት ከየት እንደመጡ መነሻቸውን /ምንጫቸውን/ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡

እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት ለዚህ በቂ የሆነ መረጃ እናገኛለን፡፡ የፊደል ስልት አንድም ቅርጽ የተጀመረው የአዳም ሦስተኛ ትውልድ በሆነው በነቢዩ በሄኖስ ዘመን ነው፡፡ ነቢዩ እግዚአብሔርን በማገልገል የታወቀ ደግ ስለ ነበር ለደግነቱ መታወቂያ /መታሰቢያ/ ይሆነው ዘንድ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሕግ ማሰሪያ የሚሆነውን ፊደል በጸፍጸፈ ሰማይ /በሰማይ ገበታነት/ ተገልጦ ታይቶታል፡፡

ስለዚህ የፊደል ቅርጽ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ለሥነ-ጽሑፍ በር መክፈቻ በማድረግ ተጠቅመውበታል፡፡ መጠሪያ ስሙንም ጽሑፍ ለማለት ፊደል ብለውታል፡፡ ይኸስ እውነትነቱ ምን ያህል ያገለግላል ቢሉ በዚያን ጊዜም በጸፍጸፍ ሰማይ ታየ የሚባለው ፊደል የእብራይስጥ ፊደል እኛ አሁን አሌፉት እያልን የምንጠራው ነው፡፡

ስለዚህ ይህ ፊደል ከፊደልነት ጥቅሙ ጋር እንደ ኅቡዕ ስም ይገመታል /ይታመናል/ ምክንያቱም የእያንዳንዱ ፊደል ትርጒም ከእግዚአብሔር ህልውና እና እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ካደረጋቸው የቸርነት ሥራዎች ጋር የተዛመደ ትርጒም ስለሚሰጥ (ስለአለው) ነው፡፡ ይህ እውነታ እና የስም አጠራር ትርጒም ግን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት አባቶች የፊደላት ትርጒም አሰጣጥ ላይ በግልጽ ተጽፎ የሚገኝ ነው /ጥንታዊ የኢትዮጵያ ትምህርት በሊቀ ሥልጣናት ሀብተ ማርያም ወርቅነህ/ በተጻፈው መጽሐፍ በግልጽ እንረዳዋለን ይህን መነሻ በማድረግ የሥነ-ጽሑፋችን በር መክፈቻ የአሌፋቶችን ስም ፊደል የሚል ስያሜ በመስጠት እንጠቀምበታለን፡- ስለዚህ ማንኛውንም ነገር ለመጻፍ ለመጪውም ትውልድ ለማስተላለፍ በጽሑፍ መቀረጽ ስላለበትና ራሱ ፊደሉ የሥነ-ጽሑፍ መጀመሪያ ስለሆነ ጽሑፍ ለማለት ፊደል ተብሎ ተጠርቷል፡፡

ለዚህም የቤተ ክርስቲያን  አባቶች ሊቃውንት አጽንዖት ሰጥተው ሲያስቀምጡት “ዘእንበለ ፊደል ኢይትነገር ወንጌል” ይላሉ ይህ ማለት ወንጌል ሳይቀር የሚጻፈው /የሚተረጎመው/ በፊደል አማካኝነት ነው፡፡ ከዚህም ሌላ ስለ ፈደል ጠቃሚነት የሚሰጡትን ሐተታዎች ከብዙ በጥቂቱ እንመልከት፡-

፩. ፊደል- ብሒል ነቅዓ ጥበብ ውእቱ፡፡

ፊደል የአእምሮ መገመቻ የምሥጢር መመልከቻ ነው ምክንያቱም ያለ ፊደል ምንም አይታወቅምና ፡፡

፪. ፊደል – ብሂል ነቅዓ ጥበብ ውእቱ፡፡

ፊደል የጥበብ ሁሉ መገኛ ምንጭ ነው፡፡

፫. ፊደል – ብሂል መራሔ ዕውር ውእቱ፡፡

ፊደል የእውር መሪ ነው፤ ምክንያቱም ሰውን ሁሉ ከድንቂርና አውጥቶ ወደ ብርሃን ይመራልና፡፡

፬. ፊደል – ብሂል ጸያሔ ፍኖት ውእቱ፡፡

ፊደል ማለት መንገድ ጠራጊ ነው፤ ምክንያቱም አላዋቂነትን /ድንቁርናን/ ከሰው ልጅ ጠርጎ /አጽድቶ/ ከፍጹም ዕውቀት ያደርሳልና፡፡

፭. ፊደል ብሂል -ርእሰ መጻሕፍት ውእቱ፡፡

ፊደል ማለት የመጻሕፍት ሁሉ ራስ /አናት/ ነው ምክንያቱም ያለ ፊደል ምንም ነገር መጻፍ አይቻልምና፤ /ኢተወልደ መጽሐፍ ዘእንበሌሁ ለፊደል/ ያለ ፊደል ምንም ነገር ሊጻፍ አይቻልምና

የግእዝ ቋንቋ ከሴማውያን ፊደሎች መካከል አንዱና ዋናው ጥንታዊ ቋንቋ ስለሆነ፣ የራሱ የሆነ ብዙ ቃላትን ከነፍቺዎቻቸው ይዞ ይገኛል፡፡ ከዚህ አንጻር ፊደል የማንኛውም ጽሑፍ መነሻ ስለሆነ፣ ጽሑፍ ብሎ ለመጥራት መጠሪያውን ፊደል ብለውታል፡፡ በአጠቃላይ ቋንቋ እንደ ማንኛውም ቋንቋ የራሱ የሆነ የአጻጻፍን ሥልትና ቅርጽ የተከተለ ጥንታዊና መሠረታዊ ቋንቋ ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 

ይቆየን

ግእዝ ከእስያ ልሳናት ጋር ሲነጻጸር

በዓለም የሥነ ልሳን ጥናት መሠረት የአካድ /የአሦር – አካዳውያን/ ቋንቋ ጥንታዊ ማንነቱ የተረጋገጠው በአንዳንድ የሥነ ጽሑፎች ቅሪት ሲሆን ይህ ቋንቋ በሥነ ልሳን ተማራማሪዎች ዘንድ የምሥራቅ ሴማዊ ልሳን ተብሎ በቅርብ ጊዜ ከተገኘው ከኤብላዊ ቋንቋ ጋር የሚመደብ ነው፡፡ አካድ እና አሦር በመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በኦሪት ዘፍጥረት የተገለጹ እና ከኖኅ ዘመን በኋላ የታወቁ መካናተ ሥልጣኔ ናቸው፡፡ በሥነ ጽሑፍ መረጃ የአከድ ልሳን 2500 ቅ.ል.ክ. እንደነበረ ይናገራል፡፡ በኋላ በአራም የአራማውያን የተባለው ቋንቋው ራሱን የገለጸበት ጊዜ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በሥነ ቅሬተ ምድርም ሆነ በሥነ ልሳን ተመራማሪዎች ዘንድ አካድ የኢኮኖሚ፣ የሕግ የአስተዳደር፣ የታሪክና የሥነ ጽሑፍ መረጃዎች እንደነበረው የተረዳ ነው፡፡


    
የካምም ልጆች ኩሽ፣ ምጽ/ስ/ ራይም፣ ፋጥ፣ ከነዓን ናቸው፡፡ የኩሽም ልጆች ሳባ፣ ኤውላጥ፣ ሰብታ፣ ሬጌም፣ ሰበቅታ ናቸው፡፡ የሬጌም ልጆችም ሳባ፣ ድዳን ናቸው፡፡ ኩሽም ናምሩድን ወለደ፣ እርሱም በምድር ላይ ኃያል መሆን ጀመረ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ ነበረ፤ ስለዚህም በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ እንደናምሩድ ተባለ፡፡ የግዛቱም መጀመሪያ በሰናኦር አገር በባቢሎን አሬክን አርካድ ሌድን ናቸው፡፡ አሦርም ከዚያች አገር ወጣ፡፡ ነነዌን የረሆቦት የተባለችውን ከተማ ካለህን በነነዌና በካለህ መካከልም ሬሴንን ሠራ፡፡ እርስዋም ታላቂቱ ከተማ ናት ምጽራይምም ሉዲምን ኢኒሜቲምን ላህቢምን ነፍታሌምን ጳጥሮሰኒምን ከእነርሱ የፍልስጥኤም ሰዎች የወጡባቸውን ከሳሎሂምን ቀፍቶሪምንም ወለደ፡፡ ዘፍ. 10፡6-14

 

አፍሪካዊያንም በየዘመናቱ የሥልጣኔ ማእከሉን በወንዞች ጤግሮሰ እና ኤፍራጥስ ዳር እንደ መሠረቱ ፤ አካዳውያን ፈለገ ግዮንን የራሱን ለአፍሪካውያን ሕዝቦች የሥልጣኔ መሠረት አድርጎ መቆየቱ የሚታወስ ታሪክ ነው፡፡ አፍሪካውያን በራሳቸው ፊደል ቢጠቀሙም በተለያዩ የዓለም ዐቀፍ ተጽዕኖዎች ሥር በመውደቃቸው መሠረታዊውን ፊደል ጽሕፈታቸውንና ቋንቋቸውን ሊያጡ ችለዋል፡፡ ይህንን ፊደል ጠብቃ የተገኘችው ኢትዮጵያ ናት፡፡ የኢትዮጵያ ፊደልና ቋንቋም በሥነ ጽሑፍ መረጃነት ለዓለም ከቀረቡት ልሳናት የሚታወቅባቸው ባሕርያት ሲኖሩት ከጠፋው ከአካድ ቋንቋ ይብልጥ በሥነ ጽሑፍ መረጃነቱ ራሱን ያሳደገ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህንም በቋንቋው ጠባያት ከአካድ ጋር ቢመሳሰል በራሱ ደግሞ ከአፍሮ እስያ ከቋንቋ መለየት ይህ ሴማዊና ካማዊ ብሎ ለመጠቅለል የሚያስቸግር ቢሆንም በቋንቋ ጥናት ዋና የመለያ ፍጥረት በማጥናት መመደብ የሚቻል ይሆናል፡፡ ከዚህ አንጻር ግእዝን ሴማዊ፣ ደቡብ ሴማዊ፣ ሰሜን ሴማዊ /በኢትዮጵያ/ አድርገው የሚከፋፍሉበት፡-

 

– ልዩ ልዩ አስማተ መካናት መመሳሰል ምሳሌ- ሳባ
– የቋንቋዎቹ የራሳቸው መመሳሰል
– የሥነ ቅርጽ መመሳሰል ወዘተ ሲሆን ግእዝ ከነዚህ ቋንቋዎች መደብ የሚለዩት ጠባያት አልነበሩትም፡፡ ወይም ደግሞ በእነዚህ ቋንቋዎች የተዘነጉ ጽሑፎች በግዕዝ ግን አልነበሩም ማለት አይቻልም፡፡ ለአብነትም ያህል «ተስዐቱ» የሚለው የጥንት ሥርው ምን ይመስላል የሚለው ሲጠና ከአረማይክ ይልቅ የግእዝ «ታስዕ» የሚለው ቃል ቀዳሚነት ጥንታዊነት ይኖረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት አረማይክ ያጣውን ግእዙ በመጠበቅ እንዴት አረማይኩ ለግእዝ በዘመኑ ያጣን ቃል ሊያቀብለው ቻለ የሚል ጥያቄ አስነሥቷል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ግእዝ በድምጸ ንባቡ የለሌሎች የአፍሪካ ልሳናት እና የሩቅ ምሥራቅ ልሳናት የሚታወቁበትን የድምፀት ንበት በመያዝ ከአፍሪካ ልሳናት ጋር ሊያመሳስለው ይችላል፡፡


 
ምሳሌ፡

                ቀዳማይ     –     ካልአይ

አካድያን  –     ያቅቱል       –     ያቀትል
ዐረበኛ    –     ቀተለ         –     ያቀቱል
ግእዝ     –     ቀተለ         –     ይቀትል
   

ማስታወሻ- አካድያን ያቅትል ሲል በ «ይ»እና በ «ቅ» መካከል አናባቢ«አ»ኔ ሲጨምር ግእዙ ግን አይጨምርም፡፡ በተጨማሪም በግእዝ ቋንቋ በቀዳማይ አንቀጽ ዝርዝር ጊዜ የአገናዛቢ ቅጥያዎችን የምንጨምር ሲሆን አካድያን ግን የሰማዊነት ባሕርይን የሚያሳይ ነው፡፡

 
ቀዳማይ፡-
ግእዝ – አካድያን
አነ – ቀተልኩ – አቅቱል
አንተ – ቀተልከ – ተቅቱል
አንቲ – ቀተልኪ – ተቀቱሊ
አንትሙ – ቀተልክሙ – ተቅቱላ
አንትን – ቀተልክን – ተቅቱላ
ንሕነ – ቀተልነ – ኒቀቱላ
ውእቱ – ቀተለ – ተቅቱል
ይእቲ – ቀተለት – ኢቅቱል
ውእቶሙ – ቀተሉ – ኢቅቱሉ
ውእቶን – ቀተላ – ኢቅቱላ
ለካልአይ – ግእዝ – አካድያን
አነ – እቀትል – አቀትል
አንተ – ትቀትል – ተቀተል
አንትሙ – ትቀትሉ – ተቀተላ
አንትን ትቀትላ – ተቀተላ
ንሕነ – ንቀትል – ኒቀተላ
ውእቱ – ይቀትል – ኢቀተላ
ይእቲ – ትቀትል – ተቀተላ
ውእቶሙ – ይቀትሉ – ኢቀተሉ
ውእቶን – ይቀትላ – አቀተላ
አንቲ – ትቀትሊ – ተቀተሊ
 

ጥንታዊ ቃላትን እየወሰዱ ቋንቋን በአንድ መመደብ የሚቻል ነው፡፡ ጥንታዊ አናባቢ /ኧ/ ከአካድያን ይልቅ በግእዝ መጠበቁ ግእዝን ልዩ ያደርገዋል፡፡ አካድያን እና ግእዝ በካልአይ የመጥበቅ ድምጽ ሲኖራቸው ጥንታዊ የደቡብ ዐረብ ልሳን ግን የሌለው በመሆኑ ግእዝን እንዴት ከሌላው ቋንቋ ከሳባ መጣ እንላለን? በተጨማሪ የግእዝን ከሌሎች ከሚመስላቸው ከማዕከላዊው ምሥራቅ ሀገራት ቋንቋዎች ስናገናኘው የጥንታዊ የቋንቋ ባሕርይ ቅርጽና ድምጽ መያዙን የምናገኝባቸው ቃላት እንጠቀማለን፡፡

 
ጥንታዊ ቃል – የአካድ – ዐረበኛ – ዕብራይስጥ – የሦርያ – ግእዝ
አብ «-»    አብ –         አብ –     አብ –         አባ –   አብ
ልበ – ልብ – ሉብ /ጥ/ – ሌይብ /ጥ/ – ሌባ – ልብ
ቤት /በይት – ቢቱ – በይት – ባይ /ቤት – በይት /ታ – ቤት
ደም- – – ደም – ዳም – ድማ – ደም
ዐይን – ዓን – ዐይን – ዐዪን – ዐይ-ና – ዐይን
ወይን – – – ወይን – ያዪን – – – ወይን
ወዘተ. . .
ይ – – – /ይ/ አልቦ ዪ – ይ

አይቴ ብሔሩ ለግእዝ?

 

ግእዝ የማን ቋንቋ ነው? የካም ወይስ የሴም ቋንቋ የሚለው የብዙዎች ምሁራን ጥናት እና ጥያቄ እየሆነ መጥቷል፡፡ ግእዝን የሴም የሚያደርጉት የሶቢየት ምሁራን ኤቢ ዶጎልስኪ /A.B. Dogopolsky/ እና ኢጎር ዲያኮኖፍት /Igor Diaknoft/ ግእዝ የደቡብ ሴማዊ ልሳን ሳይሆን በዐረብ ምድር የመጀመሪያዎቹ የአፍሪካውያን ወይም የኩሻውያን ቋንቋ ነው ይላሉ፡፡

 

የዚህን ወገን ሐሳብ የሚጋሩት ደግሞ ቸክ አንተ ዲዮፕ /Cheik Anta Diop1919/ «ተርሰሃሌ» ጥበቡ፣ «አቤንጃ»፣ ኃይሉ ሀብቱ /1987/፣ አስረስ የኔሰው፣ ሺናይደር /1976/ እና አየለ በክሪ/1997/ ወዘተ ናቸው፡፡ ለዚህ ከሚጠቀሱት ምክንያቶች ዋና ዋናዎቹ ከአፍሮ እስያ ቋንቋዎች ብዙዎቹ የሚገኙት በኢትዮጵያ ነው የሚል ሲሆን በተጨማሪም በጣም ብዙ ቋንቋዎች በተለያዩ ቡድኖች በተቀራረበ እና በተወሰነ መልከዓ ምድር ስለሚነገሩ ነው፡፡

 

መርቶኔን /A.Murtonen/ ግእዝን ሴማዊ /ከኢትዮጵያ የወጣ/ ቋንቋ ነው የሚል አቋም አላቸው፡፡ ሊኦኔል ቤኤንደርም በተመሳሳይ ሁኔታ፡፡ ከዚህም አልፈው ግእዝን የአዳም ቋንቋ፤ የመላዕክት ቋንቋ የሚሉት አልጠፋም፡፡ ምንም እንኳን የካም ወይም የሴም ብለው ቢከፍሉትም፡፡ ተጠቃሾቹም ሲዲ ጳውሎስና አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ናቸው፡፡

 

«ሴማዊ ነው»፡፡ የሚለውን ሐሳብ ቢቀበሉትም የግእዝ ተናጋሪዎቹ እነማን እንደነበሩ አላውቅም የሚሉት ጌታቸው ኃይሌ ናቸው፡፡

 

በአንጻሩ ካም ወይም ሴም የሚለውን ቃል ከቋንቋ ጋር በማገናኘት የተጠቀመበት የጀርመን መልእክተኛ ጆህን ሊዊድግከፈ /Johunn Luowigkapf1810-1881/ ነው፡፡ ከርል ፍሬድሪክ ሌፐሲየስ /Karl Freidrich Lepsius/ ካምን ሴማዊ አይደለም ይላል፡፡ ከቋንቋ ጥናት በመነሳት ነው ይህን ሊል የቻለው፡፡ ይሁን እንጂ በአሁኑ ሰዓት ያለው የሥነ ልሳን ጥናት ከሐረገ ዘር ይልቅ መልክዐ ምድራዊ በመሆኑ የካምጠሴም ቋንቋ መባሉ ቀርቶ በአፍሮ እስያነት ውስጥ በአጠቃላይ የሚታይ ነው ይላል ዮሴፍ ግሪን በርገ /Joseph Green berg/፡፡ የዮሴፍ ግሪን በርገ /Joseph Green berg/ ሐሳብ የዚህን ጽሑፍ አቅራቢ ሐሳብ የተስማማ ነው፡፡

 

የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ካለው ግንዛቤ የተነሣ የኢትዮጵያን ቋንቋ ግእዝን አፍሪካዊ የኢትዮጵያ ልሳን ውልደቱን እና እድገቱን ኢትዮጵያ አድርጎ በዘመነ ባቢሎን ሊነገር የሚችል ዓለም ዓቀፋዊና ጥንታዊ ልሳን ነው ብሎ ያምናል፡፡ የግእዝ የመጀመሪያ ጽሑፍ በ500 ቅ.ል.ክ የተጻፈ ሲሆን በአናባቢ መጻፍ የተጀመረው ግን በ4ኛው መቶ ዓ.ም ነው፡፡ ይህንንም በተከታይዮች አርእስተ ነገር ላይ ለማሳየት እንሞክራለን፡፡

የግእዝ ቋንቋ ፡ –

ሀ. የጽሕፈት ዘዴ አቡጊዳ
ለ. የጽሕፈት አቅጣጫ ከግራ ወደ ቀኝ አግድም /ከሳባ የሚለይበት ነው/
ሐ. እያንዳንዱ ፊደል በአናባቢ የተገለጸ እና አናባቢ የሌለው ሆኖ ሊጻፍ የሚችል ዓለማቀፋዊና ጥንታዊ ልሳን ነው ብሎ ያምናል፡፡
   

3 የግእዝ ቋንቋ ፊደላትና ትርጉም፡-
    

የግእዝ ቋንቋ ፊደላት የራሳቸው መለያ ትርጉም ሥዕላዊ መገለጫ ያላቸውና ከጥንት ጀምሮ ከጥቅም ላይ የዋሉ መሆናቸውን ያስረዳሉ፡፡ የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ድምጾችን ሳይለቅ ከዘመን ዘመን በሚደረገው የሥነ ጽሕፈት ልውጠትም አዳዲስ ፊደላትን ለመፍጠር ያስቻሉ ፊደላትን ይዟል፡፡ እነዚህ ፊደላትም ለአፍሪካ እንደመሠረትነት ያገለገሉ ከመሆናቸውም በላይ ለአሁኑ የሥነ ጽሑፍ ሀብታችን መሠረቶች ናቸው፡፡ ፊደላቱ በአናባቢ ተዋሕደው ቃላትን ሊወልዱ ቋንቋን ሊያበለጽጉ ችለዋል፡፡ የራሳቸው የሆነ ቅርጽ እና ፍቺም ያልተለያቸው ናቸው፡፡

ነዛሪ የጉሮሮ እግድ – አ – አሌፍ አልፍ አብ
ነዛሪ የከናፍር ፈንጂ – በ – ቤት ባዕል
ነዛሪ የትናጋ ፈንጂ – ገ – ጋሜል ገምል
ነዛሪ የጥርስ ፈንጂ – ደ – ዳሌጥ ዳ/ን/ልት
ነዛሪ የጉሮሮ ፍትግ – ሀ – ሆይ ሆይ ሀወይ
 
የከናፍር ትናጋ ደኃራይ – ወ – ዋው ዋዌ ዋሕድ
ነዛሪ የጥርስ ፍትግ – ዘ – ዘይ ዛይ
ኢነዛሪ የማንቁርት ፍትግ – ሐ – ሔት ሐወት ሕያው ሕይወት
ነዛሪ የትናጋ ፍትግ – ኀ – ኀርም ኄር
ኅዩል ኢነዛሪ የጥርስ ፈንጂ – ጠ – ጤት ጠይት ጠቢብ
ቅሩብ የከናፍር ትናጋ ደኃራይ – የ – ዮድ የማን
ኢነዛሪ የትናጋ ፈንጂ – ከ – ከፍ ከሃሊ
ጎናዊ – ለ – ላሜድ ለዊ ልዑል
ከናፍራዊ ወአንፋዊ – መ – ሜም ማይ ምዑዝ
የጥርስ ወአንፋዊ – ነ – ኖን ነሐስ ንጉሥ
ኢነዛሪ የጥርስ ፍትግ – ሠ – ሣምኬት ሣውት
ነዛሪ የማንቁርት ፍትግ – ዐ – ዐይን ዐቢይ
ኢነዛሪ የከንፈር ፈንጂ – ፈ – ፈፍ ፈቁር
ኀዩል ኢነዛሪ የጥርስ ፍትግ  – ጸ – ጻዴ ጸደቅ ጻድቅ
ፀ – ፀጰ

ኀዩል ኢነዛሪ የትናጋ ፈንጂ – ቀ – ቆፍ ቅዱስ
የድድ ተርገብጋቢ – ረ – ሬስ ራእስ
ኀዩል ኢነዛሪ የጥርስ ፈንጂ – ሰ – ሳን ስቡሕ
ኢነዛሪ የጥርስ ፈንጂ – ተ – ታው ተዊ ትጉህ
ነዛሪ የከንፈር ፈንጂ – ጰ – ጰይት ጴት
ኢነዛሪ የከንፈር ፈንጂ – ፐ – ፐ ፌ
    

ከላይ እንዳየነው የግእዝ ፊደላት ቢሆኑም ቋንቋ ምንጊዜም በለውጥ ስለሚሄድ ስለሚወልድ እና ስለሚረባ ሌሎች ልዩ ልዩ ድምጾችን እንደፈጠረ እንረዳለን፡፡ ለዚህም የ «ሰ»ን ድምጽ የመሰለ «ሠ» የ«በ»ን ድምጽ የመሰለ ፐ እና ጰ ሌሎችም በየዘመናቱ ሲፈጠሩ ከመግባቢያነት አልፈው በሥነ ጽሑፍ ደረጃ ታሪክን አስቀምጠዋል፡፡ በተለይም ዛሬ የማይነገሩ «ደ»ን የመሰለ ደ፣ ዘ የጠበቁ.. ወዘተ በየዘመናቱ እንደነበሩ የሥነ ልሳን ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ የግእዝ ፊደላት ትርጉም እና ሃይማኖታዊ ምስጢ ብቻ ሳይሆን ሥዕላዊ መገለጫዎች እንደነበሩት መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ ፊደላቱም በሥዕልነት ብቻ ሳይሆን መሠረተ አኀዝ መሆናቸውንም እንመለከታለን፡፡ ምሳሌ አ አልፋ ሲባል የበሬ ቀንድ እንደሚመስል አልፋም በላሕም ተተክቶ በመ.ቅ ይገኛል፡፡ ምሳሌ፡- አባግዐኒ ወኩሎ አልሕምተ ሲል መዝ. 8.7 በዕብራይስጥ ጾጊ ወአላፊም ይላል /ኪ.ክ/፡፡ ጥናት እንደሚያመለክተውም ላሕም ልሔም /እንጀራ/ ከእብራይስጥ ቃል የተወሰደ እና ከአላፊም ቦታ የገባ መሆኑን የሚጠቁም የሥነ ጹሑፍ መረጃ ይገኛል፡፡ ጋሜል ገመል /አባ ገሪማ የሚገኝ ወንጌል እንደ ሚያስረዳው/፡፡ ከፍ የሚለው ቃልም በትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 1.7 እግሮቻቸው ከፍ ያሉ እግሮች ነበሩ የእግራቸውም ኮቴ እንደ ጥጃ ኮቴ ነበር ሲል ጥጃ ከፍ መሆኑን ያመለክታል፡፡ በተጨማሪም ዮድ በቀኝ እጅ፣ ነ በእባብ፣ መ በውኀ ሞገድ፣ ዐ በዐይን፣ ፈ በአፍ፣ ረ በራስ፣ ተ በመስቀል፣ በ በቤት… መመሰላቸው ፈጣሪ ለሰው ልጅ ራሱን በሚታይ ነገር ከመግለጽም በላይ የፊደላትን ትርጉም ብቻ ሳይሆን ነገረ ድኅነትንም በመስቀል ምልክት በታው/ተ መደምደሙን ያሳየናል፡፡ በግእዝ ፊደላት የድምጽ ለውጥን በማድረጋቸዉ ከጊዜ ብዛት ትርጉማቸዉ ሲዛባ እና ሥዕላዊ መገለጫቸው በተወሰነ ደረጃ ጎድሎ የዘፈቀደ ትርጉም ሊሰጣቸዉ ይችላል፡፡ ምሳሌ «ጥ»ሽ «ት» ወይም «ት»ሽ «ጥ» በመለወጥ ትርጉም ሊሰጥ ይችላል፡፡ በአንጻሩም በቋንቋው የድምጽ ትርጉም ሊሠራላቸው እና ከአንድ በላይ የተለያዩ ትርጉም ሊኖራቸዉ መቻሉ የማይቀር ነው፡፡ የፊደላቱ መለዋወጥ ግን ትርጉም የሚያበላሽ ምስጢር የሚያፋልስ መሆኑ የተረዳ ነው፡፡ ይኽንኑ ለመግለጽ ሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ «መዝገብ ፊደል» በተባለው መጽሐፋቸው እንዲህ ብለዋል፡፡

እንዳገኙ መጣፍ በድፍረት በመላ
የቋንቋ ደረመን የመጽሐፍ ቢስ ገላ
ንባብ የሚያሳክክ ምስጢር የሚቆምጥ
መልክአ ትርጓሜ የሚለዋውጥ፡፡
   

ይህን ማለታቸውም የፊደል ቁጥር ማጉደሉ፣ ምስጢር ማበላሸቱ ሥርዓተ ልሳን ማፋለሱ አንድና ብዙ ሩቅና ቅርብ ሴትና ወንድ አለመጠንቀቁ ጸያፍነቱና ግዴለሽነትን በማምጣቱ ነው፡፡ ለዚህም መፍትሔ ይሆን ዘንድ ታላቁ ሊቅ መልአከ ብርሃን አድማስ ጀምበሬ በመልእክታቸው ሊቃውንቱ ተስማምተው ጉባኤ ሠርተው ሊወያዩበት ይገባል ብለዋል፡፡ የፊደላቱ ምንነትና ምስጢር ሊጠፋ የቻለው እንደነ መልአከ ብርሃን አባባል የጽሕፈት ትምህርት ቤት ባህልና ትውፊት መረሳቱና ጸሓፍያን ለፊደላት ትርጉም ሳይጨነቁ ለቅርጽ ማማር ብቻ ትኩረት መስጠታቸው ነውና ይኽንኑ ሥርዓት ባለቅኔዎችም ባለማስተዋል ለቤት መምቻ ውበት መጠቀማቸው ነው፡፡

 

የግእዝ ፊደላት ለአኀዝ መሠረት ናቸው ስንል የምናነሳው ዝምድናቸውን ሲሆን ለምሳሌ የግእዝ 6 7 ቁጥሮች «-» ምልክት ሳይኖራቸዉ ይገኛሉ፡፡

የግእዝ ቁጥሮች መሠረታቸው ፊደል ነው፡፡ ስንል እንደ ፊደሎችም ቁጥሮች ከዘመን ዘመን ቅርጻቸዉን መልካቸውን ሲለዋውጡ እና የአሁኑን መልክ ሲይዙ ይታያሉ፡፡ በአጠቃላይም ቋንቋው የራሱ የሆነ ሥርዓተ ነጥብ የሥነ ጸሑፍ አካሄድ የምንባብ አጀማመር እንዳለው ይታወቃል፡፡

ዝክረ ልሳነ ሰብእ ቀዳማዊ

1. ግእዝ ምስለ ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዘመናት የፈተና ገፈታ ቀማሽ በመሆን፣ ልጆቿን እያበረታታች ለሀገራዊ ሀብት መጠበቅም እስከ ሰማዕትነት እያበረከተች በየአድባራቱና ገዳማቱ ጠብቃ አሳድጋ ለዚህ ትውልድና ዘመን ካቆየቻቸው ዕሤቶች አንዱ ግእዝ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ቤተ መዘክር፣ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት፣ ቤተ ክርስቲያን ግምጃ ቤት፣ ቤተክርስቲያን የሥልጣኔ ማዕከል፣ ቤተ ክርስቲያን ከተማ ሀገር በመሆን ስታገለግል ቆይታለች፡፡

ስለዚህም ነው በሀገሪቱ የታሪክና የመዛግብት ጥናት ላይ የረጅም እድሜ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ሪቻድ ፓንክረስት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሀገሪቱ ባህል ጠባቂ ናት ሲሉ በውዳሴ ዘጽድቅ የሚመሰክሩላት፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የግእዝን ሥነ ጽሑፍ ሆነ ቋንቋ እንደሚከተለው ጠብቃ አስረክባናለች፡፡

በየጉባኤያቱ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ማዕከለ ትምህርት በመሆን ለዘመናት ሕዝቡን አገልግላለች፡፡ በራሷ ባሕላዊ ሥርዓተ ትምህርት ዜማውን ቅኔውን ትርጓሜ መጻሕፍቱን በዚሁ ቋንቋ ስታስተላልፍ ቆይታለች፡፡ እነዚህም ትምህርቶች የሚከናወኑበትን ትምህርት ቤት ከቤተክርስቲያኗ ዐውደ ምሕረት ዙሪያ በተዘጋጁ የመቃብር ቤቶች፣ ዙሪያውን  በተሠሩ ጎጆች አልያም በዙሪያዋ በተተከሉ ዐጸዶች አትሮንሷን ዘርግታ፣ አዘጋጅታ፣ ዜማውን አሰምታ፣ ግሱን አስገስሳ ምስጢሩን አብራርታ አስተላልፋለች፡፡ ይህንንም ስታደርግ ለደቀመዛሙርቱ ከሰንበቴው ከደጀ ሰላሙ ረድኤት እያሳተፈች ነው፡፡

በሊቃውንት የሊቃውንት፣ የፍቅር ሀገር፣ ሕይወተ ክርስትና፣ ፍሬ በረከት ስላላቸውና ዘወትር ቃለ እግዚአብሔርን በመናገር፣ ደቀ መዝሙር ሲያጠፋ ሲያርሙ ሲሳሳት ሲያስተካክሉ፣ የተበላሸውን ሲያቀኑ ባሳለፉት ድካም ሀብተ ታሪክን አውርሰዋል፡፡ የደረሷቸውን ቅኔያት፣ የጻፏቸውን መጻሕፍት ዜና መዋዕላቱን ጭምር ሲደጉሱ፣ ሲኮትቱ የተሻለ ቅርጸ ፊደልን ሲያወርሱን ወዘተ ነፍሳቸውን ከሥጋቸው አብልጠው በመኖራቸው ነው፡፡ በመሆኑም ዳዊቱን እየደገሙ፣ መጻሕፍትን እየተረጎሙ ያብራሩበትም በዚሁ ልሳን ነው፡፡ በዚህ ሳይወሰኑ ሌትም ቀንም እንቅልፍ አጥተው ከማኅሌቱ፣ ከሰዓታቱ፣ ከጉባኤ ቤቱ ሳይለዩ ስለ ነገዋ ቤተ ክርስቲያን በመጨነቅ ያስተማሩትን ደቀ መዛሙር «ኦ ወልድየ ጽንዐ በጸጋሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘኅዱር ላዕሌከ በመንፈስ ቅዱስ» ልጄ ሆይ አድሮብህ ባለው በመንፈስ ቅዱስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋው ጽና ምከር አስተምር ብለው የቃል አደራ በመስጠት በየአህጉሩ ሲያሰማሩ ቆይተዋል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ጸሎታቸውን ለሀገር በሱባኤ ሲያደርሱ ኖረዋል፡፡

ደቀ መዛሙርቱ ሀገረ ሙላዳቸውን በመተው ደበሎ ለብሰው፣ ቁራሽን ተማምነው፣ አኮፋዳቸውን ከሰሌን አዘጋጅተው፣ ዳዊታቸውን በትከሻቸው አንግበው በትምህርተ ቤተክርስቲያን ዘመናቸውን ያቆዩ ተማሪዎችም ባለውለታ መሆናቸው የማይዘነጋ ነው፡፡ እድሜ ሳይገድባቸው ገና በልጅነት እድሜያቸው ጥሬ እየቆረጠሙ በውርጭ እየተነሡ ሀገር ለሀገር በመዞር ምስጢር ሲሸምቱ የአባቶቻቸውን ትውፊት በቃል በመጽሐፍ ያስተላለፉ ደቀ መዛሙርቱም እነዚሁ ናቸው፡፡ እነዚህም በሌሊት እየተነሡ ከመምህራቸው እግር ሥር ሆነው በብርዱ፣ በቁሩ ሲቀደሱ ሲያስቀድሱ፣ የሌሊቱን ዝናብ ታግሰው ሳይታክቱ በመምህራቸው ጓሮ በትጋት የተማሩባቸውን ጉባኤያት እያስታወሱ ሲያስተላልፉ ኖረዋል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ያለኀፍረት ራሱን ዝቅ አድርጎ በምእመናን ደጃፍ ዐረፍ ብሎ የተገኘውን እየተዘከሩ ወደ ጉባኤው ሲመለሱ እያዜሙ፣ ቅኔውን እየቆጠሩ፣ ወንዙን እየተሻገሩ፣ ተራራውን እየወጡ፣ እየወረዱ የአራዊቱን ድምጽ እየሰሙ፣ ተፈጥሮን እየቃኙ፣ ምስጢርን እያዩ ያዩትንም በቅኔው እየቀመሙ ለነባር ሲያስተላልፉ ቆይተዋል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ለክብረ በዓሉ ያለውን ቀለም በአፋፍ ላይ ሆነው እየቀጸሉ በጎጆአቸው ሌሊቱን ሲያዜሙ በራሳቸው ቋንቋ «አዛኘን» እስኪ በልልኝ  በመባባል እየተሳሳሉ ለዘመናት ትምህርቱን አስተላልፈዋል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን መምህራቸውን በእርሻ፣ በማሳ፣ በሥራ እየረዱ ነው፡፡

 
ምዕመናን ለሃይማኖታቸውና ለሀገራቸው ባላቸው ፍቅር ሃይማኖታቸውን ከቤተ ክርስቲያን አጣምረው ኖረዋል፡፡ በባህል ግንባታውም ተሳትፈዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ተማሪንም ከመሶባቸው ማዕድ ሳይሰስቱ እየመገቡ ሲያስተምሩ ቆይተዋል፡፡ ቤተክርስቲያን እንድትገለገል ጧፉን መጋረጃውን አሥራቱን ሲያስገቡ ባደረጉት አስተዋፅኦ የቤተ ክርስቲያኗ ሀብቷ እንዲህ ሊተላለፍ ችሏል፡፡ ዋዜማ እየደገሱ ቁመት ሲያስቆሙ ዕድሞ ሲያስከብሩ ኖረዋል፡፡

2. የግእዝ ቋንቋ እንዲያድግ ለምን አስፈለገ?

ባህል በቋንቋ ይለካል፡፡ እምነቶች ሥነ ሕዝብ ማኅበራዊ መሠረቶች /ዐምዶች ልምዶች ዕውቀቶች ሁሉ በቋንቋ አሉ፡፡ በአደጋ ላይ ያለ ቋንቋ ማለትም በአደጋ ላይ ያለ ዕውቀት አሳሳቢ፤ ባህል ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ስለ አገባብ የሚታወቀው ዕውቀት ካፀፀ መሠረት የለሽ ድካምን ያስከትላል፡፡

በመሆኑም ቋንቋ የኅብረተሰብእ /የአንድ ሕዝብ አካል ነው፡፡ ስለ ሕይወት ባህል ልምድ የሚፈስ ዕውቀት ሁሉ ትርጉም የሚኖረው በራስ ቋንቋ በሚገኝ ዕውቀት እንጂ የተጻፈን በመቀበል አለመሆኑ ደግሞ የራስ ቋንቋን ማወቅ ወሳኝ መሆኑን ያሳያል፡፡ ልሳናት በአባቶች ቅድመ አያቶች ቀሩ ማለት የልጆች ሀገራዊ አንደበታቸው ማንነት የሚጠብቁበት ኃይል ጠፋ ማለት ነው፡፡ የእኛ ማንነትና ታሪካችን ያለው የተቆራኘው በብዙ መንገድ ከቋንቋችን /ከግእዝ ጋር ነውና ያለበትን ደረጃ ልንመረምርና ልናስተውለው ይገባል፡፡ ሌላው ይቅርና መለያችን ልዩነታችን እንኳን በቋንቋችን ሰዋስው አገባብ ሊታወቅ ይችላል፡፡ ቋንቋችን ካልተጠበቀ የሚተላለፈው ዕውቀት ትውፊት ባለበት ይቆማል፡፡ አብሮ አስሮ የያዘቸውን እውቀቶች ፍልስፍናዎች ሁሉ ይዞ ይጠፋል፡፡ ነገር ሁሉ በአዲስ ይጀምራል፡፡ ሥር የሌለው በአሸዋ የተገነባ ሕንፃን ይመስላል፡፡ የሌሎች የባህል ጎርፍ በመጣ ጊዜ በቀላሉ ይወድቃል፡፡ ቋንቋን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን እንደገና ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ በስደት፣ በዝርፊያ በዓለም ዙሪያ በየቦታው ያሉትን የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ሊመረምሩ የሚችሉ ልጆች ሊተኩ ያስፈልጋል፡፡ የተበረዘውን ማቅናትና የጠፋውን ታሪክ መፈለግ፣ የተለየንን የጥበብ ምንጭ ፍለጋ መውጣት መውረድ ያስፈልጋል፡፡ ሊጠፉ የተቃረቡትንም መጠበቅና ብሎም ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎች ተጠቅሞ በመቅረጽ ለትውልዱ ማስተላለፍ ትልቁ ኃላፊነት ይኸው ነው፡፡

አፍሪካውያን ዛሬ ቋንቋቸውን ለመጠበቅ የሚያደክማቸው ለብዙ ዘመናት በተሰላ እቅድ ሥር ተጽዕኖ በመውደቃቸውና በሌላኛው የቅኝ ግዛት መንገድ ማለፋቸው ነው። እንዳልነው ይህ ችግር ደግሞ ዛሬም ከአፍሪካ ምድር ስላልተወገደ በአደጋ ላይ የነበሩ ዕውቀቶች ሁሉ ጠፍተዋል፡፡ መፍቀርያነ ባህል አፍረንጅም በመብዛታቸው ነባሩ/ የአከባቢው መንፈሳዊውም ሆነ ቁስ አካላዊው ዕውቀት እየተረሳ መጥቷል፡፡ ይህንን እየተረሳ ያለ ሀብት ደግሞ ለመጠበቅ ልምዱ ያላቸው ወላጆችና ሽማግሌዎች አስረካቢ ሕፃናት ተረካቢ ሊሆኑለት ይገባል፡፡ እንግሊዘኛቸውን ሲናገሩ በማበላሸታቸው የሚስቁ ይቅርታ የሚጠይቁትን ወጣቶችን ልብ አማርኛን ግእዝን ግን በማበላሸታቸው ግን ይቅርታ የማይጠይቁትን አእምሮ ሊያጠቁት ይችላሉ፡፡ በዚያውም ላይ የውጪውን ቋንቋ በመጠቀም የአንደበታቸው አርአያነት ብቻ ሳይሆን መልዕክቱ የተዛባ እየሆነ መጥቷል፡፡